en
Feedback
የመዝሙር ግጥሞች ☦️

የመዝሙር ግጥሞች ☦️

Open in Telegram

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ ቆየት ያሉና አዳዲስ👇👇 👏 የቸብቸቦ መዝሙራት  🎻 የበገና መዝሙራት   👑 የቅዱሳን መዝሙራት  🙏 የንስሐ  መዝሙራት 💍 የሠርግ መዝሙራት   🌦 ወቅታዊ መዝሙራት https://t.me/Yemezmur_Gitimoche ለጥያቄ ለአስተያየት ማስታወቂያ ለማሰራት @fikreabe

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel የመዝሙር ግጥሞች ☦️

Channel የመዝሙር ግጥሞች ☦️ (@yemezmur_gitimoche) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 24 809 subscribers, ranking 2 989 in the Religion & Spirituality category and 1 402 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 24 809 subscribers.

According to the latest data from 08 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 493 over the last 30 days and by 30 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 1.63%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 2.53% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 404 views. Within the first day, a publication typically gains 627 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 3.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ ቆየት ያሉና አዳዲስ👇👇 👏 የቸብቸቦ መዝሙራት  🎻 የበገና መዝሙራት   👑 የቅዱሳን መዝሙራት  🙏 የንስሐ  መዝሙራት 💍 የሠርግ መዝሙራት   🌦 ወቅታዊ መዝሙራት https://t.me/Yemezmur_Gitimoche ለጥያቄ ለአስተያየት ማስታወቂያ ለማሰራት @fikreabe

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 09 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

Buy Ad
24 809
Subscribers
+3024 hours
+1367 days
+49330 days
Posts Archive
🌻🌻🌻አዲስ ዓመት 🌼🌼🌼 🌻🌻🌻አዲስ Skill🌼🌼🌼 🎉🎉Free የGraphics Class🎊🎊 በPC ለምትሰሩ የ 👉 Photoshop 👉 Illustrator course በስልክ ለ
🌻🌻🌻አዲስ ዓመት 🌼🌼🌼 🌻🌻🌻አዲስ Skill🌼🌼🌼 🎉🎉Free የGraphics Class🎊🎊 በPC ለምትሰሩ የ 👉 Photoshop 👉 Illustrator course በስልክ ለምትሰሩ 👉 Pixelart 👉 Pixelab ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ፈጥናችሁ ተመዝገቡ #ለመመዝገብ Contact Us 0968470934 0927724114 0953315130 @Utopia_creative_official @Utopia_creative_official

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ያበሰራት ቅዱስ መላዕክ ማን ይባላል?

የ125 ብር ካርድ ሊለቀቅ ነው 9 ደቂቃ ብቻ ነው የቀራው።  ቶሎ ከስር JOIN ሚለውን ነክታቹ JOIN REQUEST ላኩ 🏃‍♀️🏃‍♂️

Repost from N/a
photo content

አሁንም ስራ እየፈለጋቹ ነው? ወይስ ተጨማሪ ገቢ ማግኘት ይፈልጋሉ? 🔥 Graphic Design አንድ ጊዜ የሚማሩት Skill፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢ ሊያስገኝልዎ የሚችል ሙያ ነው! 💰 Profes
አሁንም ስራ እየፈለጋቹ ነው? ወይስ ተጨማሪ ገቢ ማግኘት ይፈልጋሉ? 🔥 Graphic Design አንድ ጊዜ የሚማሩት Skill፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ገቢ ሊያስገኝልዎ የሚችል ሙያ ነው! 💰 Professional Graphic Designer 👉 30,000 – 70,000+ ብር / ወር 💻 Freelance Designer 👉 50,000 – 100,000+ ብር / ወር 🌍 International Freelancing 👉 100,000 – 250,000+ ብር / ወር የሚማሯቸው: ✅ Photoshop ✅ Illustrator ✅ Logo Design ✅ Social Media Design ✅ Poster & Banner Design ✅ Branding ✅ Freelancing #utopia_graphics ከታች 👇 ያለውን ቻናል አሁኑኑ join በማድረግ GRAPHIC DESIGN Skill ወደ ገቢ ይቀይሩ! 💰🎨 @Utopia_creative_official @Utopia_creative_official

2k member ያለው የቴሌግራም ግሩፕ መግዛት የምትፈልጉ አናግሩኝ @fikreabe

ጳጉሜ ማለት ምን ማለት ነው ❓ ጳጉሜ ወርን ለምን እንጾማለን ❓ ለምንስ እንጠመቃለን ❓        ጻጉሜ ሦስት ርኅወተ ሰማይ ነው፣ ሰባቱ ሰማያት ይከፈታሉ ጸሎታችን በሙሉ ያርጋል፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ አገራችን ዘመን አቆጣጠር የጳጉሜ 13ኛ ወር ተብላ ትቆጠራለች። ወርሃ ጳጉሜ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር  13ኛ ወር ተብላ ትቆጠር እንጂ በእለት ወይም በቀናት ብዛት ግን 30 ቀን ልትሞላ ቀርቶ ከአንድ ሳምንት እንኳን ያነሰ የቁጥር ብዛት የያዘች ወር ናት።  በ3ቱ ዘመናት ማለትም በዘመነ ማቴዎስ፣ በዘመነ ማርቆስ እና በዘመነ ሉቃስ መግቢያ ላይ 5 ቀን ስትሆን በዘመነ ዮሐንስ መጀመሪያ ላይ ማለትም በ4ቱ ዘመናት ውስጥ በ 1 ዘመን ብቻ 6 ቀን ሆና ትቆጠራለች። ✍ጳጉሜን ለምን እንጾማለን ? የጳጉሜ ወር በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ኃይማኖት የዓለም ፍጻሜ መታሰቢያ ወር ተደርጋ ትታሰባለች፣ ጳጉሜ የዓመታት መሸጋገሪያ፤ ጨለማው የክረምት ወቅት ወደ ማብቂያው እና የሚያልፍበት እንደ ሆነ ሁሉ ዳግም ምጽዓትም ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ፣ ከጊዜያው ወደ ዘላዓለማዊ መሻጋገሪያ ስለሆነ ነው ጳጉሜ የእለተ ምጽአት ምሳሌ የሆነችው፡፡ በዚህም ምክንያት የኦርቶዶክስ አማኞች የጳጉሜን ወር በሱባኤ፣ በጾም፣ በጸሎት ያሳልፋሉ በገዳም ያሉ አባቶች ጳጉሜን በዝግ ሱባኤ ያሳልፋሉ በእርግጥ ጳጉሜ ከሰባቱ አጽዋማት ውስጥ ባትካተትም፤ ጳጉሜን በግዴታ ሳይሆን በውዴታ ብንጾም የበረታን፣ ሱባኤ ብንይዝባት፣ የቻልን በተዐቅቦ ብናሳልፋት ትልቅ ጥቅም እናገኝበታለን። አንደኛ በፈቃዳችን በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት፣ በሱባኤ ብናሳልፍ ፀጋና በረከት ያሰጠናል፣ ሁለተኛው ጳጉሜ የአዲስ ዓመት መቀበያ የዋዜማ ቀናት በመሆኗ አዲሱን ዓመት በጾም፣ በጸሎት በሱባኤ ብንቀበል አዲሱ ዓመት የበረከት፣ የረድኤት ይሆንልናል ማለት ነው፡፡ አዲሱን ዓመት በተለይም በዋዜማው  በጸሎት ብንቀበል አዲሱ ዓመት የበረከት ዓመት፣ ያሰብነውን ያቀድነውን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሚሳካበት ይሆንልናል፣ የገዳም አባቶቻችን የጳጉሜን ወር መንፈሳዊ ጥቅም ስለሚያውቁ በፈቃዳቸው በታላቅ ሱባኤ ሆነው ስለ አገር፣ ስለ መጪው አዲስ ዓመት መልካምነት ፈጣሪን ይማጸኑበታል፣ እኛ የአባቶቻችን ልጆች ነንና እነሱ የሄዱበትን መንገድ ተከትለን እንደ እነሱ ልንጠቀም ያስፈልጋልና ወርሐ ጳጉሜን በጾም፣ በጸሎትና ፣ በሱባኤ ብናሳልፍ እንጠቀማለን፡፡ እግዚአብሔር እንዲታረቀን፣ ምሕረቱን እንዲመልስልን፣ ወረርሽኙን እንዲያጠፋልን፣ ለቅድስት ቤተ ክርስትያናችንና ለአገራችን  ሰላም እና አንድነት እንዲሰጥልን ወርሐ ጳጉሜን እንደ በፊቱ በመብላት በመጠጣት ሳይሆን በጾም በጸሎት ብናሳልፍ ጥቅሙ ለእኛው ነው፡፡ 👉ጳጉሜን ለምን እንጠመቃለን ? እንደሚታወቀው ብዙዎቻችን ወርኃ ጳጉሜን እንጠመቃለን፣ ጳጉሜን የምንጠመቅበት ዋናው ምክንያት ከሊቀ መልአኩ ከቅዱስ ሩፋኤል ጋር የተያያዘ ነው፣በዚህ በጳጉሜ ወር በዓለም ላይ ያሉ ውቅያኖሶች፣ ባህሮች፣ ወንዞች፣ ኩሬዎች ጸበሎች በአጠቃላይ ሰማይ ተከፍቶ ውኃዎች በመላክእት የሚባረኩበት ስለሆነ፣ ጳጉሜን የቻልን ጸበል ቦታ ሄደን፣ ወይም በአከባቢያችን ጸበል ካለ እዛም ሄደን፣ መሄድ ባይመቸን፣ ቤታችን ውስጥ ባለው ውኃ ብንጠመቅ እንባረክበታለን ከበሽታችንም እንድንበታለን፡፡ በጳጉሜ ጸበል፣ እንኳን የሰው በሽታ፤ በሽታ ያለው እህል፣ በሽታው ይለቀዋል፣ ገበሬው ከጳጉሜ ወዲያ ነው የሚጠፋውንና የማይጠፋውን እህል የሚለየው፣ በተለይም ጳጉሜ ሦስት፣ የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በአሉ ስለሆነ፣ በዚህ ቀን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ውኃችን የሚባርክበትና ለሰው ልጆች በፈጣሪው ፀጋ፣ ድኅነትና ፈውስ የሚያሰጥበት ቀን ስለሆነ ብንጠመቅ ከበሽታችን እንድናለን፡፡ በመፅሐፍ ቅዱስ በዮሐንስ ወንጌል በምዕራ 5 ቁጥር 4 ላይ "አንዳንድ ጊዜ የጌታ መልአክ ወደ መጠመቂያይቱ ወርዶ፣ ውኃውን ያናውጥ ነበርና፤ እንግዲህ ከውኃው መናወጥ በኃላ በመጀመሪያ የገባ ከማናቸውም ካለበት ደዌ ጤናማ ይሆን ነበር" ይላል፣ የጌታ መልአክ "ውኃውን ያናውጥ ነበር" የተባለው ከሰማይ ወርዶ ውኃውን ይባርከው ነበር ለማለት ነው፣ ውኃውም የሚናወጠው የእግዚአብሔር መልአክ ውኃውን ሲባርከውና እና በመጠመቂያው፣ ለፈውስ ደጅ የሚጠኑት፣ ህሙማን ውኃው በመልአኩ መባረኩን የሚያውቁት ውኃው ሲናወጥ ነው፡፡ ዛሬም ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል በዓለም ላይ ያሉትን ውሃዎች ሁሉ ስለሚባርካቸው፣ ብንጠመቅባቸው እንፈወሳለን፣ ቅዱስ ሩፋኤል ብቻ ሳይሆን ሌሎች ቅዱሳን መላእክትም ውኃውን ይባርኩታል ጳጉሜ ሦስት ይህ ብቻ አይደለም ሊቀ መልአኩ ያስለመደን ነገር አለ፣ ሁል ጊዜ ጳጉሜ ሦስት ሌሊት፣ ጠዋት፣ ከሰዓት ወይም ምሽት ላይ ይዘንባል፣ ይህ ከሰማይ የሆነ የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል ጸበል ነው፡፡ ጳጉሜ ሦስት በዘነበው ውኃ መጠመቅ ትልቅ መታደል እና ፈውስ ነው፣ በደዌ ይሰቃይ የነበረው ኢዮብም በዚህ ሳምንት ነው ተጠምቆ ነው የዳነው፡፡ የቅዱስ ሩፋኤል እለት የዘነው ዝናብ በዕቃ ይቀዳና ይቀመጣል፣ በተቀዳው ጸበል  በውኃው እህሉ ይቦካበታል፣ ቤቱ ደጁ ይረጭበታል፣ ይህም የሚሆነው የቅዱስ ሩፋኤል እለት የዘነበው ውኃ እርኩሳን መናፍስትን ስለሚያርቅ ነው፣ በጸበሉ በረከት እህሉን ያበረክትልናል፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ሦስተኛው ነው፣ በመጀመሪያዋ እለተ ፍጥረት እግዚአብሔር መቶ ነገደ መላእክት ፈጥሮ በአሥር ከተማ ሲያኖራቸው ቅዱስ ሩፋኤል ራማ ላይ ነው ከነ ሠራዊቱ ያረፈው፣ በራማም መናብርት ተብለው ለሚጠሩት አሥሩ ነገድ አለቃ ወይም መሪ ሆኖ በእግዚአብሔር ተሹሟል፣ በኋላም መጋብያን በሚባሉ በሃያ ሦስቱ ነገድ ላይ ተሹሟል፡፡ ስለዚህ ጳጉሜ ሦስት የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓሉ ነው፣ ይህንንም እራሱ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል በመጽሐፈ ጦቢት ምዕራፍ 12 ቁጥር 15 ላይ "ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ" በማለት ተናግሯል፣ የስሙንም ትርጉም ስንመለከት ሩፋኤል ማለት የእግዚአብሔር ሐኪም ማለት ነው፣ ቅዱስ ሩፋኤል "ፈታሔ ማህፀን" ስለሆነ እርጉዝ የሆኑ ሴቶችም ፀበሉን በመጠጣት፣ በሰላም ይገላገላሉ፣ በሰላም ይወልዳሉ ማለት ነው። 👉የጳጉሜ ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበትም  ወር ነው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዳግም ምጽአት እንዴት እንደሚመጣ፣ እንዴት እንደሚገለጥና እንዴት ፍርድ እንደሚሰጥ የሚጠበቀውን ቀንና የዘመን መጨረሻ ዳግም ምጽአቱ የሚነገርበት ሳምንት ስለሆነ ነው። በወርሃ ጳጉሜ እለታት በቤተክርስቲያን የሚዘመረው ዝማሬ የሚቀርበው ስብሃተ እግዚአብሔር ሁሉ ስለነገረ ምጽአቱ ይናገራል። ጳጉሜ የወሮቹ መጨሻ፣ የሚመጣው አዲስ ዘመን ዋዜማ እግዚአብሔርም በዚህ ዘመን ይመጣል ተብሎ ከሚነገርባቸው ቀናት እና ዘመናት ወርሃ ጳጉሜ አንዷ እንደሆነች ቅዱሳት መፅሐፍት እና የቤተክርስቲያናችን ሊቃውንት ያስተምራሉ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር    ወለወላዲቱ ድንግል       ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየ