386
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+530 days
Posts Archive
ለማስታዎስ
ለ6ኛ እና ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ሰኞ በ22/2016ዓ.ምየሚጀምር መሆኑን እያስታወስን በቆይታችሁ በቀጣይ ለክልል ና ከተማ አቀፍ ፈተና የሚያዘጋጁ ርእሶች ተመርጠው የምትማሩ ሲሆን በውስጡም ፈተናዎች፣ መለማመጃ ጥያቄዎች እና ድንገቴ ፈተናዎች የሚሰጧችሁ ይሆናል🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ማሳሰቢያ
ትምህርቱ የሚሰጠው
ከሀምሌ 22/2016 ዓም እስከ ነሀሴ 23/2016ዓ.ነው
ሰዓት =2:00-6:10 ሰዓት
ደብተር= አራት ባለ 32 ሉክ
ለሰዋስው አካዳሚ ወላጆች በሙሉ
ለምዝገባ ስትመጡ የመጽሐፍት ክፍያንም ጭምር እንድትከፍሉ እያሳሰብን በ2017ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምንም አይነት ተማሪ ያለመጽሐፍ ትምህርት ቤት መምጣት የማይችል መሆኑን ቀድመን በጥብቅ እናሳስባለን ።
ት/ቤቱ
ማስታዎሻ
ለ6ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች በሙሉ
ውጤት ስለመጣ ሰኞ ሃምሌ 15/2016 ዓ.ም ልጆቻችሁን እንድታስመዘግቡ እናሳስባለን፡፡
ለሰዋስው አካዳሚ ማህበረሰብ በሙሉ
እንኳን ደስ አላችሁ !!!
በተስፋ ሰጪ የለውጥ ሂደት ላይ የሚገኘው አካዳሚያችን ለመጀመሪያ ጊዜ በ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ያስፈተናቸውን ተማሪዎች በከፍተኛ ውጤት ወደ 7ኛ ክፍል ማለፋቸውን እናበስራለን !
ውድ የተከበራችሁ የ6ኛ ክፍል ወላጆች እና ተማሪዎች
እባክዎን ውጤትዎን በሚከተለው ሊንክ ያረጋግጡ።
⏹6ኛ ክፍል አገናኝ፡
https://aa6.ministry.et/#/ውጤት
እንዴት ማድረግ እንደሚቻል፧
ወደ ተዘጋጀው ጣቢያ ይሂዱ እና በመጀመሪያው ክፍል ውስጥ የመመዝገቢያ ቁጥርዎን እና በሁለተኛው ክፍል ውስጥ የመጀመሪያ ስምዎን ያስገቡ, ውጤቱ እዚያ መታየት አለበት.
ከሰላምታ ጋር
ትምህርት ቤቱ
ለውድ ወላጆች
ለነባር ተማሪዎች በሙሉ
የተማሪ ምዝገባ መረጃ ስለመስጠት
የተማሪ ምዝገባ መንግስት በሰጠው የምዝገባ ቀን መሠረት ከሰኔ 28/2016ዓ.ም እስከ ሐምሌ 15/2016ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል በዚህም በርካታ ወላጆች ልጆቻቸውን ያስመዘገቡ ሲሆን ነገር ግን እስከ ዛሬው እለት(13/11/2916ዓ.ም)ድረስ ልጆቻችሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች እንዳላችሁ ምዝገባ ኮሚቴው አሳውቋል ። በመሆኑም የሚፈጠረውን አላስፈላጊ መጨናነቅ ለመቅረፍ ቅዳሜ ሐምሌ13እና ሰኞ ሃምሌ 15/2016ዓ.ም ከ2:00-11:00 ሰዓት ድረስ እንድትመዘገቡ በጥብቅ እናሳስባለን ።
ማስታዎሻ
6ኛ ክፍሎች ውጤት እንደመጣ ምዝገባ ስለሚካሄድ ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ
የ6ኛ እናየ8ኛ ክፍል የክረምት ትምህርት ሃምሌ 22/2016ዓ.ም ስለሚጀምር ቅድመዝግጅት እንድታደርጉ ።ክፍያ 1000ብር።ለነባር እና ለአዲስ ተማሪዎች
0905658865
ለ6ኛ እና ለ8ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች በሙሉ
የክረምት ትምህርት የሚጀምርበትን ቀን ስለማሳወቅ
ለነባር እና አዲስ ተማሪዎች
ውድ ወላጆች 6ኛእና8ኛ የክረምት ትምህርት ከሐምሌ 22/2016ዓ.ም እስከ ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም ለአንድ ወር የሚቆይ ትምህርት ይሰጣል።
በመሆኑም ተማሪዎቻችን የ2017 ዓ.ም ዘመን ሚኒስትሪ ተፈታኝ በመሆናቸው በዋና ዋና ትምህርቶች ማለትም
ሒሳብ
እንግሊዝኛ
ሳይንስ
አማርኛ
ማህበራዊ ሳይንስ
ሲትዝን ሽፕ
የሚማሩ ሲሆን ውድ ወላጆች አስፈላጊውን ዝግጀት እንድታደርጉ ከወዲሁ እናሳውቃለን
ማስታወሻ
ትምህርቱ የሚሰጠው
ከሰኞ እስከ አርብ
ጠዋት ከ2:30 - 6:00
ክፍያ =1000ብር
የ2017 ዓ.ም ነባር ተማሪ ምዝገባ አርብ 12/11/2016የመጨረሻው ቀን በመሆኑ
ልጆቻችሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች እንድታስመዘግቡ እናሳስባለን ።
