cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ትንሿ ቤተ-ክርስቲያን

እኛስ በትዳር ከእግዚአብሔር ጋር እንተባበራለን። ትንሿ ቤተክርስቲያንን እናይ፣እናውቅ እና እንወድ ዘንድ እንማማራለን።

Show more
Advertising posts
1 470
Subscribers
+524 hours
+397 days
+6230 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

የእናት አስፈላጊነት በልጆች አስተዳደግ ውስጥ እናት ያላት ድርሻ ጡት ከማጥባት ያለፈ ነው፡፡ እናት በልጆች ሕይወት ውስጥ በማትገኝበት ወይም እያለች ያላት ተሳትፎ ግን አናሳ በሚሆንበት ጊዜ በልጆቹ የስነ-ልቦናና ማሕበራዊ እድገት ላይ ትልቅ ቀውስ ይፈጥራል፡፡ ከእናት ውጪ ያደገች አንዲት ሴት ከሁኔታው ተገቢውን ፈውስ ካላገኘች ለበርካታ ቀውሶች ልትጋለጥ ትችላለች፡፡ ከእነዚህ ቀውሶች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡- ድፍረትን ማጣት፣ ሰዎችን ማመን አለመቻል፣ የቀይ መስመርን (personal boundary) ለማስመር ያለመቻልና የሁሉ አስደሳች የመሆን ዝንባሌ፣ በራስ ላይ ያለ የተዛባ እይታ፣ ራስን ከሰዎች ማግለል፣ የስሜት ስስነትና በማይሆን ፍቅረኛ ላይ መውደቅ፡፡ ከእናት ውጪ ያደገ ወንድም ጉዳዩ ይለከተዋል፡፡ የእናት መገኘትና አለመገኘት በወንድ ልጅም ላይ እስከ መጨረሻው የሚዘልቅ አሉታዊ ተጽእኖ አለው፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ወንድ ልጅ የመጀመሪያውን አሉታዊም ሆነ አዎንታዊ ተጽእኖ የሚቀበለው ከእናቱ ነው፡፡  አንድ ወንድ ወደዚህች አለም ከተቀላቀለ በኋላ በሕይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያውቃት ሴት እናቱን ነው፡፡ ስለሆነም ከእናቱ ጋር ያለው የልጅነት ትውስታና ግንኙነት ወደፊት በሴቶች ላይ በሚኖረው አመለካከት ላይ ዘርን ጥሎ ማለፉ አይቀርም፡፡ በእናቱ አማካኝነት የደረሰበትን የመጣል፣ ችላ የመባልና የመሳሰሉት ባህሪዎችን ወደፊት በሚኖረው ግንኙነት ውስጥ የመፍራትን ዝንባሌ ሊያዳብር ይችላል፡፡ በእናቱ “በርታ” ተብሎ ያደገ ልጅና ያንን ሳያገኝ ወይም ተቃራኒን ሰምቶ ያደገ ወንድ ይህ ልምምዱ ወደፊት ከሴቶች ጋር በሚኖረው ግንኙነት ላይ የሚጫወተው ሚና ቀላል አይሆንም፡፡ አንዳንድ የእናትን ጣእም ሳያገኙ ያደጉ ወንዶች ፍቅረኛ ወደመያዝ ደረጃ ሲደርሱና በዚያ መስክ ሲሰማሩ ሳያውቁት ያንን በልጅነት ያጡትን የእናትነት ምስልና እንክብካቤ ፍለጋ ከእድሜያቸው በብዙ ወደሚበልጡ ሴቶች የመሳብ ዝንባሌ ሊኖራቸው ይችላል፡፡ ሆኖም፣ የዚህን ዝንባሌና ተጽእኖ የሚያዩት በትዳር ውስጥ ከቆዩና የእድሜ ልዩነቱን በግላጭ ማየት ሲጀምሩ ነው፡፡ ከላይ በጥቂቱ ለመጠቃቀስ የሞከርናቸው ሃሳቦች የአባትንና የእናትን ተገቢ የሆነ ግንኙነት፣ ፍቅር፣ እንክብካቤና ሚና ሳያገኙ ያደጉ ልጆች ሊጋፈጧቸው የሚችሉትን ሞጋች ሁኔታዎች አመልካች ናቸው፡፡ እነዚህ ልጆች አድገው ወደ ወጣትነት፣ አልፎም ወደ አዋቂነት ሲሻገሩ ከተቃራኒ ጾታ ጋር ያላቸውን ግንኙነት በምን አይነት ቅድመ-ምልከታ እንደሚቀርቡት የሚወስንላቸው ይህ በልጅነታቸው አመታት ቀምሰው ወይም ሳይቀምሱ ያደጉት የቤተሰብ ጣእም ነው፡፡ @TnshuaBetechrstian
Show all...
👍 6😢 4
♡YAHWEH PROMOTION♡ ↪ ያህዌህ ፕሮሞሽንም እግዚአብሔር ዓላማው በማድረግ በርከት ያሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ቻናሎች መዝግቦ ለምእመናን  እንዲዳረሱ  ፕሮሞት እያደርገ ይገኛል ። ↪  በፍጥነት ለማሳደግ አሁኑኑ ይስመዝግቡ               ➱ 👉@ZEMARYAM_NEGN ☎ Tel      :- +251943686155   :- +251977157265 📞 ያገኙናል https://t.me/Saint_Mary21 ይቀላቀሉ
Show all...
ሰአሊ ለነ ቅድስት

ፍቅር ግን ከሁሉ ይበልጣል

⛪የህይወት ምክር⛪
❤ ምክረ አበው ❤
✅ ተአምረ ማርያም ✅
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፩
⛪ሥርዓተ ቤተክርስቲያን እንማማር ⛪
✅መንፈሳዊ ትምህርት✅
🔸የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙሮች 🔸
💟የኢትዮጵያ አድባራትና ገዳማት ታሪክ💟
👏ኑ እንዘምር 👏
🎚ነይ ነይ እምዬ ማርያም🎚
📍Ortoodooksi 📍
ዘሰዋስም
💧የመ/ር ዘበነ ለማ መግለጫዎች 💧
💠ሐመረ ኖህ💠
💧የንግስ መዝሙሮች 💧
መንፈሳዊ ግጥሞች እና ወጎች
♦የቤተክርስቲናችን መዝሙርና ግጥሞች♦
♻ ምስባክ ወማኅሌት ♻
⚜አምኃ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ ⚜
🔸የክርስቶስ ጃንደረባ 🔸
🔸ነ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እንወቅ 🔸
🔸ማስያስ 🔸
🀄የመንፈስ ፍሬዎች 🀄
1⃣አንዲት ሃይማኖት1⃣
☦መዓዛ ሠናይ☦
⚜ንቁ ክርስትያኖች ⚜
💠ደቂቀ እስጢፋኖስ 💠
📯ከብሮን የዜማ መሳርያ 📯
⚜የማርያም ፍሬዎች⚜
⚜ቅድስት ፌብሮኒያ⚜
💠መኅርኒ ድንግል💠
🔸ትንሿ ቤተክርስቲያን🔸
📯ራእየ ማርያም 📯
ዘመርቆሬዎስ
✍ከባለ20ሺ -30ሺ ለማስመዝገብ
✍ከባለ10ሺ-20ሺ ለማስመዝገብ
📝ነጻ ፕሮሞሽን ለሁሉም 📝
Free FaceSwap🤖
Best DeepNude🙈
♡YAHWEH PROMOTION♡ ↪ ያህዌህ ፕሮሞሽንም እግዚአብሔር ዓላማው በማድረግ በርከት ያሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ቻናሎች መዝግቦ ለምእመናን  እንዲዳረሱ  ፕሮሞት እያደርገ ይገኛል ። ↪  በፍጥነት ለማሳደግ አሁኑኑ ይስመዝግቡ               ➱ 👉@ZEMARYAM_NEGN ☎ Tel      :- +251943686155   :- +251977157265 📞 ያገኙናል https://t.me/Saint_Mary21 ይቀላቀሉ
Show all...
ሰአሊ ለነ ቅድስት

ፍቅር ግን ከሁሉ ይበልጣል

⛪የህይወት ምክር⛪
❤ ምክረ አበው ❤
✅ ተአምረ ማርያም ✅
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፩
⛪ሥርዓተ ቤተክርስቲያን እንማማር ⛪
✅መንፈሳዊ ትምህርት✅
🔸የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙሮች 🔸
💟የኢትዮጵያ አድባራትና ገዳማት ታሪክ💟
👏ኑ እንዘምር 👏
🎚ነይ ነይ እምዬ ማርያም🎚
📍Ortoodooksi 📍
ዘሰዋስም
💧የመ/ር ዘበነ ለማ መግለጫዎች 💧
💠ሐመረ ኖህ💠
💧የንግስ መዝሙሮች 💧
መንፈሳዊ ግጥሞች እና ወጎች
♦የቤተክርስቲናችን መዝሙርና ግጥሞች♦
♻ ምስባክ ወማኅሌት ♻
⚜አምኃ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ ⚜
🔸የክርስቶስ ጃንደረባ 🔸
🔸ነ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እንወቅ 🔸
🔸ማስያስ 🔸
🀄የመንፈስ ፍሬዎች 🀄
1⃣አንዲት ሃይማኖት1⃣
☦መዓዛ ሠናይ☦
⚜ንቁ ክርስትያኖች ⚜
💠ደቂቀ እስጢፋኖስ 💠
📯ከብሮን የዜማ መሳርያ 📯
⚜የማርያም ፍሬዎች⚜
⚜ቅድስት ፌብሮኒያ⚜
💠መኅርኒ ድንግል💠
🔸ትንሿ ቤተክርስቲያን🔸
📯ራእየ ማርያም 📯
ዘመርቆሬዎስ
✍ከባለ20ሺ -30ሺ ለማስመዝገብ
✍ከባለ10ሺ-20ሺ ለማስመዝገብ
📝ነጻ ፕሮሞሽን ለሁሉም 📝
Free FaceSwap🤖
Best DeepNude🙈
Photo unavailableShow in Telegram
1 ጢሞቴዎስ 2 (1 Timothy) 9-10፤ እንዲሁም ደግሞ ሴቶች በሚገባ ልብስ ከእፍረትና ራሳቸውን ከመግዛት ጋር ሰውነታቸውን ይሸልሙ፤ እግዚአብሔርን እንፈራለን ለሚሉት ሴቶች እንደሚገባ፥ መልካም በማድረግ እንጂ በሽሩባና በወርቅ ወይም በዕንቍ ወይም ዋጋው እጅግ በከበረ ልብስ አይሸለሙ። ስለ ትንሿ ቤተክርስቲያን 👇👇👇👇👇👇👇👇 @TnshuaBetechrstian
Show all...
22👍 7🥰 4
Photo unavailableShow in Telegram
ላላገቡ . . . ልጅ፡- “እማዬ፣ ሃብታም ሰው ባገባ ይሻላል ወይስ ቆንጆ ሰው ባገባ ይሻላል?” እናት፡- “ልጄ፣ እውነተኛ ሰው አግቢ”! #ስለ #ትንሿ #ቤተክርስቲያን 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TnshuaBetechrstian
Show all...
21👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
#ስለ #ሩካቤ #ስጋ ወደ ትዳር ስንገባ በጣም አስፈላጊው ነገር ልምድ አልባ መሆን ነው።ምንም እንኳን አንዳንድ ሰዎች የሩካቤ ፍላጎታቸውን ለመፈጸምና ድካማቸውን በምክንያት ለመሸፈን ሲሉ "እንደ ስራ ልምድ" ቢቆጥሩትም እውነታው ግን እንደዚያ አይደለም።አንድ ኦርቶዶክሳዊ ወደ ትዳር ለመግባት የሩካቤ ልምድ አያስፈልገውም ኹለታችንም ልምድ አልባ ስንሆን የትዳር አጋሮቻችንን ከሌሎች ጋር አናነጻጽራቸውምና።አንዳችን ለአንዳችን የሚኖረን ፍቅርም ንጹህ እንዲሆን ያደርገዋል። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይህንን ሲያብራራው እንዲህ ይላል፦ "ድንግል ወንድ ድንግል ሴትን ማግባቱ ለትዳራቸው ጤናማነት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ቀላል እንደሆነ ታስባለህን? አይደለም!ድንግልናውን ለጠበቀ ወንድ ብቻ አይደለም ፤ድንግልናዋንም ለጠበቀች ልጃገረድም ጭምር እንጂ።ፍቅራቸው ፍጹም ንጹሕ አይሆንምን? ከሁሉ በላይስ እነዚህ ወጣቶች ንጽሕናቸውን ጠብቀው እንደ ሕጉና እንደ ስርአቱ ተጋብተው ስለ ተዋሐዱ ደስ ተሰኝቶ እግዚአብሔር  ትዳራቸውን ስፍር ቁጥር በሌለው በረከት አይሞላላቸውምን? አዎን እንደዚህ ሆነው ባል ለሚስቱ ያለውን ንጹሕ ፍቅር ዘወትር እንዲያስበው ያደርገዋል።ይህን አይነት መውደድ፣ይህን አይነት ፍቅርም ዘወትር እንዲያስበው ያደርገዋል።ይህንን አይነት መውደድ ይህን ፣አይነት ፍቅር አጽንቶ የያዘ እንደሆነም ከሚስቱ በቀር ወደ ሌላ ሴት ዓይኑን አያነሳም።" #ስለ #ትንሿ #ቤተክርስቲያን 👇👇👇👇👇👇👇 @TnshuaBetechrstian
Show all...
20👍 1👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
አባት-ሆይ አባቶች!!! ስለሴት ልጆቻችሁ የወደፊት ስትሉ እቤታችሁ ተገኙ፤ የአባትነትን ሚና ተጫወቱ! ሴት ልጃችሁ ከወንድ የሚገኘውን ጥበቃ (Security) እና የጨዋ ወንድ ባህሪይ ለመጀመሪያም፣ ለመጨረሻም ጊዜ የምትማረው ከእናንተ ብቻ ነው፡፡ ሴት የትክክለኛ ባልን ምንነት ለመጀመሪያም፣ ለመጨረሻም ጊዜ የምትማረው ከእናንተ ብቻ ነው፡፡ ሴት ልጃችሁ ከሌላ ወንድ ትኩረትን አገኘችም አላገኘችም በራሷ ሙሉ ሆና ልትኖር እንደምትችል ያላትን የሙሉነት ግንዛቤ ለመጀመሪያም፣ ለመጨረሻም ጊዜ የምትማረው ከእናንተ ብቻ ነው፡፡ #ስለ #ትንሿ #ቤተክርስቲያን 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TnshuaBetechrstian
Show all...
17👍 6
+ ዘኬዎስ አጭር ባይሆን + ዘኬዎስ በማጠሩ ምክንያት በኢያሪኮ እያለፈ ያለውን ክርስቶስን ለማየት ተቸገረ:: ሕዝቡ ብዙ ነውና የቆሙት ሁሉ ጌታን ከማየት ከለሉት:: የሾላ ዛፍ ላይ ወጥቶ ጌታን ለማየት ሲሞክር ጌታ አሻቅቦ አየው:: እሱ ዛፍ ላይ ጌታን ሊያይ እንጂ ሊታይ አልወጣም:: ጌታ ሊታዩ ከሚሞክሩ ይልቅ ሊያዩት የሚሹትን ይወዳልና ዘኬዎስን ጠራው:: ከምድር ቆመን ዓይናችንን አንጋጥጠን ማረን የምንለው ጌታ ዘኬዎስን ከምድር ሆኖ ወደ ላይ እያየ ና ልማርህ አለው:: "ዛሬ በቤትህ እውል ዘንድ ይገባኛል" አለው:: ጌታ ወደ ቤቱ ገባ:: ለዘኬዎስ ቤት መዳን ሆነለት:: ዘኬዎስ አጭር ባይሆን ኖሮ ከሰዎች ጋር እየተጋፋ ጌታን ያይ ይሆናል እንጂ በጌታው ዓይን ለመታየት የሚያበቃ ትጋት አያሳይም ነበር:: ምናልባትም ሰዎችን ገለል በሉ እያለ በኩራት ሲጋፋ ከአንዱ ጋር ሲጣላ ሊቆይ ይችል ነበር:: ዘኬዎስ አጭር ባይሆን ከዛፍ ላይ አይወጣም ነበር::  ዘኬዎስ አጭር ባይሆን የሠራዊት አምላክ ወደ ቤቱ አይገባም ነበር:: በኪሩቤል ላይ የሚቀመጠው ንጉሥ በቤቱ ወንበሮች ላይ የተቀመጠው ዘኬዎስ በማጠሩ ምክንያት ነው:: የዘኬዎስ ነፍስ የዳነው በቁመቱ ማጠር ነበር:: እግዚአብሔር የመዳኑን ቀን የቆረጠለት ቁመቱን ሲያሳንሰው ነበር:: በምድር በመጽሐፍ ቅዱስ በሰማይ በሕይወት መዝገብ ስሙ የተጻፈው ዘኬዎስ አጭር በመሆኑ ነው:: ስለ ቁመት የማወራ እንዳይመስልህ:: እግዚአብሔር ለነፍሳችን መዳን የሚያሳጥርብን ብዙ ነገር አለ:: እንደ ዘኬዎስ ቁመትህ አጭር ባይሆን የሚያጥርህ ነገር ግን አይጠፋም:: ይሄ ጎደለኝ የምትለው ከሰዎች አነስኩበት የምትለው ነገር አንዳች ነገር የለም? እሱን ማለቴ ነው:: ይሄ ይጎድለኛል ከሰው አንሳለሁ እያልክ አትማረር:: እጥረትህ መክበሪያህ ነው:: ጉድለትህም መዳኛህ ነው:: እግዚአብሔር ያጎደለብህ የመሰለህ ነገር ወደ ዛፍ እንድትወጣ ምክንያትህ ይሁን:: በጉድለትህ እንደ ዘኬዎስ ከፍ በልበት:: ያኔ ሰዎች አንተን አንጋጠው ከማየት ውጪ አማራጭ አይኖራቸውም:: ፈጣሪ በፍቅሩ ይይህ እንጂ ሰዎች ወዳንተ ያዘነብላሉ::  በቤትህ መዳን ይሆንልሃል:: ከዚያም ስላጠረህ ስለጎደለህ ነገር ፈጣሪህን ስታመሰግነው ትኖራለህ:: እመነኝ አንዳንድ ጉድለቶች እድሎች ናቸው:: ዘኬዎስ አጭር ባይሆን ይሄኔ በሾላው ዛፍ ጥርሱን እየፋቀ ይቀር ነበር:: በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ #ስለ #ትንሿ #ቤተክርስቲያን 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TnshuaBetechrstian
Show all...
👍 8 5
Photo unavailableShow in Telegram
"መላው ዓለምን ያስደነገጡ ታላላቅ መከራዎች ኹሉ መነሻቸው ትዕቢት ነው ፡፡"         ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይምረን ዘንድ በፊቱ እንበርከክ
Show all...
🙏 17 4👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
ደናግል ሆይ! መለኮታዊ ክብርና ጸጋ የተሰጣችሁ መልካም ወይን ናችሁ። #ስለ #ትንሿ #ቤተክርስቲያን 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TnshuaBetechrstian
Show all...
🙏 12🥰 5 1👏 1