Enterprenuership Development Institute (EDI)-Ethiopia
Open in Telegram
Website: edi-ethiopia.org Email: info@edi-ethiopia.com LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/entrepreneurship-development-centre/ Facebook: https://www.facebook.com/ediethiopia22?mibextid=ZbWKwL Location: Joseph Tito Street Nega city Mall 3rd floor
Show more410
Subscribers
+4224 hours
+3417 days
+1 28230 days
Posts Archive
"የኢንተርፕሪነርሺፕ ስነ-ምህዳሩ በተፈለገው መጠን እንዳይሰፋ የሚያግዱ የተዘጉ በሮችን ለማስከፈት የሚመለከታቸውን አካላት ንቁ ተሳትፎ ይጠይቃል፡፡"
ክቡር አቶ ንጉሡ ጥላሁን
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ
የኢንተርኘሪነርሽኘ ልማት ኢኒስቲትዮሽን እና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ‹‹ለኢንተርፕርፕሪነሮች ክፍት ይሁኑ በሮች›› በሚል መሪ ሃሳብ የዓለም አቀፍ የኢንተርፕሪነርሺፕ ሳምንትን በተለያዩ ዝግጅቶች ከህዳር 24/2016 ዓ.ም ጀምሮ እያከበሩ ይገኛል፡፡
የሣምንቱ አካል የሆነው የፓናል ውይይት ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ሥምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ንጉሡ ጥላሁን እንደገለፁት፤ የኢንተርፕሪነርሺፕ ምህዳሩ በተፈለገው መጠን እንዳይሰፋ የሚያግዱ የተዘጉ በሮችን ለማስከፈት የሚመለከታቸውን አካላት ንቁ ተሳትፎ ይጠይቃል፡፡
በቅርቡ እንደሚፀድቅ የሚጠበቀውን የስታርት አኘ አዋጅን ጨምሮ ለፈጠራና ኢኖቬሽን መንግስት እየተሰጠው ትኩረት ኢትዮጵያን በቀጣዮቹ ዓመታት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢንተርፕሪነሮች የሚፈሩባት ሀገር ከማድረግ አንፃር ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡
የኢንተርፕሪነርሺፕ ልማት ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሃሰን ሁሴን በሀገራችን የኢንትርፕነርሺፕ ሥነ ምህዳርን ለማስፋት ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን አስታውሰው በቀጣይም የፋይናንስ ድጋፍን ፣ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ፣ የትምህርት ጥራትንና የወጣቶች ክህሎትን በማሳደግ ለኢንተርፕሪነሮች በሮችን ክፍት ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡
ከግሉ ዘርፍ የተወጣጡ አካላት ተሳታፊ በሆኑበት የፓናል ውይይት በአገራችን የኢንተርፕሪነርሽፕ ልማትን ለማስፋት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት በሚያስችሉ የመፍትሔ አማራጮች ላይ ሰፊ ውይይት አካሄደዋል፡፡
....
የኢትዮጵያ ኢንተርፕረነርሺፕ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሃሳን ሁሴን በበኩላቸው ከዚህ ቀደም ዘርፉ ትኩረት የተነፈገው እንደነበር አስታውሰው በአሁን ወቅት በተለይ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መመራት ከጀመረ በኋላ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተደገፈ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡
በመድረኩ በግል ሥራ ፈጠራ ተሰማርተው ሥኬታማ የሆኑ ኢንተርፕረነሮች ልምድና ተሞክሮአቸውን ያጋሩ ሲሆን በተለይ በጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች ደረጃ የሚያጋጥሙ ችግሮች እና መፍቴሄዎቻቸው ላይ ያተኮረ ምክረ ሃሳብ ሰጥተዋል፡፡
በግል ሥራ ስኬታማ የሆኑ ሥራ ፈጣሪ ኢንተርፕረነሮች ልምድና ተሞክሮአቸውን ያካፈሉበት መድረክ ተካሄደ፡፡
ዓለም አቀፍ የኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት ለኢንተርፕረነሮች ክፍት ይሁኑ በሮች በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ በያዝነው የህዳር ወር ይገኛል፡፡
የሳምንቱ ፕሮግራም አካል የሆነው በኢትዮጵያ በግል ሥራ ስኬታማ የሆኑ ሥራ ፈጣሪ ኢንተርፕሪነሮች እና ጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች የተሳተፉበት የልምድ ልውውጥ እና የምክክር መድረክ ተካሂዷል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ንጉሡ ጥላሁን፤ ኢንተርፕሪነሮች የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች ለመፍታት እና ሥነ ምህዳሩ ለኢንተርፕረነርሺፕ የተመቸ ለማድረግ ከህዳር እስከ ህዳር የተለያዩ ሥራዎች እየተሰሩ ቢቆይም ሳምንቱ ግን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከበረወን የኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት አስመልክቶ በልዩ ሁኔታ ከሥራ ፈጣሪዎች ምክክር የሚደረግበት፣ ልምድና ተሞክሮ ልውውጥ የሚከናወንበት፣ ኢንተርፕረነሮች በሚጋጥሟቸው በተግዳሮቶች እና መውጫ መንገዶች ዙሪያ ምክክር የሚደረግበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሳምንቱ ባለፈው ዓመት ሚሊዮን ፈተናዎች ሚሊዮን ዕድሎች በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሃ ግብሮች መከበሩን ያስታወሱት ሚንስትር ዴኤታው ዘንድሮ ለኢንተርፕረነሮች የማይመቹ የተዘጉ በሮች በመኖራቸው እነዚህ የተዘጉ በሮች እንዲከፈቱ እና እንቅፋቶች እንዲቀረፉ ታሳቢ በማድረግ ለኢንተርፕረነሮች ክፍት ይሁኑ በሮች በሚል መሪ መልዕክት ባለድርሻ አካላትን በሳተፉ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል ብለዋል፡፡
የኢንተርፕሪነርሺፕ ምህዳርን ለማስፋት የተጀመሩ ሥራዎች በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ያስረዱት ክብርት ሚኒስትር ‹‹ለኢንተርፕሪነሮች፣ ክፍት ይሁኑ በሮች፤ ›› የሚለውን መሪ ሃሳብ ለመተግበር በሚያስችል መልኩ የፖሊሲና የህግ ማሻሻያዎች እንዲተገበሩ ግፊት ማድረግን ጨምሮ አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ትብብሮችን የማጠናከር ፣ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን የማስፋትና የፈጠራ ባለቤቶችን የማብቃት ሥራ በስፋት እንደሚሰራም ተናግረዋል፡፡
‹‹ ለኢንተርፕሪነሮች፣ ክፍት ይሁኑ በሮች! ››
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የዓለም አቀፉን የኢንተርፕሪነርሺፕ ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች ከህዳር 24/2016 ዓ.ም ጀምሮ እያከበረ ይገኛል፡፡
‹‹ለኢንተርፕሪነሮች፣ ክፍት ይሁኑ በሮች›› በሚል መሪ ሃሳብ እየተከበረ በሚገኘው በዚህ በዓል ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ባስተላለፉት መልዕክት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ የሥራ ዕድልን የሚያሰፉና አዳዲስ የፈጠራና የኢኖቬሽን ሃሳቦች በልፅገው ወደ ተግባር እንዲቀየሩ የሚያስችሉ ሥራዎችን በትኩረት እየሠራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
ከአንድ ዓመት በፊት ‹‹ከህዳር እስከ ህዳር›› በሚል ኢንትርፕሪነርሺፕን ለማበልፀግ በተያዘው ዕቅድ መሰረት ዘርፈ ብዙ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን የጠቀሱት ክብርት ሚኒስትር የፈጠራ ሃሳብ ውድድሮችን በማድረግ ኢኖቬተሮችን የማበረታታትና የማብቃት ሥራዎች መሰራታቸውን አስታውሰዋል፡፡
በዓመቱ በመላ አገሪቱ ከሚገኙ እያንዳንዱ ወረዳዎች የተውጣጡ ከአንድ ሺ በላይ ተወዳዳሪዎችን ያሳተፈ አገር አቀፍ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር ማካሄድ መቻሉንም ክብርት ሚኒስቴር ተናግረዋል፡፡
በዓመቱ በተካሄዱ ውድድሮች አሻናፊ የሆኑ ወጣቶችንና ሌሎችም የፈጠራና የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችን ሃሳብ ወደ ምርት ለመቀየር እንዲቻልም ‹‹የሠመር ካምፕ›› በሚል ሥያሜ ተግባራዊ እየተደረገ ባለው ፕሮጀክት የፈጠራ ባለሙያዎቹ በአንድ ማዕከል ተሰባስበው በሚደረግላቸው የቴክኖሎጂና የባለሙያ እገዛ የፈጠራ ሃሳባቸውን የማበልፀግና የማሳደግ ሥራ እየሰሩ እንደሚገኙም አብራርተዋል፡፡
የኢንተርፕሪነርሺፕ እሳቤ እንዲዳብርና ተቋማዊ ቅርፅ እንዲኖረው ለማስቻልም ለሥራና ክህሎት ተጠሪ የሆነውን የኢንተርፕሪነርሺፕ ልማት ኢኒስቲትዩትን የማጠናከር ተግባር መከናወኑም ተገልጿል፡፡
Closing ceremony for #GEW2023Ethiopia @ Haile Grand Hotel | Global Entrepreneurship Network
https://www.genglobal.org/ethiopia/closing-ceremony-gew2023ethiopia-haile-grand-hotel
✨✨🌟☀️Congratulations team,🌟☀️✨✨
The GenGlobal website is now up and running. Please review our recent event on the Gen platform👇
NEST(Next Ethiopian Start Up) Cafe duscussion on the way @ the closing ceremony of the #GEW2023Ethiopia📌
Global Entrepreneurship Week is a celebration of innovators who dream big and launch startups that bring ideas to life. GEW reaches millions of people of all ages and backgrounds through local, national and global events and activities. During one week each November(December), partners around the world hold events and competitions to celebrate and support local entrepreneurs.
In Ethiopia, this renowned event is being celebrated with different seminars, workshops and meetings with key stakeholders across the nation with a theme of ''Open Doors for Entrepreneurs''
Today, the closing session is being conducted @ the Haile Grand Hotel, Addis Ababa.
#GEW2023Ethiopia
Entrepreneurship Development Institute, towards building a healthy Entrepreneurial Ecoystem
በስራ አንቀሳቃሾች በተነሱት ሐሳቦች ውይይት ያደረገው የልዑካን ቡድኑ ለፖሊሲ ግብአት የሚሆኑ ሐሳቦችንና መፍትሄ የሚሻቸውን ጥያቄዎች ለሚመለከታቸው አካላት በዶ/ር ሐሰን በኩል ለማቅረብ ስምምነት ላይ ደርሷል::
በጉብኝቱ የኢትዮጵያ ልማት ባንክና የስኬት ባንክ የተካተቱ ሲሆን የኢንትርፕሪነርሽፕ ልማት ኢኒስቲትዩት እና ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ ሃላፊዎችም ተገንተዋል፡፡
የአለም አቀፉን የኢንትርፕሪነሪነርሽፕ ሳምንት ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ የተሰማሩ የግል ተቋማትን ከፍተኛ አመራሮች ጉበኙ፡፡
የኢንትርፕሪነርሽፕ ልማት ኢኒስቲትዩት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በሐገር አቀፍ ደረጃ የአለም አቀፉን የኢንትርፕሪነሪነርሽፕ ሳምንት በተለያዩ ፕሮግራሞች እያከበረ ይገኛል፡፡ የዚህ አካል የሆነው የከፍተኛ አመራሮች የግል ተቋማትን በዶ/ር ሐሰን ሁሴን በተመራ ልዑክ ተዘዋውሮ ጉብኝቷል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን አመራሮች በመወከል ቡድኑን የመሩት ዶ/ር ሀሰን ሁሴን ይህንን መሰል ተግባር ማከናወናችን ለኢንተርፕሪነሮች ስነ-ምህዳሩን ምቹ ለማድረግ ነው ብለዋል፡፡
ከተጎበኙት መካከል የኢፓክት ጋርመንትና የህትምት መስራችና ስራ አስኪያጅ የሆነችው ወ/ሮ ማርሸት ፀሃይ ባለፉት ዓመታት ከ15 ሺ ብር በመነሳት ዛሬ ላይ የ20 ሚሊዩን ካፒታል ማንቀሳቀስ የቻልኩት በሴቶች ኢንትርፕሪነርሽፕ ልማት ፕሮጀክት በተደረገልኝ ያላሰለሰ ድጋፍ ነው ያለች ሲሆን ከዚህ በላይ ለመንቀሳቀስ ግን የንግድ ስርዓቱን ምቹ ማድረግ ያስፈልጋል ብላለች፡፡
ከ300 በላይ ለሚሆኑ ሰራተኞችን የስራ ዕድል በመፍጠር ለሃገሪቱ የማያቋርጥ የውጭ ምንዛሬ እያስገባ ያለው ኤክስለረንት ቴክኖሎጂ ሶሊሸን የዓለም አቀፍ የአውት ሶርሲንግ ስራን ወደ ኢትዮጵያ በስፋት እንዲገባ ከመንግስት ከፍተኛ ድጋፍ ያስፈልጋል ይላል ዋና ስራ አስኪያጁ አቶ መላኩ በሻህ፡፡
በዚህ ጉብኝት ከተካተቱት መካከል አንዷ የሆነቸው አራያት ታምራት በእደ ጥበብ ቢዝነስ ላይ ተሰማርታ
ከ80 በላይ ለሚሆኑት የስራ እድል ፈጥራለች፡፡ ባህላዊ የኢትዮጵያ እሴትን ወደ ቢዝነስ የቀየረችው አራራት ከዚህ የበለጠ ለመስራት የብድር አቅራቢ ተቋማት ከተለመደው አሰራር ወጥተው ተራማጅ የሆነ አሰራር ሊከተሉ ይገባል ብላለች፡፡
የኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት "ለኢንተርፕረነሮች ክፍት ይሁኑ በሮች" በሚል መሪ ሀሳብ ከህዳር 24-28/2016 ዓ.ም በተለያዮ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡
በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደውን ዝግጅት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የኢንተርኘሪነርሽኘ ኢንስቲትዮት በጋራ የሚያከብሩት ሲሆን የኢንተርፕረነርሸፕ ሳምንቱን አስመልክቶ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ሥምሪት እና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ንጉሡ ጥላሁን ጋዜጣዊ መግለጫ ዛሬ ሰጥተዋል፡፡
ሚንስትሩ በመግለጫቸው ኢንተርፕረነሮች ለሀገር ኢኮኖሚ ያላቸውን ከፍተኛ አስተዋጽዎ ከግምት ውስጥ በማስገባት የፋይናንስ ተቋማት እና መንግስታዊ ድጋፎች እንዲያገኙ መንግስታዊ ተቋማት እና በግሉ ዘርፍ የተሰማሩ አካላት በራቸውን ክፍት በማድረግ ሃሳብ፣ ምርትና አገልግሎት ያላቸው ኢንተርፕረነሮች እንዲበረታቱና እንዲያድጉ በሮቻቸውን ሊከፈቱላቸውና እንቅፋቶችን ሊያስወግዱላቸው ይገባል ነው ያሉት።
የሚከበረው የኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት አዳዲስ ሃሰብ እንዲከበር፣ በሀገራችን ያሉ ኢንተርፕራይዞች በዓለም አደባባይ እንዲታወቁ እና እርስ በርስ ትስስር እንዲፈጥሩ ትልቅ ዕድል ይፈጥርላቸዋል ብለዋል፡፡
የኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት ማክበር ከተጀመረ አመታት የተቆጠሩ ሲሆን ባለፋት ሁለት ዓመታት ኢንተርፕረነርሺፕ አስተሳሰብ በሀገራችን ባህል እንዲሆን እና ሥራ ፈጣሪዎች እንዲነሳሱ በር ይከፍትላቸዋል ስራዎችን በመከወን እየተከበረ ነው፡፡
በመድረኩ ለዘርፉ ቁልፍ ባለድርሻ አካላት የሚባሉት መንግስት፣ የግሉ ሴክተር፣ የፋይናስ ተቋማት፣ የምርምር ተቋማት እና የመሳሰሉ ተገናኝተው ሃሳብ እንዲለዋወጡም እና የድርሻቸውን እንዲወጡ ይደረግበታል፡፡
ሳምንቱ በፓናል ውይይቶች : በሽልማቶች: በጉብኝቶች እና በሌሎችም ዝግጅቶች ከህዳር 24-28 ቀን 2016 ዓ.ም ይከበራል፡፡
