en
Feedback
MEHON MEDIA

MEHON MEDIA

Open in Telegram
1 440
Subscribers
No data24 hours
-117 days
-4530 days
Posts Archive
የ2017 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆኗል። በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው በመደበኛው ፕሮግራም ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተ
የ2017 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆኗል። በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው በመደበኛው ፕሮግራም ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የሚያስችል የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ሆኗል። ተማሪዎች ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ምደባቸውን ማየት እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል። ድረ-ገፅ: placement.ethernet.edu.et ቴሌግራם: MoE Student Bot የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማያስተናግድ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል። @mehonmedia

እንኳን ደስ አላችሁ **** የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመደበኛው፣ በተከታታይና በክረምት መርሀ-ግብር ያስተማራቸውን 3271 የ2016 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎችን መስከረም 25/2
እንኳን ደስ አላችሁ **** የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመደበኛው፣ በተከታታይና በክረምት መርሀ-ግብር ያስተማራቸውን 3271 የ2016 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎችን መስከረም 25/2017 ዓ.ም ያስመርቃል። በመሆኑም ለመላው የዩኒቨርሲቲያችን እና የአካባቢያችን ማህበረሰብ እንዲሁም ለተመራቂ ተማሪዎቻችንና ለተማሪ ቤተሰቦቻቸው ከወዲሁ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። እንኳን ደስ ያላችሁ ! *** ለልህቀት እንተጋለን የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳሬክቶሬት መስከረም 21/2016 ዓ.ም @mehonmedia

የህፃን ሄቨንን ጉዳይ በተመለከተ የተደረገ ውይይት @mehonmedia

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልጇን በግፍ ለተነጠቀቸው ሕጻን ሄቨን እናት የመኖሪያ ቤት አበረከተ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልጇን በግፍ ለተነጠቀቸው ሕጻን ሄቨን እናት የመንግስት መኖሪያ ቤት
+1
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልጇን በግፍ ለተነጠቀቸው ሕጻን ሄቨን እናት የመኖሪያ ቤት አበረከተ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልጇን በግፍ ለተነጠቀቸው ሕጻን ሄቨን እናት የመንግስት መኖሪያ ቤት አበርክቷል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ የሄቨንን እናት በማግኘት አጽናንተዋል:: ልጇን በግፍ ተነጥቃ ባለፈው አንድ ዓመት ፍትሕ ሳታገኝ ለቆየችው ሲስተር አበቅየለሽ የፍትሕ ሒደቱን ለመከታተል፣ያለችበት ሁኔታ የተሻለ እንዲሆንላትና ተጋላጭነቷን ለመቀነስ እንዲመች የከተማ አስተዳደሩ አንድ የመንግስት መኖሪያ ቤት አበርክቷል፡፡ ከዚህ ባለፈም በሙያዋ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ እንድትሰራ መመቻቸቱን ነው ከንቲባ አዳነች የገለጹት፡፡ የህጻን ሄቨን ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ በመሆኑ ድርጊቱ ተገቢውን ፍትሕ ማግኘቱ የሌሎች ህፃናት ተጋላጭነትን ለመቀነስ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ከንቲባዋ አስገንዝበዋል፡፡ መሰል ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት እንዳይፈፀም የማህበረሰቡ የአመለካከት ለውጥ እንዲመጣና ችግሩ የጋራ ጉዳይ በመሆኑ ሁሉም ሃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ @mehonmedia

#Ethiopia #ፍትሕ በአሰቃቂ ሁኔታ ተደፍራ የተገደለችው የ7 ዓመቷ ህጻን ሔቨን ታሪክ የበርካቶችን ልብ የሰበረ ጉዳይ ሆኗል። ይህ ድርጊት የተፈጸመው ከዛሬ #አንድ_ዓመት በፊት በባህርዳር ከተማ እንደሆነ ዛሬም ድረስ መሪር ሀዘን ውስጥ የምትገኘው እናት " ኢዮሃ " በተሰኘ የማህበራዊ ሚዲያ ላይ ቀርባ ተናግራለች። ሕጻን ሔቨን የተደፈረችው ተከራይተው ይኖሩበት በነበረ ግቢ አከራይ ነው። የተደፈረችበት መንገድም ወደ ሽንት ቤት በምትሔድበት ጊዜ ጠብቆ ወደ ቤት በማስገባት ነው። እጅግ በጣም አሰቃቂም ነበር። ህጻን ሔቨንን የደፈረው ወንጀለኛ በምትደፈርበት ወቅት አንገቷን አንቆ ፤ አፏን አፍኖ ድርጊቱን የፈጸመ ሲሆን ወድቃ የሞተች ለማስመሰል ደሟን አንጠባጥቦ በር ላይ ጥሏት መሄዱን እናት ታስረዳለች። እናት ልጇን ብቻ አይደለም ያጣችው ፤ ፍትህ ስትጠይቅ ይህንን ግፍ ሰምተው እንዳልሰማ የሆኑ ጎረቤት እና ቤተሰቦች ፤ በጥቅም ወንጀለኛውን ነጻ ለማስወጣት የሰሩ ፤ እናትን ጭምር ተባብረው ለማጥፋት ረጅም ርቀት የተጓዙ ፤ ማስፈራሪያ ደርሷቸው ቃላቸውን ከመስጠት የጠፉ ሁሉ ለእናት ፈተና ሆነውባታል። ይህም ሆኖ ጥቂት የሚባሉ (የሴቶች እና ህጻናት ወንጀል መሪማሪ ፖሊሷ፤ የሴቶችና ህጻናት ቢሮ) አንዳንዶቹ ማስፈራሪያ ጭምር እየደረሳቸው አግዘዋት ከብዙ መከራ በኋላ ድርጊቱን የፈጸመው ግለሰብ በ25 ዓመት ጽኑ እስራት ይፈረድበታል። እናት ግን ዛሬም ትኩስ ሀዘን ላይ ነች። ሥራ እየሰራች መኖር አልቻለችም። ነገ ከእስር ሲለቀቅ እሷንም ጭምር ለመግደል እንደሚፈልግ ፤ ለዚህም ደግሞ ዳግም ሥራ ከጀመረችበት ቦታ ቤተሰቦቹ ተከታትለዋት ጥላ መውጣቷን እናት አስረድታለች። ዛሬም እውነተኛ ፍትሕ አጥታ ትንከራተታለች። ግፍ ላይ ግፍ ! በመሰረቱ በዚህች ምስኪን አንድ ፍሬ ፤ ክፉ ደግ በማታውቅ ህጻን ላይ አሰቃቂ የመድፈር እና ኃሏም ህይወቷን ያሳጣ የወንጀል ድርጊት የፈጸመ ሰው እንዴት 25 ዓመት ይፈረድበታል ? እውነት ይህ ማስተማሪያ ነው ? ወይስ ሌላ ነው ዓላማው ? የሔቨን ታሪክ የብዙ ህጻናት ታሪክ ጭምር ነው። ከዚህ በፊት ሴቶች፣ ህጻናት ጭምር ሲደፈሩ የሚተላለፉ የፍርድ ውሳኔዎች ህዝቡን እያስቆጣ መሆኑን አሳውቀን ነበር። ዛሬም ፍትሕ ተጓድሏል። ፍትሕ ይስፈን። ዛሬ አጋጣሚ ይህ ጉዳይ አደባባይ ወጣ እንጂ ስንቷ እናት ቤቷ ዘግያ እያለቀሰች ይሆን ? ስንት ሴቶች በግፍ ሰለባ ሆነው እያነቡ ይሆን ? @mehonmedia

photo content
+3

የ7 አመት ህፃን ደፍሮ ከዛም በጭካኔ የገደለው ወንጀለኛ ይግባኝ የማለት መብት ለምን ተሰጠው በሚል እየሞገተ መሆኑን የአማራ ክልል የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ በትናንትናው እለት በእዮሃ ሚድያ
የ7 አመት ህፃን ደፍሮ ከዛም በጭካኔ የገደለው ወንጀለኛ ይግባኝ የማለት መብት ለምን ተሰጠው በሚል እየሞገተ መሆኑን የአማራ ክልል የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ በትናንትናው እለት በእዮሃ ሚድያ የተላለፈ የአንድ ህፃን መደፈር እና በጭካኔ መገደል መረጃ ከወጣ በኋላ በርካቶችን ማሳዘኑ እና ማነጋገሩን ቀጥሏል። ድርጊቱ ከተፈፀመበት ከ2014 መጨረሻ ወራት ጀምሮ ጉዳዩን ሲከታተሉ ከነበሩ የመንግስት አካላት አንዱ የሆነውን የአማራ ክልል የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊን መሠረት ሚድያ አነጋግሯል። የቢሮው ሀላፊ ወ/ሮ ብርቱካን ሲሳይ "የ25 አመት ፍርድ ያገኘ ጉዳይ እንዴት ይግባኝ ተፈቀደበት ብለን ከክልሉ ፍትህ ቢሮ ጋር በጋራ እየሰራንበት ነው" ብለው ማብራርያ ሰጥተዋል። "ግለሰቡ 25 አመት ተፈርዶበት እስር ላይ ቢገኝም በህግ ይግባኝ ተፈቅዶበታል፣ ፍርድ ቤት ያስቀርባል ብሎታል። አሁን እኛ ይግባኝ መባሉ እንዴት ተቻለ ብለን እየሞገትን ነው" ብለው መረጃ ሰጥተዋል። ሀላፊዋ ግለሰቡ የፍርድ ውሳኔ እንዲያገኝ ክልሉ ካለበት አሁናዊ ሁኔታ አንፃር ከፍተኛ ጥረት ተደርጎ እንደተፈረደበት ገልፀው "ይሄ እንዴት ይግባኝ ያስቀርባል?" ብለው ለራሳቸው ጥያቄ እንደሆነባቸውም ገልፀዋል። በተያያዘ ዜና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በህፃን ሄቨን ላይ በተፈፀመው ወንጀል በተሰጠው ውሳኔ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር እሰራለሁ ብሏል። ሚኒስቴሩ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ በህፃኗ ላይ በተፈፀመው ዘግናኝ የሆነ ኢ ሰብአዊ ወንጀል የተሰጠው ዉሳኔ አስመልክቶ ይግባኝ ለመጠየቅ የሚኬድበት አግባብ ባለመሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር እንደሚሰራ አስታውቋል። @mehonmedia

#Ethiopia በማራቶን ውድድር ላይ " ተጠባባቂ ነህ " ተብሎ የተያዘውና ለውድድሩ የተመረጠ ሌላ አትሌት መጎዳቱን ተከትሎ ሀገሩን ወክሎ የተሳተፈው ጀግናው አትሌት ታምራት ቶላ ለሀገሩ ኢትዮጵያ ወ
+2
#Ethiopia በማራቶን ውድድር ላይ " ተጠባባቂ ነህ " ተብሎ የተያዘውና ለውድድሩ የተመረጠ ሌላ አትሌት መጎዳቱን ተከትሎ ሀገሩን ወክሎ የተሳተፈው ጀግናው አትሌት ታምራት ቶላ ለሀገሩ ኢትዮጵያ ወርቅ ማምጣት ብቻ ሳይሆን በሚደንቅ ብቃት የኦሎምፒክ ሪከርድም ጭምር ነው የሰበረው። ጀግናው አትሌት ታምራት ከአትሌት ገዛኸኝ አበራ በኋላ (ከ24 ዓመታት በኃላ) ነው የመጀመሪያውን የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ ለሀገራችን ያስገኘው። ሌላው አንጋፋው ኢትዮጵያ ሁል ጊዜ በስራው የምታመሰግነው የ42 ዓመቱ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ 39ኛ ደረጃ ይዞ እጅግ ከባድ የነበረውን የፓሪስ ማራቶን አጠናቋል። አትሌት ደሬሳ ገለታም 5ተኛ ደረጃ በመውጣት እጅግ በጣም አበረታችና ተስፋ ሰጪ ውጤት አስመዝግቧል። ምንም እንኳን ዛሬ በወንዶች ማራቶን የተገኘው ውጤት አስደሳችንና የሚያኮራ ቢሆንም በፓሪስ እየተመዘገበ ያለው ውጤት ኢትዮጵያን የሚመጥናት አይደለም። በጭቅጭቅና ንትርክ በተሞላው በዚህ ውድድር ኢትዮጵያ ያገኘችው እስካሁን 3 ሜዳሊያ ብቻ ነው። 1 ወርቅ እና 2 ብር ብቻ። የአትሌቲክሱ ዘርፍ ትኩረት ተሰጥቶ ያሉ ችግሮች እና ኢትዮጵያን ዝቅ ያደረጉ ነገሮች ሁሉ ተፈትሸው መለወጥ እንዳለባቸው የፓሪስ ኦሎምፒክ በግልጽ አመላክቷል። ከሚዲያ በዘለለ ስለዚህ ሀገር አትሌቲክስ ሁሉም " የሀገር ክብር ያሳስበኛል " የሚል ቁጭ ብሎ ተነጋግሮ በአስቸኳይ ለውጥ ማምጣት አለበት። እንዲህ ከቀጠለ በዓለም ደረጃ የነበረን ክብር የማናጣበት ምክንያት የለም። @mehonmedia

#Ethiopia በኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ የሐዋሳ ቅርንጫፍ በመደበኛው የፓይለት ስልጠና ልምምድ ላይ የነበረ ቀላል የተማሪዎች መለማመጃ አውሮፕላን (Dimond DA40NG) አየር ላይ ሳለ ባጋጠ
#Ethiopia በኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ የሐዋሳ ቅርንጫፍ በመደበኛው የፓይለት ስልጠና ልምምድ ላይ የነበረ ቀላል የተማሪዎች መለማመጃ አውሮፕላን (Dimond DA40NG) አየር ላይ ሳለ ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር ምክንያት አርሲ ነጌሌ አካባቢ ለማረፍ መገደዱን የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርስቲ ገልጿል። " ይህንን ተከትሎ በመደበኛ ስልጠናው ላይ የነበሩት አስተማሪውና ተማሪው የመለማመጃ አውሮፕላኑ ሕብረተሰቡ ላይ አደጋ በማያደርስ ሁኔታ ለማሳረፍ ከፍተኛ ጥረት ያደረጉ ቢሆንም ለማረፍ በተደረገው ጥረት መሬት ላይ በነበረች አንዲት ታዳጊ ላይ ጉዳት ደርሷል " ሲል ገልጿል። የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርስቲ፥ የአደጋው መንስኤ ምን እንደሆነ በሚመለከታቸው አካላት በመጣራት ላይ መሆኑን አሳውቋል። @mehonmedia

#Tigray #TPLF "ሊካሄድ በታቀደው ጉባኤ አልሳተፍም ! " - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስታዳደር ፕሬዜዳንት እና የህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ ዛሬ ዓርብ ነሀሴ 3/201
+1
#Tigray #TPLF "ሊካሄድ በታቀደው ጉባኤ አልሳተፍም ! " - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስታዳደር ፕሬዜዳንት እና የህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ ዛሬ ዓርብ ነሀሴ 3/2016 ዓ.ም ለህወሓት ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ፣ ለድርጅቱ የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ተኽለብርሃን ኣርኣያ በፃፉት ደብዳቤ በጉባኤው እንደማይሳተፉ አረጋግጠዋል። ፕሬዜዳንቱ በደብዳቤያቸው የድርጅቱን ከፍተኛ አመራሮች ውሳኔ በጣሰው ጉባኤና የምዝገባ ሂደት እንደማይሳተፉ በመግለፅ " ህወሓት መዳን የሚችለው አባላቱና አመራሩ በሚያካሂዱት ጤናማ እንቅሰቃሴ ነው " ሲሉ አስታውቀዋል።  @mehonmedia @mehonpodcast1

የደመወዝ ማሻሻይ ይፋ ተደርጓል ? እስካሁን የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ / ጭማሪ ዝርዝር መረጃ ይፋ አልተደረገም። በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በቴሌግራም ፣ በፌስቡክ እየተዘዋወረ ያ
የደመወዝ ማሻሻይ ይፋ ተደርጓል ? እስካሁን የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ / ጭማሪ ዝርዝር መረጃ ይፋ አልተደረገም። በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በቴሌግራም ፣ በፌስቡክ እየተዘዋወረ ያለው " የፌዴራል መንግሥት ሲቪል ሰርቫንት ደመወዝ ማሻሻያ " የሚለው መረጃ ምንም ምንጩ የማይታወቅ ነው። የተሰራጨው የደመወዝ ማሻሻያ ሰንጠረዥ ፤ የፅሁፍ ስህተቶች ጎልተው የሚታዩበት፣ የአጻጻፉ ግድፈት ያለበት፣ የድምር ጭምር ግልጽ እና ቀላል ስህተት ያለበት ነው። ሲቀጥል ማን ይፋ እንዳደረገው አይታወቀም። ማህተም አላፈረበትም ፤ መረጃውን ያወጣው መ/ቤትም አይታወቅውም። እስካሁን በይፋ ለህዝብ የተሰራጨ የደመወዝ ጭማሪ ዝርዝር መረጃ የለም። መንግሥት በቅርቡ የደመወዝ ጭማሪ እንደሚደረግ ማሳወቁ ይታወሳል። @mehonmedia @mehonpodcast1

#አበሽጌ በማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ጉራጌ ዞን፣ አበሽጌ ወረዳ ዋልጋና ዳልጌ ከተሞች የሚኖሩ ወጣቶች ባለሀብቶችና አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች በጸጥታ ኃይል በአፈሳ እየተያዙ መሆናቸውን ተከትሎ ወ
#አበሽጌ በማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ጉራጌ ዞን፣ አበሽጌ ወረዳ ዋልጋና ዳልጌ ከተሞች የሚኖሩ ወጣቶች ባለሀብቶችና አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች በጸጥታ ኃይል በአፈሳ እየተያዙ መሆናቸውን ተከትሎ ወጣቶች ከቤት ለመውጣት ፍርሀት ውስጥ መሆናቸው ተሰምቷል። አካባቢው በተለይ ከኦሮሚያ ጋር የሚዋሰንባቸው መንደሮች ካሁን በፊት ግጭቶች መፈጸማቸውን ተከትሎ በስጋት መቆየታቸውን የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች ከሰሞኑ እየሆነ ያለው ነገር እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል። ምንም እንኳን ወጣቱ በፍርሀት ቤቱ ቢቀመጥም አንዳንዶቹ ቤታቸዉ ባሉበት መያዛቸዉን ተከትሎ ፍርሀቱ ከፍ ሊል ችሏል። ሁኔታውን በተመለከተ ማን ማንን ነው እየያዘ ያለው ? ስንል የጉራጌ ዞን ፖሊስ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ገና ደገሞን ጣይቀናል። እሳቸውም " የተቀናጀ የጸጥታ ኃይል ወንጀለኞችን እየያዙ ነው " ብለዋል። በተጨማሪም ሰው ፍርሀት ውስጥ ነው ለሚባለው " ወንጀል ውስጥ እጁ ካለበት ሰው ውጭ ንጹሀኑ ፍርሀት ሊገባው አይገባም " ሲሉ መልሰዋል። " አሁን ላይ የብሄራዊ ደህንነትን ጨምሮ የፌደራል ፖሊስና መከላከያ ሰራዊት በአካባቢዉ ተሰማርተዉ አሰሳ በማድረግ የጥፋት ኃይሎችን እየያዙ ነው " በማለት አካባቢዉ በፍጥነት ወደነበረ ሰላሙ ይመለሳል ብለዋል። ዋና ኢንስፔክተሩ አክለዉ " እንቅስቃሴዉ በአበሽጌ ወረዳና በኦሮሚያ ወሰን መካከል መሆኑን በመግለጽ ሰላማዊ ሰዎች ያለስጋት የእለት ተእለት እንቅስቃሴያቸውን እንዲቀጥሉ " ሲሉ ተናግረዋል። @mehonmedia @mehonpodcast1

#የተማሪዎችድምጽ " ብዙ ልጆች ተቸግረዋል፡፡ የምግብ አገልግሎት ተከልክለናል " - የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ኢንትርን ሀኪሞች " ጥያቄያቸው ይቅረብና ፍትሃዊ ከሆነ እናያለን፡፡ የሚመለከተው አካል ለምን እንዳላስተናገደም የምቀጣ ይሆናል " - ዩኒቨርሲቲው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ 6ኛ ዓመት የህክምና ተማሪዎች፣ በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የምግብ አገልግሎት የሚሰጥ ሆኖ ሳለ እነርሱ ግን ምግብ መከልከላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ቅሬታቸውን አቅርበዋል፡፡ ቅሬታቸውን ለተማሪዎች አገልግሎት ቢያቀርቡም መፍትሄ በማግኘት ፋንታ " እናባርራችኋለን " የሚል ዛቻ እንደደረሰባቸው አስረድተው፣ "  ብዙ ልጆች ተቸግረዋል፡፡ የምግብ አገልግሎት ተከልክለናል " ነው ያሉት። ዩኒቨርሲቲውን የተቀላቀሉት 2010 ዓ.ም እንደሆነ ፤ በተለያዩ ችግሮች ሁለት ዓመታት የሚጠጋ ጊዜ እንደባከነባቸውና እንዳልተካካሰላቸው ገልጸዋል። በሌላ በኩል በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች መደበኛ ተማሪዎች ነጻ የህክምና አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ ሆኖ ሳለ እነርሱ ህክምና መከልካላቸውን አስረድተዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የተማሪዎቹን ቅሬታ ይዞ የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዚደንት ዶክተር መንገሻ አየነን አናግሯል። ዶክተር እሳቸው ጋር ምንም አይነት የቀረበላቸው ቅሬታ እንደሌለ ገልጸው፣ ለማን ቅሬታ እንዳቀረቡ ኢንተርን ሀኪሞቹ በድጋሚ እንዲጠየቁ አሳስበዋል፡፡ እሽ በማለት ቅሬታ አቅራቢዎቹን ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት አሳውቃችሁ ነበር ? ስንል ጠይቀናቸው በሰጡን ምላሽም፣ " ለዶክተር መንገሻ አልደረሰም፡፡ ለተማሪዎች አገልግሎት አቅርበናል " ብለዋል። ለምን ለዩኒቨርቲው ከፍተኛ አካላት እንዳላቀረቡ ሲያስረዱም፣ " የተማሪዎች አገልግሎት 'ይሄ ጉዳይ ከእኔ አልፎ ወደ ላይ ቢሄድ አውቶማቲካሊ ሴኔት ሰብስብቤ ፈርሜ አባራችኋለሁ' አለን " ብለዋል፡፡ " ቅሬታችንን ለዶክተር መንገሻም አላሳወቁትም ከታች ነው ያስቀሩት " ሲሉም አክለዋል፡፡ ቅሬታው ደርሷቸዋል የተባሉት አካላት ለጊዜ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆኑ ሲሆን፣ የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዚዳንት ቅሬታ አቅራቢዎቹ ቅሬታ ያቀረቡበትን ክፍል በመግለጽ በድጋሚ ስለጉዳዩ ጠይቀናቸዋል፡፡ ፕሬዚደንቱ መንገሻ (ዶ/ር)፣ የኢንተርን ሀኪሞቹ ቅሬታ ዩኒቨርሲቲው ያላወቀው ቅሬታ እንደሆነ አስረድተው፣ ጥያቄያቸውን ማቅረብ እንሚችሉ ጠቁመዋል፡፡ " ፕሮፌሰር የሺጌታ የሚባል ሲኢድ አለን ህክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅን ሙሉውን የሚመራ የፕሬዚዳንቱ ተወካይ ነው እዚያ ግቢ " ያሉት መንገሻ (ዶ/ር)፣ ' ፕሮፌሰሩን ይጠይቁ፡፡ እሱ ካልፈታላቸው ወደ እኔ ይመጣሉ ወይም ደብዳቤ ካላቸው ያምጡ " ብለዋል፡፡ " ጥያቄያቸው ይቅረብና ፍትሃዊ ከሆነ እናያለን፡፡ የሚመለከተው አካል ለምን እንዳላስተናገደም የምቀጣ ይሆናል " ሲሉ አክለዋል፡፡ (ጉዳዩ ከምን እንደደረሰ ተከታትለን መረጃ የምናቀርብ ይሆናል) @mehonmedia @mehonpodcast1

የፓስፖርት ክፍያ 5000ብር ገባ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ 550/2024 መሰረት ለመደበኛ፣ ለአስቸኳይ፣ ለእድሳት፤ ለጠፋ እና እርማት ፓስፖርት አገልግሎቶች ከነሃሴ 1 ጀምሮ 2016 ዓ/ም ተግባ
+1
የፓስፖርት ክፍያ 5000ብር ገባ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ 550/2024 መሰረት ለመደበኛ፣ ለአስቸኳይ፣ ለእድሳት፤ ለጠፋ እና እርማት ፓስፖርት አገልግሎቶች ከነሃሴ 1 ጀምሮ  2016 ዓ/ም ተግባራዊ የሚሆን የዋጋ ማሻሻያ ክፍያ ዝርዝር መደበኛ አዲስ ፓስፓርት 5,000 አስቸኳይ በ2ቀን 25,000 አስቸኳይ በ5 ቀን 20,000 የጠፋ ፓስፓርት እርማት የጠፋ መደበኛ 13,000 የጠፋ አስቸኳይ በ2 ቀን 33,000 የጠፋ አስቸኳይ በ5 ቀን 28,000 የጠፋ እርማት ያለው መደበኛ 20,500 አስቸኳይ በ2ቀን 40,500 አስቸኳይ በ5ቀን 35,500 [የፓስፖርት እድሳቱን ከምስሉ ይመልከቱ] የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት @mehonmedia

#NBE ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ሊያካሄድ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ሊያካሄድ እንደሆነ በዛሬው ዕለት አሳውቋል። ይኸው ልዩ ጨረታ የአሜሪካ ዶላር ለሚፈልጉ ባንኮች ነው
+1
#NBE ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ሊያካሄድ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ሊያካሄድ እንደሆነ በዛሬው ዕለት አሳውቋል። ይኸው ልዩ ጨረታ የአሜሪካ ዶላር ለሚፈልጉ ባንኮች ነው። ጨረታው ነገ ነው የሚካሄደው። ፍላጎትት ያላቸው ባንኮች እንዲያመለክቱ ጥሪ ቀርቧል። እንደ ገበያው ሁኔታ ደግሞ በመጪዎቹ ሳምንታት ተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ሊወጣ እንደሚችል አሳውቋል። (ዝርዝር መረጃው ከላይ ተያይዟል) @mehonmedia

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን እያስመረቀ ነው። ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን ተማሪዎች እያስመረቀ ነው። አንጋፋው ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዛሬ የሚያስመርቃቸው ተማ
+4
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን እያስመረቀ ነው። ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን ተማሪዎች እያስመረቀ ነው። አንጋፋው ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዛሬ የሚያስመርቃቸው ተማሪዎች ቁጥር 8 ሺህ 524 መኾናቸውን ከዩኒቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት መንገሻ አየነ (ዶ.ር) ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች፣ መምህራን፣ ተመራቂ ተማሪዎች፣ ተጋባዥ እንግዶች እና የተመራቂ ወላጆች ተገኝተዋል። @mehonmedia

#የደመወዝ_ጭማሪ " ታች ላለው የመንግስት ሠራተኛ 300 እጥፍ ደመወዙን ጨምረናል " - ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ መንግሥት ሠራተኛ የደመወዝ ጭማሪ ምን ተባለ ? ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)
#የደመወዝ_ጭማሪ " ታች ላለው የመንግስት ሠራተኛ 300 እጥፍ ደመወዙን ጨምረናል " - ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ መንግሥት ሠራተኛ የደመወዝ ጭማሪ ምን ተባለ ? ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር። በዚህ ማብራሪያቸው በሪፎርሙ በዋጋ ንረት ምክንያት ሊጎዱ ይችላሉ / ሪፎርሙ በትሩን ሊያሳርፍባቸው ይችላል ተብሎ ከተለዩት የመንግሥት ሠራተኞች ዋነኞቹ ናቸው ብለዋል። በመሆኑም ዝቅተኛ  የሆነ ወርሃዊ ደመወዝ ለሚበሉት ሠራተኞች ከፍተኛ የደመወዝ ማሻሻያ ይደረጋል ሲሉ ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ፦ " መንግሥት በወር 1,500 ብር የሚበላ ሠራተኛ አለው። የአሁኑ ደመወዝ ማሻሻያ ከ90 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ ሃብት ጠይቆናል። ለዚህ ምን አይነት መንገድ ተከተልን ታች ያለው 1,500 ብር የሚበላው የመንግስት ሠራተኛ 300 እጥፍ ደመወዙን ጨምረናል። ይህ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ አይታወቅም። ላይ ያለው ከ25 ሺህ በላይ ያለውን ለጊዜው ታገሰን አልነው። ደመወዝ የጨመርነው ታች ለሚጎዱት ይሄ ሪፎርም ለሚጎዳቸው ሰዎች በርከት ያለ ሃብት ጨምረን ትንሽ ሻል ሻል ያለና ለተወሰነ ጊዜ ጫናውን ለሚቋቋሙት አቆየን  ይበቃቸዋል ማለት አይደለም እነሱም ቢሆኑ ፤ በንጽጽር ግን በጣም እያለቀሰ የሚያድረውን ሠራተኛ ማገዝ አለብን ነው። ተሿሚዎች ብዙ ላያገኙ ይችላሉ። ታች ግን አድርገናል። " @mehonmedia

#National_GAT የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ የሚካሔደው ከሐምሌ 24/2016 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 05/2016 ዓ.ም መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። በመሆኑም
#National_GAT የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ የሚካሔደው ከሐምሌ 24/2016 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 05/2016 ዓ.ም መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። በመሆኑም በ2017 የትምህርት ዘመን በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ያላችሁ አመልካቾች የመመዝገቢያው ቅጽ ላይ የተዘረዘሩት መስፈርቶችን በሟሟላት በተጠቀሰው ጊዜ መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል። ለመመዝገብ 👇 https://NGAT.ethernet.edu.et @mehonmedia

#Contractual_Agreement ትምህርት ሚኒስቴር ከሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ለ2017 ትምህርት ዘመን የአፈጻጸም ውል ስምምነት በመፈራረም ላይ ይገኛል። ትምህርት ሚኒስቴር ባለሙያዎች
+2
#Contractual_Agreement ትምህርት ሚኒስቴር ከሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ለ2017 ትምህርት ዘመን የአፈጻጸም ውል ስምምነት በመፈራረም ላይ ይገኛል። ትምህርት ሚኒስቴር ባለሙያዎችን በመመደብ የሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎችን የ2016 ዓ.ም ቁልፍ ውጤት አመላካቾች (KPIs) አፈጻጸም ላይ ውይይት እያደረገ ነው። ውይይቱን ተከትሎ ሚኒስቴሩ ከዩኒቨርሲቲዎቹ ጋር የአፈጻጸም ውል ስምምነት ፊርማ (Contractual Agreement) ለ2017 ትምህርት ዘመን እየተዋዋለ መሆኑም ታውቋል። @mehonmedia