ጸሎት የሁሉም ነገር ቁልፍ ነው።✝️🤲🙏🛐
Open in Telegram
ለመኖር ስትል ገብቶህ እንዳልገባህ የምታልፋችው ብዙ ነገሮች አሉ!! https://www.facebook.com/matmenge78?mibextid=ZbWKwL
Show more573
Subscribers
-224 hours
-87 days
-1230 days
Posts Archive
#ወር_በገባ_በ8_ፃድቁ_አባታችን_ቅዱስ_አቡነ_ኪሮስ_ናቸው ።
#በጨነቃቹ_በተከፋችሁ_ጊዜ_ቅዱስ_አቡነ_ኪሮስ_አለሁ_ይበላችሁ።
#ካልታሰበ_አደጋ_ወቶ_ከመቅረት_ይሰውሩን
#ወር_በገባ_በ7_አጋእዝተ_ዓለም_ቅድስት_ሥላሴ_ናቸው።
#ቅድስት_ሥላሴ_በዕለተ_ቀናቸው #ያላሰብነውን_ደስታ_ይስጡን፡፡🙏
#የአብርሃሙ_ሥላሴ_ወቶ_ከመቅረት_ከክፉ_ነገር_ሁሉር_ይሰውሩን
#በጨነቃችሁ_ጊዜ_ሁሉ_ፈጣሪያተ_ዓለም #ቅድስት_ሥላሴ_አለው_ይበሏችሁ።
https://t.me/Reading100T
ስብሐት ለ አብ
ስብሐት ለ ወልድ
ስብሐት ለ መንፈስ ቅዱስ
#አጋዕዝተ_ዓለም_ቅድስት_ሥላሴ_ለዓለም_አሜን።
"እግዚአብሔር ከእንቅልፉ እንደሚነቃ ተነሣ" (መዝ 78:65)
ውድ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም በጤና አደረሰን!!
"ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና (1ኛ ቆሮ 15፡21)
"ሰማያት (ሰማያውያን መላእክት) የደስታ በዓልን ያደርጋሉ፤ ደመናት (ቅዱሳን) የደስታን በዓል ያደርጋሉ፣ ምድር (ምድራውያን ሰዎችም) በክርስቶስ ደም ታጥባ (ታጥበው) የፋሲካን በዓል ታደርጋለች (ያደርጋሉ/ያከብራሉ /ታከብራለች)፡፡ ዛሬ በሰማያት (በሰማያውያን መላእክት) ዘንድ ታላቅ ደስታ ሆነ፤ ምድርም በክርስቶስ ደም ታጥባ የፋሲካን የነጻነት በዓል ታደርጋለች፡፡ የትንሣኤያችን በኲር ክርስቶስ ከሙታን ሁሉ ተለይቶ ቀድሞ ተነሣ፡፡" (ድጓ ዘፋሲካ)
ክርስቶስ ከዲያብሎስ ባርነት ነፃ አወጣን እኛም ራሳችንን ከዘመኑ የኅሊና ባርነት ነፃ እናውጣ!
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን!
በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን!
አሠሮ ለሰይጣን!
አግዐዞ ለአዳም!
ሰላም!
እምይእዜሰ!
ኮነ!
ፍሥሐ ወሰላም!
መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንልን!!!
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን #ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ_ለብርሃነ_ትንሣኤው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሉ ሉያ "#ይትፌሣሕ_ሰማይ_ወትትሐሠይ_ምድር ወይንፍሑ ቀርነ መሠረታተ ኅምዝ ወይወውዑ አድባር ወአውግር ወኵሉ ዕፀወ ገዳም ወዮምሰ ዐባይ ፍሥሓ በሰማያት #ወምድርኒ_ትገብር_ፋሲካ_ተሐጺባ_በደመ_ክርስቶስ። ትርጉም፦ ምድርና ሰማይ ይደሰቱ፣ ቀርነ መለከትም ይነፋ፤ ተራሮችና ኮረብቶችም የዱር ተክሎችም ይደሰቱ፤ ዛሬ በሰማያት ታላቅ ደስታ ሆነ፣ #ምድርም_በክርስቶስ_ደም_ታጥባለችና_ፋሲካ (ደስታን) ታደርግ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።
❤ #ትንሣኤ።
❤ ትንሣኤው የዓለም ድኅነት ሆነ በረቀቀ ጥበቡ ሠላሳ ሦስት ዓመት ያህል በምድር ላይ ሥራውን ሠርቶ በፈጸመ ጊዜ በፈቃዱ ሕማማተ መስቀል ተቀብሎ ሙቶ ከተቀበረ በኋላ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷልና።
❤ በዚች ዕለት ከሲኦል በመዳን ሙታንና ሕያውን ደስ አላቸው በዚች በጌታችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ መነሣት መነሣታቸውን አረጋገጡ የከበረ ቅዱስ ጳውሎስ በመነሣቱ ክርስቶስ የሙታን በኵር ሆነ እንዳለ እርሱ ለሙታን በኵራቸው ነውና። ለእርሱም ክብር ምስጋና ለዘላለሙ ይሁን አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 29 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃሕ እምንዋም። ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን። ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ"። መዝ 77፥65-66። የሚነበቡት ወንጌላት ማቴ 28፥1-ፍ.ም፣ ማር16፥1-ፍ.ም፣ ሉቃ 24፥1-13።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ቅዳሴ_ምስባክ፦ "ዛቲ ዕለት እንተ ገብረ እግዚአብሔር። ንትፈሣሕ ወንትሐሠይ ባቲ። ኦ እግዚኦ አድኅንሶ።" መዝ 117፥24-25 ። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 15፥20-41፣ 1ጴጥ 1፥1-13 እና የሐዋ ሥራ 2፥22-37። የሚነበው ወንጌል ዮሐ 20፥1-19። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የብርሃነ ትንሣኤ በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
#የሰሙነ_ሕማማት_አምስተኛ_ቀን_የሆነው_ዓርብ_በክርስትና_እምነት_ውስጥ_እጅግ_ታላቅና_መሠረታዊው_ዕለት_ነው።
ይህ ቀን የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጅ ድኅነት ሲል በመስቀል ላይ ተሰቅሎ የሞተበትና የሰው ልጅ ከኃጢአት ባርነት ነፃ የወጣበት ዕለት በመሆኑ ስቅለተ ዓለም በመባል ይታወቃል። ዕለቱ የሚከተሉት ስያሜዎችና ጥልቅ ትርጓሜዎች አሉት፡-
አርብ ስቅለተ ዓለም ይባላል
ይህ ስያሜ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳም ዘር ሁሉ ሲል በቀራንዮ አደባባይ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ መሞቱን ያመለክታል። ዓለም ሁሉ በኃጢአት ምክንያት ከፈጣሪው ተለይቶ በሞት ጥላ ሥር በነበረበት ጊዜ፣ ጌታ በመስቀል ላይ በከፈለው መሥዋዕትነት የዓለምን በደል የደመሰሰበት ዕለት በመሆኑ ስቅለተ ዓለም ይባላል።
ሌላው አርብ የነፃነት ዓርብ ይባላል
በዚህ ዕለት የሰው ልጅ ለዘመናት ተጭኖት ከነበረው የዲያብሎስ የባርነት ቀንበር ነፃ ወጥቷል። ጌታችን በመስቀል ላይ ሳለ "ተፈጸመ" (ተፈጸመ ማለቱ የሰው ልጅ የመዳን ሥራ ተጠናቀቀ ማለት ነው) ብሎ ነፍሱን አሳልፎ በሰጠ ጊዜ፣ በሞቱ ሞትን ድል አድርጎ የልጅነት ክብራችንን ስለመለሰልን ዕለቱ የነፃነት ዓርብ ይባላል።
ነቢዩ ኢሳይያስ "በእርሱ ቁስል እኛ ዳንን" ብሎ እንደተነበየው፣ በዚህች ዕለት ጌታችን ስለ እኛ ቆስሎ፣ ተገርፎና ተንቆ እኛን ካለንበት የውርደት ሕይወት አውጥቶናል። በመስቀል ላይ የፈሰሰው ቅዱስ ደሙ ከኃጢአት ሁሉ የሚያነጻና ሕይወትን የሚሰጥ በመሆኑ፣ ዓርብ ለሰው ልጅ ሁሉ የድኅነት (የመዳን) ምንጭ የሆነበት ዕለት ነው።
ምንም እንኳን መስቀል በጥንት ዘመን የውርደትና የቅጣት ምልክት ቢሆንም፣ ጌታችን ግን በከበረ ደሙ ቀድሶ የድልና የክብር ምልክት አድርጎታል። ስለዚህ በዚህ ዕለት ክርስቲያኖች በመስቀሉ የተገኘውን ሰላምና እርቅ እያሰቡ መስቀሉን እንደ ድል አርማ ያከብሩታል።
መልካሙ ዓርብ (Good Friday) በመባልም ይታወቃል
ይህ ስያሜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅ ሲሆን፣ ምንም እንኳን ዕለቱ የጌታ ሕማምና ሞት የሚታሰብበት ቢሆንም፣ ውጤቱ ግን ለሰው ልጅ "መልካም" የሆነውን ዘላለማዊ ሕይወትና ይቅርታን ያስገኘ በመሆኑ መልካሙ ዓርብ ይባላል።
በአጠቃላይ ዕለተ ዓርብ ፍጹም መለኮታዊ ፍቅር የተገለጠበት ቀን ነው። ጌታችን በፈቃዱ ለሞት መሰጠቱ እኛን ምን ያህል እንደሚወደን ያሳየበት ነው። በዚህ ዕለት ምእመናን ከጠዋት እስከ ማታ በቤተክርስቲያን በመገኘት ስቅለቱን፣ ሰባቱን የጌታ ቃላት፣ በግርፋቱና በመስቀል ላይ የተቀበላቸውን መከራዎች እያሰቡ በታላቅ ስግደትና ጾም ያሳልፉታል። ይህ ዕለት የጥል ግድግዳ ፈርሶ ከእግዚአብሔር ጋር የታረቅንበት ታላቅ የሠላም ቀን ነው።
" #በዕለተ_ዓርብ_ጠዋት_ሦስት_ሰዓት_ጌታ_ተገረፈ" ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪታይ ድረስ 6666 ጊዜ ገረፉት።
ጲላጦስም ጌታን መርምሮ አንዳችም ለሞት የሚያበቃ በደል አላገኘበትም። እሱም ሊፈታው ፈለገ ህዝቡ ግን “ስቀለው ስቀለው” እያሉ አብዝተው ጮሁ።
ጲላጦስም ምናልባት ቢገረፍ እሱ ይበቃዋል ብለው ይገደል የሚለውን ጥያቄያቸው ይተዋሉ ብሎ በማሰብ ለመገረፍ አሳልፎ ሰጠው። በልማዳቸው የተገረፈ አይሰቀልም እና። እነርሱ ግን ልባቸው በጭካኔ የደነደነ ነበር እና እየተፈራረቁ ክንዳቸው እስኪዝል ድረስ አርባ ብቻ ሊገረፍ የተፈረደበትን ቁጥር ያሳሳቱ በማስመሰል ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪታይ ድረስ ስድስት ሺህ ስድሥት መቶ ስልሳ ስድስት (፮፼፮፻፷፮)(6666) ጊዜ ገረፉት።
ጌታ እንዲሰቀል የህዝቡ ጩኸት በበረታ ጊዜም ጲላጦስ ከዘመኑ ንጉስ ከቄሳር ጋር እንዳያጣሉት ለሥልጣኑ በመስጋት እኔ ከደሙ ንጹህ ነኝ ብሎ በውሃ እጁን ታጠበና ጌታን እንዲሰቅሉት አሳልፎ ሰጣቸው።(ማቴ ፳፯፡፳፬-፳፮ ፤ ማር ፲፭፡፮-፲፭ ፤ ሉቃ ፳፫፡፩-፳፮ ፤ ዮሐ ፲፰፡፳፰-፴፰)።
#በዚች_ሌሊት_ዓለም_ተኝታለች
አንተ ግን ስለ እኔ በደም ላብ እየተጠመቅህ ትጨነቃለህ። እኔ ግን ዛሬም እንደ ደቀመዛሙርቱ "አንዲት ሰዓት እንኳ" ካንተ ጋር መትጋት አቅቶኝ በቸልተኝነት እንቅልፍ ተኝቻለሁ።
#ስለ_እኔ_ስግብግብነት
ኦ ጌታ ሆይ ይሁዳ ሠላሳ ብር በእጁ ይዞ አንተን አሳልፎ ሰጠ፤ እኔ ግን የይሁዳን ሠላሳ ብር በልቤ ውስጥ ደብቄያታለሁ።
ያቺ ሠላሳ ብር የእኔ ክፉ ምኞት ናት።
ያቺ ሠላሳ ብር የእኔ ጥላቻና ቂም ናት።
ያቺ ሠላሳ ብር ካንተ ይልቅ ያስቀደምኳቸው የዚህ ዓለም ጣጣዎች ናቸው።
ይሁዳ አንተን የሸጠው ለአንድ ሌሊት ጥቅም ነው፤ እኔ ግን ለዘላለም የምትሆነኝን አንተን፣ ለጥቂት ደቂቃ ስሜት ስል አሳልፌ ሰጠሁህ። እርሱ በመሳም ካደህ፤ እኔም "ጌታ ሆይ እወድሃለሁ" እያልኩ በድርጊቴ ግን ቸንክሬሃለሁ።
#የነፍሴ_ስብራት_ጌታ_ሆይ
ዛሬ ራሴን አይቼው ተሰበርኩ። በአንደበቴ ቅዱስ፣ በልቤ ግን ይሁዳ ነኝ። አንተ ግን ዛሬም ድረስ "ወዳጄ ሆይ" እያልክ ትጠራኛለህ። ዛሬ ትሕትናን ልታስተምረኝ ዝቅ ብለህ የደቀመዛሙርትህን እግር አጠብክ። እባክህ ጌታ ሆይ! እግሬን ብቻ ሳይሆን በክፋት የቆሸሸውን ኅሊናዬን እጠበው። በእኔ ውስጥ ያለውን "ይሁዳዊ" ማንነት ዛሬ በዛ በፈሰሰው ደምህ እጠብልኝ ።
#አምላኬ_ሆይ
ለይሁዳ የተሰጠው ሠላሳ ብር መጨረሻው ሞትና ስቅላት ሆነ። እኔም በኃጢአቴ የምሰበስበው "ትርፍ" ሁሉ መጨረሻው ጥፋት ነው።
እባክህ ካንተ ውጪ ያለኝን ሀብት ሁሉ አሳጣኝ፤ ካንተ ውጪ ያለኝን ክብር ሁሉ አርክስብኝ። አንተን ብቻ እንዳገኝ፣ ካንተ ጋር ብቻ በማዕድ እንድቀመጥ አድርገኝ።
በዚች ሌሊት ከጎንህ እንድቆም፣ በስቃይህ እንድካፈል፣ በሞትህ ውስጥ እኔም ለኃጢአቴ እንድሞት ጸጋህን ስጠኝ። ልቤ ተሰብሯልና አትናቀኝ፤ ነፍሴ ተጨንቃለችና አጽናናኝ።
#ልደታ_ማሪያም
#በዕለተ_ቀኗ_ከክፉ_ሁሉ_ትሰውረን_ረድኤት_በረከቷ_አይለየን።
#በጨነቃችሁ_ጊዜ_ሁሉ_እናቴ_ልደታ_ለማርያም_አለው_ትበላችሁ።
☞ #ተፈጸመ_ወርኀ_መጋቢት_ቡሩክ_በሰላመ_እግዚአብሔር_ስቡሕ_ወውዱስ_አሜን።
#ወአመ ፴፦
✝ #በዛቲ_ዕለት፦ ገብረ እግዚአብሔር ጠፈረ፥ ከመ ያብርሁ ቦቱ ብርሃናት (ወዓዲ ከፈሎ ለማይ ለኀበ ሠለስቱ)
✝ሰሙነ ሕማማት ቅድስት፥ ዘእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኀኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ዘሎቱ ስብሐት ወአኮቴት
✝ቅድስት ጾመ ድኅነት (እስመ በዛቲ ዕለት አኅለቁ ምክረ አይሁድ፥ ከመ ይስቅልዎ ለመድኅን)
✝ተዝካረ በዓሉ ለቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያ፥ ወንጌላዊ ወሰማዕት
✝ወተዝካረ በዓሎሙ ለቅዱሳን፦ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት፥ ወአባ ሣሉሲ ክቡር፥ ወማር ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት፥ ኦርኒ ንጽሕት፥ ወጤቀላ ድንግል፥ አንስት ንጹሐት ጲስጢስ፡ አላጲስ፡ ወአጋጲስ፥ ወቅድስት ሶፍያ እሞን፥ ወጻድቃን ዘዴጎ
❖ #ወበዓለ_ቅዱሳን_አበው፦
✝ዐቢይ ወክቡር መልአክ፥ ገብርኤል ሊቅ፥ ሊቀ መላእክት፥ ሰባኬ ዜና ሐዲስ፥ ወፍሡሐ ገጽ፥ ርዕሰ አርባብ፥ ዘደለዎ ከመ ይጹር ዜና ሥጋዌሁ ለወልደ እግዚአብሔር (ወዘአብሠራ ለእግዝእትነ ማርያም)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወነቢይ፥ ሶምሶን ኃያል ረዓይታዊ፥ መስፍኖሙ ለእስራኤል፥ ዘቀተሎሙ ለኢሎፍሊ በመንሰከ አድግ (ወዘኮነኖሙ ለ፳ኤል ፳ ዓመተ)
✝ክቡራን ጻድቃን፥ ማኑሄ ወእንትኩይ፥ ዘእምነገደ ዳን (ወላድያኒሁ)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ኃያል ወመስተጋድል፥ ጻድቅ ወሰማዕት፥ ያዕቆብ ዘግሙድ፥ ዘፈጸመ ገድሎ በምድረ ፋርስ (ፍልሠተ ሥጋሁ)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ፥ ወመተርጉመ መጻሕፍት፥ አባ ዮሐንስ መምህር፥ ወኤጲስ ቆጶስ ዘአክሱም (ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን)
°ቅድስት መካኑ አክሱም፥ ወቅዱሳን ውሉዱ
❖ #ወስብሐት_ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡
#ወር_በገባ_በ29_የበዓል_ሁሉ_ራስ_የሆነው_በዓለ_ወልድ #በዓለ_እግዚአብሔር_ነው።
#በጨነቃችሁ_ጊዜ_ሁሉ_ቅዱስ_በዓለ_ወልድ_አለሁ_ይበላችሁ።
#ቅዱስ_በዓለ_ወልድ_ከክፉ_ሁሉ_ይጠብቀን_ወቶ_ከመቅረት_ይሰውረን።
#ወር_በገባ_በ28_አባታችን_ቅዱስ_አማኑኤል_ነው ።
#በጨነቃችሁ_በችግራችሁ_ጊዜ_ሁሉ_ቅዱስ_አማኑኤል_አለሁ_ይበላችሁ።
#ወቶ_ከመቅረት_ካልታሰበ_አደጋ_ከክፉ_ነገር_ሁሉ_ይሰውረን።
" #በህይወቴ_ትልቁን_ገጠመኝ_ልንገራችሁ"
ጊዜው ከሁለት ዓመት በፊት ነበር።በቃል ከምገልጸው በላይ በጣም ቸግሮኝ ነበር።ትንሽ ብር እንዲያበድሩኝ ከቴሌ የድምጽ ጥቅል ተበድሬ አንድ አንድ የምቀርባቸው ወዳጆቼ ጋር ስልክ ደወልኩኝ.............አልተሳካም 😔
አስታውሳለሁ የባንክ አካውንቴ ላይ 15.04 ብር እና እጄ ላይ ያልተዘረዘረ ድፍን 100 ብር ብቻ ነበረኝ። እንደ ማጣት ከፉ ነገር ግን አለ? በጣም ስለከፋኝ አቅራቢያዬ ወደሚገኘው 6ኪሎ ቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስቲያን ግቢ ገባሁና ግቢ ውስጥ ባለው አንድ አግዳሚ ወንበር ላይ ቁጭ ብዬ የውስጤን ለእግዚአብሔር መንገር ጀመርኩ.......
ጸሎቴን አድርሼ እንደጨረስኩኝ አንድ ጠቆር ያለ ሰው፥የተለያዩ መድኃኒቶችን አጉልቶ በሚያሳይ ስስ ፔይስታል ይዞ እየተረመደ ወደ እኔ መጣ፤ልክ እንደደረሰ "ወንድሜ እናቴ ታማ ልትሞትብኝ ነውና መድኃኒት ልገዛ መጥቼ አሥር ብር ብቻ ጎደለኝ፥እባክህ ሙላልኝ።"አለኝ።፥ሰውዬው ተናግሮ ሳይጨርስ ብዙ ገንዘብ እንደያዘ ሰው አራቱንም ኪሶቼን(ሁለት የሱሪና ሁለት የጃኬት) በአንዴ መፈተሽ ጀመርኩ🤣
በአራተኛው ተሳክቶልኝ ያቺን የተጨማደደችና አንድ ለእናቱ የሆነች መቶ ብር ወጣ አደረኳትና "ያለችኝ አንድ መቶ ብር ብቻ ናት እንዴት ላድርግ?"አልኩት።አንድ አንድ ሰዎችን ዝርዝር እንዳላቸወ ጠየቅን።ነገር ግን አጣን.....
"በቃ ቤተክርስቲያኑ በር ላይ ያለው ሱቅ ሄጄ ዘርዝሬው ልምጣ እዚሁ ቆየኝ፥አለና 100 ብሩን ይዞት ሄደ።እስከ ሠላሳ ደቂቃ ድረስ ዝርዝር አጥቶ ይሆናል፥አሁን ተመልሶ ይመጣል፥እያልኩ በተስፋ ጠበኩኝ....አልመጣም...አንድ ሰዓት ሞላው..ወፍ የለም 😔
እውነት ለመናገር ከሆነ በሰውዬው አንዳች አልተናደድኩበትም።እኔ ግን ምን ዓይነት ዕድል ነው ያለኝ? ብዬ በጣም አለቀስኩ።በልቅሶዬ መኃል ቤተክርስቲያኑ በር ላይ አንድ የንዋየ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ አሻግሬ ተመለከትኩ።አንድ ክፉ ሀሳብ ወደ አዕምሮዬ ዘልቆ ገባ። ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ስመረቅ ብዙ የስዕለ አድህኖ ሥጦታ ተሰጥቶኝ ስለነበር፥ለምን አልሸጣቸውም፥ካለሁበት ችግር አይብስም እኮ።አልኩና ወደ ሱቁ አመራሁ....
ልክ እንደደረስኩኝ አንድ ደርባባ እናት በፈገግታ ተቀበለችኝ።በውስጤ ፍርሃት እየተሰማኝ "እናቴ ስዕል ትገዢያለሽ እንዴ?" ብዬ ጠየኳት።"የተሰረቀ ከሆነ አልገዛም አለችኝ።"አረ የተሰረቀ አይደለም ።በጣም ስለቸገረኝና ገንዘብ ስለሚያስፈልገኝ ነው አልኳት።እንደዚያ ከሆነ ይዘሃቸው ና እገዛሃለሁ።አለችኝ።
በሩጫ ወደ ቤቴ ሄድኩና ተሸክሜ ወደ ሱቁ መጣሁ።ሴትየዋ ስዕለ አድኅኖዎቹን አዩና በዘመኑ በገበያ ላይ ከ1300ብር እስከ 1500ብር የሚሸጡ ስዕለ አድህኖዎችን በሁለት ሁለት መቶ ብር ገመተችልኝ🙁 በጣም ተናደድኩ....ቸገረኝ ስላልኩሽ ነው አይደል አልኳትና፥ተሸክሜ ወደ ቤቴ ጉዞ ጀመርኩ።
በጉዞ ላይ እያለሁ፥በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ቆይታዬ የማውቃቸውና ካናዳ ሀገር እህታቸው ጋር ሄደው በዚያው የቀሩ አባ ወልደ ሩፋኤል የተባሉ አባት አስፓልት ዳር ከሆነ ሰው ጋር ተቃቅፈው ሠላም ሲባባሉ አየኋቸው።በጣም ደስ አለኝ፥ጠጋ ብዬ አባዬ አልኳቸው።አቅፈው ሠላም አሉኝና በመስቀል ባረኩኝ.....😃ሠላምታ ከተለዋወጥን በኋላ የተሸከምከውን ቶሎ ቤት አድርሰህ ና! በጣም እፈልገሃለሁ እንዳትቆይ የሚል አጭር ትዕዛዝ ሰጡኝና ስልካቸውን ተቀብዬ ተለያዬን.......
በፍጥነት ቤት ገብቼ ስዕለ አድኅኖውን አስቀምጬ፥በሩጫ አባ ወዳሉበት ሄድኩኝ፥"ምነው ቆየህ? አሉኝ።የታክሲ አጥቼ ነው ላለማለት ታክሲ አጥቼ ነው አልኳቸው።ምሳ ጋበዙኝ፥እውነቱን ለመናገር በጣም ርቦኝ ስለነበር የቀረበልኝን ማዕድ ለመጨረስ÷ከሁለት ጉርሻ በላይ አልጎረስኩም ነበር።አባ ምን ይጨመር አሉኝ....እያመነታሁ ኧ.ኧ. ጠግቢያለሁ አባታችን አልኳቸው።አባ ቀጡሉ፥"ካስዬ ስላገኘሁ በጣም ደስ ብሎኛል፥ታስታውሳለህ አንድ ጊዜ ዕቃ ለመግዛት ብር ጎድሎኝ 1500 ብር አበድረኅኝ፥አልመለስኩልህም ነበር......?አሉኝ
በእውነቱ ትዝ አላለኝም ነበር።ቦታውን ከነምልክቱ ነገሩኝ፥እውነትም አበድሬያቸው እንደነበር አስታውሼ ነገርኳቸው።"ብዙ ጊዜ ስልክህ ጠፍቶብኝ ስፈልግህ ነው የኖርኩት።"አሉና ጠረጴዛ ላይ ያስቀመጧትን ትንሽዬ ሌዘር ቦርሳ ከፍተው ሁለት የገንዘብ ኖቶችን ጠቅልለው ሰጡኝ።ሳየው 150$ ነበር።ፈገግ አሉና "አይዞህ ከአንተ 1500 ብር የኔ 150$ ይበልጣል።"አሉኝና ተሳስቀን አመስግኜያቸው ተለያየን....🙏
#ወዳጆቼ፦ያለንበት ዓለም የፈተና ዓለም ናት።
እናገኛለን፣አናጣለን
እንደሰታለን፣እናዝናለን
እንስቃለን፣እናለቅሳለን
ሰበሰብን ስንል፥ይበተናል
ቋጥረናል ስንል፥ይፈታል.....መውደቅ፥መነሳት፥ ብቻ ምን አለፋችሁ ቋሚ ነገር በውስጧ የለባትም።
እግዚአብሔር ግን መልካም ነው።ፈተና በዝቶብን ስንቅበዘበዝ እርሱ ወዳጃችን በራሱ መንገድ ሊደግፈን ወደእኛ ይመጣል፤ያሳርፋል፥ከጭንቀት ይገላግላል፥በፈተና ብዛት የዛለውን ሰውነት ያበረታል።
#አረ_ማን_እንደ_እግዚአብሔር?
ፈተናው፣ወጀቡና ማዕበሉ በበዛ ቁጥር ወደርሱ እንቅረብ፥ባደረግነው በጎነት ወደ ኋላ ተመልሰን አንጸጸት....ያንጊዜ ኤልሻዳይ(ሁሉን ቻይ) የሆነው እርሱ ይመጣና ከደስታ ብዛት የተነሳ የነበርንበትን ፈተና ያስረሳናል።ታሪክ ያደርገዋል የኛ ጌታ😘
◈ክብር፣ምስጋና፣አምልኮና ውዳሴ ለገናናው ሥሙ ይሁን🙏
"በዓለም ሳላችሁ ፈተና አለባችሁ፥ነገር ግን አይዞአችሁ፥እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁና። ዮሐ 16÷33
መ/ካሳሁን ቶ
የዓለም ትክክለኛ መልክዋ ይኼ ነው። <ሆሳዕና> ተብሎ ሲዘመር ሁሉም መዝሙሩን ተቀብሎ ይዘምራል፤ አላፊ አግዳሚው ይጋፍል፣ መሬት መርገጥ አይገባህም ብሎ ልብሱን እስከ ማንጠፍ ይደርሳል።
በተሰደብክበትና በተዋረድክበት ጊዜ ደግሞ ሁሉም ሊሰድብህ ይሻማል ፤ልትረግጠው አይገባህም ብሎ ባነጠፈልህ መሬት ላይ አንተን አንጥፎ ይረግጥሃል፣ ክሱን እንኳን ሳያጣራ <ይሰቀል ይሰቀል> ብሎ ይጮኸል፤ መንገድ አላፊው ሳይቀር በመሳደብ ይተባበራል ዓለም ንፅህናንና እውነተኝነትን ብትወድ ኖሮ ከመድኀኒ ዓለም በላይ ንፅሕና እውነተኛ የለም።
📕 #ህመማት@Reading100T #ህመማት
#ነገ_እኮ_በ27_የአለም_በዛ_መድኀኔዓለም_ነው።
#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን።
#በሕይወታችን_የጎደለውን_ኹሉ_የዓለሙ_ቤዛ
#ቸሩ_መድኃኔዓለም_ይሙላልን።
የወደቀ የሚያነሳ የፈጠረውን የማይረሳ የደክመን የሚያበረታ የታመመን የሚፈውስ ያዘነን የሚያጽናና የተከፋን የሚያስደስት የተስበራን የሚጠግ የዘላለም አባት ልኡል
እግዚአብሔር ስሙ ለዘለዓለም እስከ ዘላለሙ የተመሰገነ ይሁን አሜን።
#በጨነቃቹ_በተከፋችሁ_ጊዜ_ቸሩ_መድኃኔዓለም_አለሁ_ይበላችሁ።
#ወር_በገባ_በ26_ፃድቁ_አባታችን_አቡነ_ሃብተ_ማርያም_ናቸው።
#አቡነ_ሃብተ_ማርያምወቶ_ከመቅረት_ካልታሰበ_አሰጋ_ይሰውሩን።
https://t.me/Reading100T
#በጨነቃችሁ_ጊዜ_አቡነ_ሃብተ_ማርያም_አባቴ_አለው_ይበላችሁ።🥰🙏🥰
#ወር_በገባ_በ25_ሰማዕቱ_ቅዱስ_መርቆሬዎስ_ነው።
#መርቆሪዎስ_ማለት_የአብ_ወዳጅ_የወልድ_አገልጋይ_ማለት1ነዉ።
ቅዱስ መርቆሬዎስ ሆይ እግረ ልቦናዬ በፊትህ በቆመ ጊዜ በነጋ በነጋ ጎብኘኝ ሰላምንም ስጠኝ።
ወቶ ከመቅረት ካልታሰበ አደጋ ከክፉ ነገር ሁሉ ይሰውረን።አሜን በእውነት
