Ajeba Emmanuel united church
Open in Telegram
እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” — ዮሐንስ 5፥24 (አዲሱ መ.ት)
Show more259
Subscribers
-224 hours
-27 days
-430 days
Posts Archive
ገላቲያ ክፍል 15 የምዕራፍ ሁለት መጨረሻ
#ሰው_ክርስቶስን_በማመን_ይፀድቃል
ገላ 2፡15-21
ሰው እግዚአብሔር አለ ብሎ በቤተእምነት ታዛ ስር ተጠልሎ በቅዱሳት መፅሐፍት ውስጥ ውሎ የሚያድረው ብሎም አንዳንዱ የምፅዋት እጁ የሚዘረጋው በተለያዩ ስፍራዎች የሚጓዘው ለምንድነው ብለን ብንጠይቅ መልሱ በአመዛኙ ከመፅደቅ ጋር ከዘላለም ሕይወት ጋር የተገናኘ ነው ። ጳውሎስ የሰው የውስጥ ጩኸት የሆነውን በእዚህ መፅሐፍ ውስጥ ላያዳግም ምላሽ ይሰጠዋል ።
በገላቲያ 2:15-21 ባለው ክፍል ውስጥ ጳውሎስ ሊናገር የፈለገበት የመጨረሻ ከፍታ ላይ የደረሰ ይመስላል ለእዚህም በጥቂት ቁጥሮች ውስጥ የአጠቃላይ የስለ መለኮት አረዳዳችንን ሊቃኝ የሚገባውን ንግግር ይናገራል ፡፡
🔸2:15 እኛ በፍጥረት አይሁድ ነን ኃጢአተኞችም የሆኑ አሕዛብ አይደለንም፤
ጳውሎስ ራሱን በማካተት እኛ አሕዛብ አይደለንም ይላል ፡፡ ይህ ማለት ሕግ እንደሌላቸው ከኪዳን እንደራቁት የተስፋ ቃል እንደሌላቸው አይነት ሰዎች አይደለንም ማለቱ ነው ፡፡እነርሱ ኃጢያተኞች ናቸው ፡፡( ሁሉ ኃጢያተኛ ቢሆንም አይሁዳውያን ራሳቸውን ለየት በማድረግ እነሱን እንዲህ ይጠሯቸው ነበር ።)
ጳውሎስ ግን አይሁዳዊ ነውና ራሱን ከአህዛብ ወገን እንዳልሆነ ይናገራል ፡፡ ስለ አይሁድ በሌላ ስፍራ እንዲህ ብሎ ነበር ፡፡
‹‹እነርሱ እስራኤላውያን ናቸውና፥ ልጅነትና ክብር ኪዳንም የሕግም መሰጠት የመቅደስም ሥርዓት የተስፋውም ቃላት ለእነርሱ ናቸውና፤›› ሮሜ 9፡4
ስለዚህ ጳውሎስ የእዚህ ማህበረሰብ አባል እንደሆነ ይናገራል ፡፡ይህ ካለ በኋላ ግን ነገሩን ወደ ዋና ጉዳዩ ያዞርና ነገር ግን ብሎ መፃፍ የሚፈልገውን ይለጥቃል ይዘልቃል ይጀምራል ፡፡
🔸2:16 " ነገር ግን ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንዲጸድቅ እንጂ በሕግ ሥራ እንዳይሆን አውቀን፥ ሥጋን የለበሰ ሁሉ በሕግ ሥራ ስለማይጸድቅ፥ እኛ ራሳችን በሕግ ሥራ ሳይሆን በክርስቶስ እምነት እንጸድቅ ዘንድ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል።"
👉ነገር ግን ይልና አንድ አካል ይጠራል ‹‹ሰው››
👉ቀጥሎ ይህንን ቃል በሌላ ቃል ተክቶ ያስቀምጠዋል ፡፡ ስጋን የለበሰ ሁሉ ‹‹ ሰው ማለቱ ነው ››
ሰው ምን ?
🔸በክርስቶስ በማመን ይፀድቃል
🔸በሕግ ስራ አይፀድቅም (በሕግ ስራ እንዳይሆን አውቀን )
ስለዚህ ለመፅደቅ ማመን እንደ ቅደመ ሁኔታ ስለሆነ ለመፅደቅ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል ይላል ጳውሎስ ። ይህ ማለት እንኳን እናንተ ሕግ ያሌላችሁ ቀርቶ እኛ ሕግ የተሰጠን እንኳ የምንፀድቀው ክርስቶስን በማመን ነው እያለ ነው ።
👉በሌላ ቦታ ሰው ለመዳን ከሰው የሚጠበቀው ምን እንደሆነ እና የእግዚአብሄር ፍቃድ ምን እንደሆነ ይነግረናል ፡፡ይህም
‹‹በእግዚአብሔር ጥበብ ምክንያት ዓለም እግዚአብሔርን በጥበብዋ ስላላወቀች፥ በስብከት ሞኝነት #የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኖአልና።››
በስብከት ሞኝነት ማመን!!
🙏ይህን ማለት ጥበብ በማይመስለው የክርስቶስ ኢየሱስ ስቅለት ውስጥ መዳኔ አለ ለእኔ ነው የሞተው ብሎ ማመን ነው ፡፡
ጳውሎስ ይህንን ለማፅናት ሌሎች ንግግሮችን በእዚህ አውድ ውስጥ ይጠቀማል፡፡ ይህ ከመናገሩ በፊት ግን በእምነት የፀደቀ ሰው በኃጢያት የሚመላለስ እንዳይሆን ይልቅ በክርስቶስ ጋር የተሰቀለ መሆኑን ያሳስባል ፡፡ ገላ 2፤17-20
‹‹ነገር ግን በክርስቶስ ልንጸድቅ የምንፈልግ ስንሆን ራሳችን ደግሞ ኃጢአተኞች ሆነን ከተገኘን፥ እንግዲያስ ክርስቶስ የኃጢአት አገልጋይ ነዋ? አይደለም።ያፈረስሁትን ይህን እንደ ገና የማንጽ ከሆንሁ ራሴ ሕግ ተላላፊ እንድሆን አስረዳለሁና።እኔ ለእግዚአብሔር ሕያው ሆኜ እኖር ዘንድ በሕግ በኩል ለሕግ ሞቼ ነበርና።ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።››
ይህንን ክፍል ብናብራራው እጅግ ብዙ ቁም ነገሮች የምናገኝበት ነው ፡፡ ወደ ፊት በፒዲፍ መፅሐፍ አድርጌ አስፍቼ እንዲደርሳቹሁ አደርጋለሁ ( ፀጋው ይርዳኝ) ፡፡ ጳውሎስ ከእዚህ ንባብ በኋላ የመጀመሪያ ሃሳቡን የሚያጠናክርበት አረፍተ ነገር ይናግራል
🔸2: 21 ‹‹የእግዚአብሔርን ጸጋ አልጥልም፤ ጽድቅስ በሕግ በኩል ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።››
በሕግ ስራ እፀድቃለው ብሎ ማለት የእግዚአብሄር ፀጋ እንደመጣል ነው ፡፡ ስለዚህ በእግዚአብሄር ላይ ተደግነፈን በክርስቶስ ሞት እንፀድቃለን ብለን በማመን የዘላለም ሕይወት በእርሱ እንደምናገኝ በማመን በእርሱ ሆነን እንኑር!!
ይህ የወንጌላት የጳውሎስ እና የሌሎቹም ሐዋሪያት ትምህርት ነው ።
ፀጋ ይብዛላችሁ ።
✍️ Girum Difek
ከምዕራፍ ሶስት እስከ ስድስት ያለውን ይህንን ጨምሮ በአንድ ላይ በፒዲፍ በነፃ ለእናንተ ለሚቅረብ እሞክራለሁ ።
ፀልዩልኝ !!
በድጋሚ ፀጋ እና ሰላም ይብዛላችሁ ።
የዕለቱ የቃሉ መልዕክት ክፍል ፦
ማርቆስ 4:35-41
ርዕስ፦#ፍፁም_ፀጥታ_ሆኗል!
ማርቆስ 4
³⁵ በዚያም ቀን በመሸ ጊዜ፦ ወደ ማዶ እንሻገር አላቸው።
³⁶ ሕዝቡንም ትተው በታንኳ እንዲያው ወሰዱት፥ ሌሎች ታንኳዎችም ከእርሱ ጋር ነበሩ።
³⁷ ብርቱ ዐውሎ ነፋስም ተነሣና ውኃ በታንኳይቱ እስኪሞላ ድረስ ማዕበሉ በታንኳይቱ ይገባ ነበር።
³⁸ እርሱም በስተኋላዋ ትራስ ተንተርሶ ተኝቶ ነበር፤ አንቅተውም፦ መምህር ሆይ፥ ስንጠፋ አይገድህምን? አሉት።
³⁹ ነቅቶም ነፋሱን ገሠጸው ባሕሩንም፦ ዝም በል፥ ፀጥ በል አለው። ነፋሱም ተወ ታላቅ ፀጥታም ሆነ።
⁴⁰ እንዲህ የምትፈሩ ስለ ምን ነው? እንዴትስ እምነት የላችሁም? አላቸው።
⁴¹ እጅግም ፈሩና፦ እንግዲህ ነፋስም ባሕርም የሚታዘዙለት ይህ ማን ነው? ተባባሉ።
➫ እስራኤላውያንን እግዚአብሔር ከግብፅ ባርነት ባወጣቸው ጊዜ በመንገድ ላይ የዮርዳኖስ ወንዝ በመንገዳቸው ሆነው እንዳያልፉ ዘግቶ ነበረ ነገር ግን እግዚአብሔር የቃል ኪዳንን ሕዝብ ለመሻገር ታቦቱን እንዲያስቀድሙት ወደ ወንዙን ይዘው እንዲገቡ በታቦቱም ምክንያት በደረቅ ምድር በሰላም እንድሻገሩ አድርጎአቸዋል። እኛም ከሞት ባሕር በሰላም የተሻገረንበት ታቦተችን ኢየሱስ ነው።
#ወደ_ማዶ_እንሻገር ያለው ኢየሱስ ታላቁን የኃጢአትን የሞትን የጨለማን ነፋስ ፀጥ አድርጓል። የሞትን ነፋስ ባሕሩንም ጌታ ኢየሱስ ዝም በል፥ ፀጥ በል አለው ፀጥታም ሆነ።
✒ ጌታ ኢየሱስ እንደቃሉ ወደ ማዶ አሻግሮናል
ሉቃስ 8፡²²
#ጌታ_ታማኝ_ነው።
✒ ታማኝነትህ ብዙ ነው። ሰቆ.ኤር 3፥23
#እንሻገር ብሎ የተነገረው እርሱ ኢየሱስ ታማኝ ነው።
✒እግዚአብሔር ግን የታመነ ነው፥ ለእናንተም የሚነገረው ቃላችን አዎንና አይደለም አይሆንም።
— 2ኛ ቆሮ 1፥18
✒ ባናምነው፥ እርሱ የታመነ ሆኖ ይኖራል፤ ራሱን ሊክድ አይችልምና።
— 2ኛ ጢሞቴዎስ 2፥13
#የተስፋን_ቃል_የሰጠው_የታመነ ነውና እንዳይነቃነቅ የተስፋችንን ምስክርነት እንጠብቅ፤
— ዕብራውያን 10፥23
መምህር ታረቀኝ ተገኝ ፀጋው ይብዛልህ
ገላቲያ ክፍል አስራ አራት
#ግብዝነት_የወንጌል_እንቅፋት
ገላ 2:11-14
ከሁለት ሺ አመት በፊት ኢየሱስ ያስቸግሩት ይታገሉት የነበሩት ግብዞች ነበሩ ። ለእውነተኛ አገልጋዮች እንደ ግብዞች ፈታኝ ያለ የለም ብል አላገነንኩም ።ግብዞች የአገልግሎት ማቆሚያ ምክንያት ናቸው ግብዞችን የተቋቋመ በእውነት ፀጋ በዝቶለታል ። ግብዝ ማለት ያልሆነውን ሆኖ የሚተውን ተዋናይ ማለት ነው ። አስመሳይ ውሸተኛ እውነተኛ መሳይ ማለት ነው ።
ይህ ደግሞ በሐይማኖት ስር ሲሆን እጅግ አደገኛ እና መጥፎ ይሆናል ። ለእዚህ ነው ኢየሱስ እነዚህን ሰዎች በተደጋጋሚ ሲቃወም የነበረው ። ኢየሱስ በማቲዎስ ሀያ ሶስት የጻሕፍት ፈሪሳውያንን ግብር ሲቃወም የምናየው ለእዚሁ ነው ።አጅግ ከባድ ቃላቶችን በመጠቀም የግብራቸውን እኩይነት ይገልጣል ።
ግብዟች
1ኛ መንግስተ ሰማይን በሰዎች ፊት ይዘጋሉ
“እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ መንግሥተ ሰማያትን በሰው ፊት ስለምትዘጉ፥ ወዮላችሁ እናንተ አትገቡም የሚገቡትንም እንዳይገቡ ትከለክላላችሁ።”
— ማቴዎስ 23፥13
2ኛ በመንፈሳዊነት ሰበብ ምስኪኖችን የሚበዘብዙ ናቸው
“እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በጸሎት ርዝመት እያመካኛችሁ የመበለቶችን ቤት ስለምትበሉ፥ ወዮላችሁ፤ ስለዚህ የባሰ ፍርድ ትቀበላላችሁ።”
— ማቴዎስ 23፥14
3ኛ መንፈሳዊ የሚመስሉ አስመሳዮች ናቸው
“እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ አንድ ሰው ልታሳምኑ በባሕርና በደረቅ ስለምትዞሩ፥ በሆነም ጊዜ ከእናንተ ይልቅ ሁለት እጥፍ የባሰ የገሃነም ልጅ ስለምታደርጉት፥ ወዮላችሁ።”
— ማቴዎስ 23፥15
ሰሩ ለመባል የሚሰሩ እንጂ የሰው ነብስ ግድ ብሏቸው አያፀኑትም ።
4ኛ ዋናውን ነገር የሚተው በጥቂቷ ትኩረት የሚያደርጉ ናቸው
ማቴዎስ 23
²³ እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ ከአዝሙድና ከእንስላል ከከሙንም አሥራት ስለምታወጡ፥ ፍርድንና ምሕረትን ታማኝነትንም፥ በሕግ ያለውን ዋና ነገር ስለምትተዉ፥ ወዮላችሁ፤ ሌላውን ሳትተዉ ይህን ልታደርጉ ይገባችሁ ነበር።
²⁴ እናንተ ዕውሮች መሪዎች፥ ትንኝን የምታጠሩ ግመልንም የምትውጡ።
5ኛ ለውጪያዊ ነገር የሚጨነቁ ናቸው
“እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በውስጡ ቅሚያና ስስት ሞልቶ ሳለ የጽዋውንና የወጭቱን ውጭ ስለምታጠሩ፥ ወዮላችሁ።”
— ማቴዎስ 23፥25
ከእዚህ በተጨማሪ ብዙ ነገር ማለት ይቻላል ይህንን እዚህ ላይ እናቁምና በእዚህ አይነት መንፈስ የአዲስ ኪዳን አገልጋዮች ተይዘው ስናይ ምን ይባላል ? ሊያው ጴጥሮስና በርናባስ ሌሎችም ናቸው ። አገልጋዮች ምናልባት በእዚህ አይነት መንፈስ ተይዘው ከሆነ ቶሎ ራሳቸውን በማየት መመለስ አለባቸው ።
ጳውሎስ እነ ጴጥሮስ ግብዝ ሆነው ሲያገኛቸው እንዲህ ይላቸዋል በተለይ ጴጥሮስን
ገላትያ 2
¹¹ ነገር ግን ኬፋ ወደ አንጾኪያ በመጣ ጊዜ ፊት ለፊት ተቃወምሁት፥ ይፈረድበት ዘንድ ይገባ ነበርና።
¹² አንዳንድ ከያዕቆብ ዘንድ ሳይመጡ ከአሕዛብ ጋር አብሮ ይበላ ነበርና፤ በመጡ ጊዜ ግን ከተገረዙት ወገን ያሉትን ፈርቶ ያፈገፍግ ነበርና ከእነርሱ ተለየ።
¹³ የቀሩትም አይሁድ ደግሞ፥ በርናባስ ስንኳ በግብዝነታቸው እስከ ተሳበ ድረስ፥ ከእርሱ ጋር አብረው ግብዞች ሆኑ።
¹⁴ ነገር ግን እንደ ወንጌል እውነት በቅንነት እንዳልሄዱ ባየሁ ጊዜ በሁሉ ፊት ኬፋን፦ አንተ አይሁዳዊ ሳለህ በአይሁድ ኑሮ ያይደለ በአሕዛብ ኑሮ ብትኖር፥ አሕዛብ በአይሁድ ኑሮ ሊኖሩ እንዴት ግድ አልሃቸው? አልሁት።
የአሕዛብ ሰዎችን ለብቻቸው ሲያገኛቸው አብሮቸው ምግብ ይበላል የአይሁድ ሰዎች ሲመጡ ከእነሱ ዞር ይላል ። ይሄ በቤተክርስቲያን ውስጥ ልዩነትን በመፍጠር ለወንጌል እንቅፋት እንደሚሆን ጳውሎስ ገብቶታል ።ስለዚህ ነው መቃወሙ ለወንጌል አንቅፋት ይሆናልና።
ወገኖቼ ሆይ ግብዝነትን ከእኛ እናስወግድ አስመሳይነትን እናጥፋ የዛኔ ወንጌል በድፍረት መስበክ እንችላለን ።
የጌታ ፀጋ ይብዛልን አሜን ።
ይቀጥላል ..
✍️ Girum Difek
@followers
@highlight
ገላቲያ ክፍል 13
#እግዚአብሔር_የሰው_ፊት_አይቶ_አያዳለም !!
እኛ አማኞች ደስ እያለን በእምነት እና በእርግጠኝነት እግዚአብሔርን እንድንከተለው እንድንታመንበት ከሚያደርጉን ነገሮች አንዱ በእርሱ ዘንድ እንደ ሰው አድሎ አለመኖሩ ነው። 🔸በእርሱ እርግጠኛ ነን ፍትህ የሚያዛባ አይሆንም
🔸በእርሱ እርግጠኛ ነን ለሌሎች አዳልቶ እኛን አይጥለንም ።
🔸በእርሱ እርግጠኛ ነን እርሱ ታማኝ አምላክ ነው አያዳላም ።
ሰው በተለያየ ሚዛን መዝኖ ያዳላል ። ለብሄሩ ሰው ያዳላል ዘር እና ጎሳ ቆጥሮ ይበይናል ።ሰው ገንዘብ አይቶ ያዳላል ። የኪሱን ውፍረት የገንዘቡን ረብጣነት አይቶ ያዘነብላል ። ገንዘብ ላላቸው ብቻ የሚፈርዱ አዳዮች በምድራችንም ሞልተዋል። በስልጣን ምክንያት ሰው ያዳላል ። ለባለ ስልጣን የሚያዳሉ ብዙዎች በምድራችን አሉ ። እንዲህ እያልን ብዙ መጥቀስ እንችላለን ።
ጳውሎስ ግን እንዲህ ይላል ገላ 2:6
እግዚአብሔር የሰው ፊት አይቶ አያዳለም !!
“አለቆች የመሰሉት ግን፥ በፊት ማን እንደ ነበሩ አይገደኝም፤ #እግዚአብሔር_የሰውን_ፊት_አይቶ_አያደላም፤ አለቆች የመሰሉት አንዳች እንኳ አልጨመሩልኝምና፥”
— ገላትያ 2፥6
እግዚአብሔር የሆነ ሰው ብቻ የሚል የድነትም ፕሮግራም የለውም የዘላለም ሕይወትን ለሁሉ እንዲሆን ልጁን የመስዋት በግ አድርጎ ልኳል ። ከእዚህ ጋር ተያይዞ ጳውሎስ በእዚህ አውድ ውስጥ ግን ሁለት ዋና ጉዳዮችን ያነሻል የዘላለም ድነት እና አገልግሎት ።ገላ 2:6-10
1ኛ በዘላለም ድነት በአሕዛብ እና በአይሁድ መካከል ባለው አጀንዳ እግዚአብሔር አድሎ አያደርግም ።
አይሁድ ክርስቲያኖች በሰአቱ እግዚአብሔር የእነሱ እንጂ የሁሉ አይመስላቸውም ነበር ይህ ማለት የእግዚአብሔር የማዳን አጀንዳ ለአይሁድ እንጂ ለአህዛብ ነው ብለው ማሰብ ይከብዳቸዋል ። ይሄ ጴጥሮስ እንኳ የሚያምንበት እርሱን እንኳን የፈተነ ጉዳይ ነበር። በሐዋርያት ስራ መፅሐፍ ምዕራፍ አስር ላይ የቆርኔሌዎስ ታሪክ የሚነግረን እግዚአብሔር አህዛብን ለማዳን ሲፈልግ ጴጥሮስ ደግሞ ሲታገል መሆኑን ነው ። ቆርኔሌዎስ አይሁድ አልነበረም ።
እግዚአብሔር ለጴጥሮስ በሕልም /በተመስጦ የሚያሳየው ይህንን የእግዚአብሔርን የማዳን አጀንዳ ነው ለአሕዛብም ለሁሉ ይህ መዳን እንደሆነ እንዲገባው ነበር ። እርሱ ግን እግዚአብሔርን የአድሎ አምላክ አድርጎ ታገለ ።
አይሁድ አባታችን አብርሃም ነው ይላሉ ነገር ግን እግዚአብሔር የአሕዛብም አባት እንዲሆን አብርሃምን እንዳሰበው ዘንግተዋል። ጳውሎስ ይህንን ያስረዳቸዋል ።የእግዚአብሔር አጀንዳንም በተለያዩ መልዕክቶቹ ይናገራል ።
የተወሰኑ ክፍሎችን እንመልከት።
ሮሜ 4
¹¹ ሳይገረዝም በነበረው እምነት ያገኘው የጽድቅ ማኅተም የሆነ የመገረዝን ምልክት ተቀበለ፤ ይህም እነርሱ ደግሞ ጻድቃን ሆነው ይቆጠሩ ዘንድ ሳይገረዙ ለሚያምኑ ሁሉ አባት እንዲሆን ነው፥
¹² ለተገረዙትም አባት እንዲሆን ነው፤ ይኸውም ለተገረዙት ብቻ አይደለም ነገር ግን አባታችን አብርሃም ሳይገረዝ የነበረውን የእምነቱን ፍለጋ ደግሞ ለሚከተሉ ነው።
ገላትያ 3
⁶ እንዲሁ አብርሃም በእግዚአብሔር አመነና ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት።
⁷ እንኪያስ ከእምነት የሆኑት እነዚህ የአብርሃም ልጆች እንደ ሆኑ እወቁ።
⁸ መጽሐፍም እግዚአብሔር አሕዛብን በእምነት እንዲያጸድቅ አስቀድሞ አይቶ፦ በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ።
⁹ እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ።
እግዚአብሔር የአሕዛብም አምላክ ነው ።
ሮሜ 3
²⁸ ሰው ያለ ሕግ ሥራ በእምነት እንዲጸድቅ እንቆጥራለንና።
²⁹-³⁰ ወይስ #እግዚአብሔር_የአይሁድ_ብቻ_አምላክ_ነውን? #የአሕዛብስ_ደግሞ_አምላክ_አይደለምን? አዎን፥ የተገረዘን ስለ እምነት ያልተገረዘንም በእምነት የሚያጸድቅ አምላክ አንድ ስለ ሆነ የአሕዛብ ደግሞ አምላክ ነው።
ስለዚህ በእግዚአብሔር የማዳን እቅድ ውስጥ አድሎ የለም እግዚአብሔር አይሁድም ደግሞ አሕዛብም እንዲድኑ ይፈልጋል ።
ጳውሎስ እንዲህ የሚለን ለዛ ነው ።
“ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው።”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥3-4
2ኛ በአገልግሎት ሹመት ውስጥ አድሎ የለም ።
ጳውሎስ ሐዋሪያ ነው ጴጥሮስም ሐዋሪያ ነው የጴጥሮስ ሐዋሪያነት ከጳውሎስ ሐዋሪያነት አይበልጥም ለሁለቱም የሰራው ራሱ እግዚአብሔር ነው ። ጳውሎስ እንዲህ የሚለው ለዛ ነው ።
“ተመልሰው ግን ጴጥሮስ #ለተገረዙት የሆነው ወንጌል አደራ እንደ ተሰጠው እንዲሁ ለእኔ #ላልተገረዙት የሆነው ወንጌል አደራ እንደ ተሰጠኝ አዩ፤”
— ገላትያ 2፥7
እንኳን በሁለት ሐዋሪያቶች መሐል በማንኛው የፀጋ ስጦታዎች ላይ መበላለጥ የለም ። እግዚአብሔር እርሱ እንደወደደ ለአንዷ አካል መታነፅ የሚሰው ስጦታ ስጦታ እንጂ የበላይ እና የበታች የለም ።
ይህን ሃሳብ ስንጠቀልል ይህን ያዙ
እግዚአብሔር እንደ ሰው አይደለም ፊት አይቶ አያዳለም ። ስለዚህ እመኑት በእርሱ ላይ የፀና እምነት ይኑራቹ ይህንን የእግዚአብሔር የማዳን አጀንዳ ለፍጥረት ሁሉ እንደሆነ እያሰባችሁ ወንጌልን ይዛችሁ ገስግሱ ። በተሰጣችሁ የፀጋ ስጥታም ጌታን በታማኝነት አገልግሉ ።
እግዚአብሔር ፀጋ ይጨምርላችሁ
አሜን!!
ይቀጥላል ......
✍️ Girum Difek 💓
ማን ያስፈልገናል?
ቅሬታዎች ናቸዋ!!
ቅሬታዎች እና ዘመን ጥብቅ ቁርኝነት አላቸው። ቅሬታዎች በተበላሸ ዘመን እና የህይወት ስርአት ውስጥ ከተበላሸው አለም ጋር ራሳቸውን ሳያነካኩ በእግዚአብሔር ፀጋ ድል እየነሱ የሚኖሩ በተስፋ ሃይል የሚሰማሩ ናቸው።
ያለንበት ዘመን መፍትሔ የሚሻ ችግርን አዝሏል ።ይህ ችግር ከቤተ መቅደሱ እስከ ቤተ መንግስቱ ከቤተ መንግስቱ እስታች ማህበረሰብ የወረደ በሃሳብ ሲጠነጠን ኖሮ በተግባር እየተፈፀመ ያለ እኩይ ሃሳብ ያለበት ጊዜ ነው።
አስመሳይነት,ውሸት,ዘረኝነት ,ጭካኔ,አረመኔያዊነት ,ትዕቢት ,ገንዘብ ወዳድነት ,የስነ ምግባር ዝቅጠት, መወገዝ ያለባቸው ሃሳቦች የመወደሻ አጀንዳ ሆነው የቀረቡበት ዘመን ነው ።
ታዲያ ይህ እንዴት ይጠራል ?
ችግርን ማወቅ እንጂ ችግርን ብዙ ማውራት መፍትሄ ሆኖ አያውቅም! መጀመሪያ ችግራችንን እንረዳው !! አንድ ሃኪም ረጅም ሰአት ስለ በሽታው ለታካሚው ቢያወራው መፍትሄ ግን ሊሆነው የሚችለውን ባይነግረው ወይም ባይሰጠው ምን ይፈይዳል? ነገር ግን ስለ ችገሩ ማወቁ ለመፍትሄው መሰረት ነው። እኛም እንዲሁ ችግራችንን እንረዳው ከዛ ችገራችንን ደጋግመን እናውራው ሳይሆን ወደ መፍትሄው እንምጣ!! የብዙ ሰዎች ችግር ይሄ ነው ችገሩ ላይ ተተክሎ መቅረት!!
የተበላሸን የህይወት ስርአት የተበላሸን አለም እና ቤት የሚለውጡ እግዚአብሔር ለአላማ የሚጠቀምባቸው ሰዎች ያስፈልጉናል። አንተ ወይም አንቺ ልትሆኚ ትችያለሽ !!
የተግባር ሰዎች ሰርተው የሚያሳዩ ቆራጦች ለአላማቸው እስከ ሞት የመሄዱ ብርቱዎች ሰንፍናን የሚፀየፉ ትዕግስተኞች ትዕቢትን የሚጠየፉ ከኔ በላይ ላሳር የማይሉ የደከመውን ለመሸከም ልብ ያላቸው ... ቅሬታዎች!!
ቤተ ክርስቲያን ችላ ልትይው የማይገባሽ ስራ ቅሬታዎችሽን ማስታጠቅ ነው ።እንደ ሙሴ ብድራታቸውን የሚመለከቱ ቅሬታዎችን ማብቃት ነው።
ፀሃፈዎች ዛሬ ያለንበት ውጥንቅጥ ትላንት በተሰነደ የሃሳብ ክታብ መሆኑን አውቃቹ ለነገ ዛሬን የሚቀይር ጠቃሚ ፅሁፍ ፃፉ!!
ሰባኪዎች መድረክቻችሁን ዋጁ ስለ ሰላም ስለ ፍቅር ስለ እውነት ሃዋሪያቱ ስላስተማሩት የስነ ምግባር መርህ ኢየሱስ በዚህ ምድር እንዴት መመላለስ እንደሚገባን የነገረንን በፍቅር ስበኩ!!
አስተማሪዎች ፈያጅ ስነ መለኮት ያሻናል።ጉዳያችን ባልሆኑ ነገሮች ከምንዘባዘብ ጠቃሚ በሆኑ ለትውልድ የሚጠቅሙ ቤተ ክርስቲያንን ሊያግዙ የሚችሉ በሰላ አእምሯቹ ተጠቅማቹ አስተምሩን!!
ይህንን ትውልድ የሚያሻግሩ ለነገ መሰረት የሚጥሉ ቅሬታዎችን እናፍራ!!
ይህ ማምለጫችን ነው !!
ጌታ ሆይ ፀጋ ያግዘን አሜን!!
እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ተናግሮናል 👇
✒#እርሱን_ስሙት🙌
ሉቃስ 9
³⁰ እነሆም፥ ሁለት ሰዎች እነርሱም ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ይነጋገሩ ነበር፤
³¹ በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር።
³² ነገር ግን ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት እንቅልፍ ከበደባቸው፤ ነቅተው ግን ክብሩንና ከእርሱ ጋር ቆመው የነበሩትን ሁለት ሰዎች አዩ።
³³ ከእርሱም ሲለዩ ጴጥሮስ ኢየሱስን፦ አቤቱ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነውና አንድ ለአንተ አንድም ለሙሴ አንድም ለኤልያስ ሦስት ዳሶች እንሥራ አለው፤ የሚለውንም አያውቅም ነበር።
³⁴ ይህንም ሲናገር ደመና መጣና ጋረዳቸው፤ ወደ ደመናውም ሲገቡ ሳሉ ፈሩ።
³⁵ ከደመናውም፦ የመረጥሁት ልጄ ይህ ነው፥ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።
³⁶ ድምፁም ከመጣ በኋላ ኢየሱስ ብቻውን ሆኖ ተገኘ። እነርሱም ዝም አሉ ካዩትም ነገር በዚያ ወራት ምንም ለማንም አላወሩም።
✒እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።
ማቴ17:5
#ሙሴም_ስለእርሱ_ተናግሮ_ነበረ👇
✒“ሙሴም ለአባቶች፦ ጌታ አምላክ እኔን እንዳስነሣኝ ነቢይን ከወንድሞቻችሁ ያስነሣላችኋል፤ በሚነግራችሁ ሁሉ እርሱን ስሙት።
— ሐዋርያት 3፥22
✒ይህ ሰው ለእስራኤል ልጆች፦ እግዚአብሔር ከወንድሞቻችሁ እንደ እኔ ያለ ነቢይ ያስነሣላችኋል፤ እርሱን ስሙት ያላቸው ሙሴ ነው።
— ሐዋርያት 7፥37
በአብ የተወደደውን ልጁን መስማት ይሁንልን 🙌
#ደማቅመቅ ብላችሁ ዋሉልኝ💚🙌
መልካም ቀን
📝Teka.E
የእግዚአብሔር ተስፋዎች አዎ እና አሜን ናቸው!
📌 የእግዚአብሔር የተስፋ ቃል ሁሉ አዎን በእርሱ ነውና በእርሱም አሜን በእርሱ ለእግዚአብሔር ክብር በእኛ በኩል አለ። 2ኛ ቆሮንቶስ 1፡20
📌 በመጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ ያለው የእግዚአብሔር የተስፋ ቃል ሁሉ አዎ እና አሜን ነው። አንዳንድ ጊዜ አዎ እና አንዳንድ ጊዜ አይደለም አይደለም። ዘመኑ ሁሉ አዎ ነው አሜን ነው። አንዳንድ ሰዎች የእግዚአብሔር ተስፋዎች ሁልጊዜ አዎ እና አሜን ስንል አይወዱም ምክንያቱም በሕይወታቸው የእግዚአብሔርን ተስፋዎች ስላላጋጠሟቸው ነው። ምናልባት በጤናቸው ውስጥ፣ በአካሎቻቸው ውስጥ አጠቃላይ ጤና አያገኙም።
📌 ስለዚህ አንዳንድ ጊዜ የእግዚአብሔር ተስፋዎች አዎ እና አንዳንድ ጊዜ አይደለም ሊሆን ይችላል ብለው ያስባሉ።አይደለም መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ተስፋዎች ሁልጊዜ አዎ እና አሜን ናቸው ይላል።ያጋጠመን ነገር ምንም አይደለም፣ ምንም እንኳን ቃሉ ከሚናገረው ጋር የሚቃረን ቢሆንም፣ በቃሉ ላይ ያለንን እምነት መቀጠል አለብን። ልምዳችን የእግዚአብሔር የበረከት መለኪያ አይደለምና የእግዚአብሔር ቃል መለኪያው ነው።
📌 በልባችሁ ስታስገቡ ነው እግዚአብሔር የሚሰጣችሁ ቃል ሁሉ አዎን እና አሜን የሚሆነው ኢየሱስ በተጠናቀቀ ስራው ያዘጋጀላችሁን ማየት አትችሉ ይሆናል።ሐዋርያው ጳውሎስ፡- “ነገር ግን እግዚአብሔር እውነተኛ እንደ ሆነ ለእናንተ የገባነው ቃላችን አዎንና አይደለም አልነበረም። በእኛ በኩል በእኔና በስልዋኖስ በጢሞቴዎስም በመካከላችሁ የተሰበከ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ አዎን እና አይደለም አልነበረም ነገር ግን በእርሱ አዎን ነበረ።
📌 ሐዋርያው ጳውሎስ የሰበኩት ቃል አዎን እና አይደለም አይደለም እያለ ነው። በክርስቶስ የሰበኩት ቃል አዎን እና አሜን ነበርና። ስለዚህ የምንሰብከው የእግዚአብሔር ቃል ሁኔታችን ቢለወጥም ሊለወጥ ይችላል። ቃሉ አዎንና አሜን ነው። እምነታችንን በእግዚአብሔር ቃል ላይ እናሳርፍ እና በህይወታችን የእግዚአብሔርን ተስፋዎች እናገኛለን ።
🙏ከእኔ ጋር ጸልዩ የሰማይ አባት፣ ለእኔ ስለሰጠህኝ ታላቅ መዳን አመሰግንሃለሁ። ቃል ኪዳኖችህ ሁሉ አዎን እና አሜን መሆናቸውን አውቄ በቃልህ ላይ አርፌያለሁ። እኔን ያጋጠመኝ ነገር ምንም ለውጥ አያመጣም።እምነቴ በቃል ኪዳኖችህ ላይ ነው።ምክንያቱም አዎ እና አሜን ናቸው።
📝Eyob grace ❤🙌
ፀጋው ይብዛልክ!❤
