en
Feedback
AMAN አማን

AMAN አማን

Open in Telegram
1 125
Subscribers
No data24 hours
+27 days
-4830 days
Posts Archive
☆Anahira☆ 🎀 ክፍል 18 ☆ከሳጥን ውስጥ ፋሻ እና ቁስል ማድረቂያ አውጥቼ በዞረበት አቅጣጫ ሄጄ ተቀመጥኩ ትራሱን በግማሽ ጎኑ ተንተርሶ ተኝቷል ቀኝ እጁን እያነሳሁ <<አላህ ባሮቹን በንብረቶቻቸው፣ በገንዘባቸው(በንግዳቸው ላይ ክስረትን ውድመትን) ፣ በቤተሰቦቻቸው ፣ በወዳጆቻቸው ባላቸው ነገር በሙሉ ይፈትናቸዋል በእሱ አታምንም>> አይን አይኔን እያየ ዝም አለ <<በፈተናዎች ውስጥ ደግሞ ያለፉትን ያለፈ ወንጀላቸውን ይምርላቸዋል>> ከአይኖቹ እንባ መፍሰስ ጀመረ <<والله يحب الصبرين አላህም ትዕግስተኞችን ይወዳል የሚለውን አያ አስታወስከው?>> እጁን ሊነጥቀኝ ሞከረ ቁስሉ ተሰምቶት ይመስለኛል <<ይገባኛል የተፈጠረውን በምንም  ልንቀይረው አንችልም ግን ሷብር ብናደርግ አንከስርም ወደ ፊት ብዙ ቀናት አሉ በእነዛ ውብ ቀናት እሷም አብራን ብትኖር ደስ ይለኝ ነበር ግን ደግሞ አላህ አላለም እሱ የወደደውን የፈቀደውን አደረገ እ……… ይጎዳል ይገባኛል እናትን ማጣት ያሳዝናል ግን እንደዚህ አትሁን? እ…? እኔ እኮ ቅድም ስላላለቀስክ ደህና መስለኸኝ ነበር>> <<ሁለት አመት ሙሉ በድብቅ ትከታተለው  የነበረ ህክምና መኖሩን ሳውቅ አቅም አጣሁ እንደምትሞት ቀድማ ታውቅ ነበር ለምን አልነገረቺኝም? ትክክለኛ ልጅ ስላልሆንኩ አይደል? አንድ ቀን ለስራ እንጂ ለእሷ ጊዜ ሰጥቻት ስለማላውቅ አይደል?>> ድንጋጤዬን ለመደበቅ እየሞከርኩ <<ለምን እንደዛ ታስባለህ እሷ እኮ ለአንተ አስባ ነው ያልነገረችህ>> ተነስቶ ትራሱን እያቃና ተቀመጠ <<ደህና አይደለሁም ዝምታዬ ደህና መሆኔን እያስመለከተ ቢያስዋሸኝም……… በጣም ከፍቶኛል ሚንሃ ይሄ ነው የማልልሽ ህመም እንደዛ ተቆፍሮ የተከመረው አፈር በሙሉ በእናቴ ላይ መጫኑን ሳስብ አቅም አጣለሁ በቃ አልችልም>> ትከሻውን ተንተርሼ <<ሁሉም ሰው አልችልም ብሎ በሚያስበው ነገር ላይ ሁሉ ተፈትኗል ከፈተናው ጋር ችሎታን የሚሰጥ ጌታ አለ አላህ እስከፈቀደው ጊዜ ድረስ ደግሞ አብሬህ ነኝ እሺ?……>> ፈገግ ለማለት እየሞከረ <<እንድረጋጋ የሚያደርገኝም ብቸኛው ነገር እሱ አይደል?>> ግንባሬን ሳመኝ                ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~                ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ረፋዱ ላይ ኢርቫ በስልክ መስመር:- <<አሰላሙ አለይክ ሃቢብ>>አለችው <<ወአለይኪሰላም አክስቴ>> <<እንዴት ነህልኝ?>> <<አልሃምዱሊላህ እንዴት ነሽ አክስቴ?!>> <<አልሃምዱሊላህ መጥተናል ልትቀበለን ትችላለህ? ከመጣሁ ስለቆየሁ አንዳንድ ነገሮች ተቀይረውብኛል>> <<መርሃባ አሁን እመጣለሁ>> ብሏት ወደ እኔ ዞረ <<አዚዘቲ አክስቴ የአቢ እህት መጥታለች ሄደን ብንቀበላትስ?>> <<እሺ ልብስ ልቀይር>> ከደቂቃዎች በኋላ ወደ ቦሌ አየር ማረፊያ ሄድን አክስቱ አሚራ ከሁለት ልጆቿ ጋር ሻንጣዋን ይዛ ጠበቀችን ወንድ ልጇ ከኢርቫ በለጥ ይላል 29 አመቱ ሲሆን ሴት ልጇ ደግሞ 20 አመቷ ነው የአሜሪካ ተወላጆች ስለሆኑ አራርቆ መውለድ የሚለው ሃሳብ በእነሱም ላይ ተጽዕኖ እንደነበረው ግልፅ ነው እናታቸው በአባቷ ቁጥጥር የበዛበት ሁኔታ ውስጥ ስላደገችበት የኖረችበትን እና እስልምናዋ ላይ ማሻአላህ ናት እነሱ ደግሞ የእሷ ተቃራኒ ሴት ልጇን በሱሪ ነበር የተቀበልናት መንሱረት ትባላለች ወንድ ልጇ ደግሞ አይመን አይመን እና ኢርቫ ከፊት ሆነው እኛ ሶስታችን ደግሞ ከኋላ ተቀምጠን ቤት ደረስን ያው የሚያርፉት እኛ ጋር ነው እናት እና ልጅ እያወሩ እኔን ዘንግተውኝ ነበር ብቻ ቤት ስንደርስ ነው ማንነቴ የታወቀው ክፍሎቻቸውን አሳይቻቸው ምግብ ላዘጋጅላቸው ሄድኩኝ ግን አሁን ፕሌን ውስጥ በልተናል እንቅልፍ ስለተዛባብን እንተኛ ነበር ያሉኝ እሺ ብዬ ወደ ክፍሌ ገባሁ ኢርቫ ደግሞ አክስቱ እና አባቱ በልጆቿ ምክንያት መጋጨታቸውን እየነገረኝ እንዳለ መታጠቢያ ቤቱን የሚጠግኑ ባለሞያዎች መጡ ስለዚህ ወጣ ብለን እንመለሳለን ብሎኝ ወጣን በጣም ደስ ብሎኝ ነበር ከምንም በላይ ኢርቫ የሚያነሳቸውን ሃሳብ ስሠማ እና ተቀይሯል አሁን አንድ ከመንደራችን ያልወጣ ካፍቴሪያ ውስጥ ፒዛ አምሮኝ ነበር ፒዛ እና ሻይ አዘን መብላት ጀመርን <<ገዝተን እንውሰድላቸው እንዴ መጨረሻ ላይ ስንሄድ? ካሰብኩት በላይ የሆነ ፒዛ ነው>> <<እሺ እንይዝላቸዋለን>> አልኩት <<እህት……… አስተናጋጅ … አንድ ፒዛ ጭማሪ ፈልገን ነበር ልታዘጋጂልን ትችያለሽ?>> <<እሺ>>አለች እሷም እየበላን እንዳለ በመሃል ኢርቫ <<ወንድም አይንህን ንቀል እንጂ?>> ብሎ ከተቀመጠበት ተነሳ የሆነ ግርግር ልበላችሁ ብቻ እንደዛ አይነት ወከባ ነገር ፈጠረ ልጁም <<ኧረ አባት እኔ ማንንም አላየሁም>> ሰው ወዳለበት መሰብሰብ ሲጀምር <<ኢርቫ አላህን ፍራ እንጂ  ምን እያደረግክ ነው?>> <<እያየሽ ነበር ለምን ያይሻል? ምንድነው የፈለገው?>> አብዛኛው  ጊዜ ስሜት ምክንያታዊ አልሆን ስለሚል ታዛቢ ያፈራል ሳቄ ደርሶ እየተናነቀኝ <<እ እ እ? ነው እንዴ? በቃ የካፌውን እቃ በሙሉ ከጥቅም ውጪ አድርገው መስታውቱን እዚህ ደግሞ ጠረጴዛ እና ወንበርም አለ የቡና ማሽን አለ የወተት ፍሪጅ…………ቆይ ምን ነክቶሃል? በሰላም ተጠቅመን ብንወጣ ምን አለበት?>> <<ቀለድሽ በቃ?>> <<አልቀለድኩም እሱ አላየህም እያለህ ከዛ በኩል የተቀመጡት ሶስት ሴቶች እንኳን ባንተ እየፈረዱ አንተ ተነስተህ ልደባደብ ስትል ያሳፍራል ኢርቫ ምን ሆነሃል?>> <<ታውቂዋለሽ?>> አለኝ <<አስተغፊሩላህ………ወደ ራስህ ተመለስ>> <<የት ነው የተዋወቃችሁት?>> ለሚናገረው ሁሉ ችላ አልኩት አናደደኝ አውቆ እየሆነ ያለው ነገር አበሸቀኝ <<እህት ፒዛውን ጨረስሽልኝ? እሺ ሂሳብ ስንት ነው?>>  ፒዛችንን ይዘን ከካፌው ወጣን  ቤት ስንደርስ ጠጋኞቹ ጨርሰው ሄደዋል እንግዶቻችንም አልተነሱም ድርሻቸውን ላስቀምጥ ወደ ማዕድ ክፍል ስገባ መንገድ ላይ ዝም ያለው ኢርቫ እየለፈለፈ ተከተለኝ <<ንገሪኝ እንጂ የት እንደምታውቂው?>> ዝም አልኩት በቃ ይረጋጋል ሁለታችንም ካወራን ጥሩ አይመጣም ብዬ ግን ለውጥ አልነበረውም <<ኢርቫ አላህን ፍራ እኔ የትም እንደማላውቀው ሁለታችንም እናውቃለን ለምንድነው እንደዚህ አይነት ጥያቄ የምትጠይቀኝ?>> <<በጣም ተከራከርሽለት አልመሰለሽም?>> <<እሺ አንተ እንደፈለግክ አስበው አይመለከተኝም>> <<ለምን? ራስሽ ባመጣሽው ችግር አያገባኝም ስትዪ ትንሽ አታፍሪም ሃያዕ ይኑርሽ እንጂ አንቺ እንደዛ በሆነው ባልሆነው ስትስቂ…>> ንግግሩን ሳላስጨርሰው ትቼው ወደ ክፍሌ ሄድኩ እና ጋደም አልኩ እንባዬ ደርሶ እየተናነቀኝ ነበር አልቆየም መንታ መንታ ሆኖ መውረድ ጀመረ ሰላም እንደማጣት አልያም በጭቅጭቅ ውስጥ እንደመኖር የሚመር ምንም ነገር የለም  እናቱ እንዲህ እንደሚሆን አውቃ ነበር ማለት ነው እንዳትርቂው ያለቺኝ በዚህ ሁኔታ እኮ አንድ ሌሊት በሰላም ማደር አንችልም             10 🥰 ይቀጥላል☆ ☆ ☆. . . .

" ሙሉ ውጤታችን Disqualified ተደርጓል " ያሉ በርካታ የ2018 ዓ.ም #REMEDIAL ተማሪዎች  ቅሬታ አቅርበዋል። ተማሪዎቹ " ይፋ በተደረገው የፈተና ውጤት ላይ የገጠመን ከፍተኛ ችግር እንዲሰማልን እንፈልጋለን " ብለዋል። ቅሬታቸውን ካቀረቡት መካከል በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳንይንስ ተማሪዎች ውጤታቸው " ሙሉ በሙሉ Disqualified " የተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪ፥ በደብረ ብርሃን፣ ወሎ፣ አርባ ምንጭ፣ ሚዛን ቴፒ፣ ሰመራ፣ ባህርዳር፣ ወልቂጤ፣ ኦዳ ቡልቱም፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ የተለያዩ ተማሪዎች ውጤት ላይ ተመሳሳይ ችግር እንደገጠማቸው አመልክተዋል። ትምህርት ሚኒስቴር ቅሬታቸውን ተመልክቶ ምክንያቱን በመለየትና በማሳወቅ እንዲሁም በመመርመር አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና 53,620 ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል። https://t.me/HayatAcademyy

Repost from N/a
ሰበር ዜና የ2018 ሪሜዲያል ውጤት ተለቋል የ ሬሜዲያል ዉጤት Offical ተለቋል Link:-https://result.ethernet.edu.et @addisentrancehub
ሰበር ዜና የ2018 ሪሜዲያል ውጤት ተለቋል የ ሬሜዲያል ዉጤት Offical ተለቋል Link:-https://result.ethernet.edu.et @addisentrancehub

☆Anahira☆ 🎀 ክፍል 17 ☆የሰሊመት ጀናዛ ተቀብሮ ቀባሪዎች ተመልሰዋል አሁንም ኢርቫ ላይ ፍፁም እርጋታ እንጂ ሃዘን አይነበብም <<እንዴት ነው ግን እሱ ደህና ሊሆን የቻለው?>> አልኳት ለአትሮኖስ <<ደህና እንኳን አይደለም ዝም ስላለ ደህና ነው ማለት አይቻልም ያንቺ ስቃይ አሁን እየጀመረ ነው>> <<ማለት?>> አልኳት ቅምሻ መቅደም ስላለበት የቴምር ካርቶን እየፈታን ነው ኡሚ እና ሌሎች ጓደኞች ምግብ እያዘጋጁ ነው <<ማለትማ ቤት ውስጥ ሰላም አይኖርሽም ምንም እንዳልሆነ እያስመሰለ ነው>>አለቺኝ ለምን እንዲህ እንደሆነ አላህን መጠየቅ ማቆም አልቻልኩም ከምንም በላይ ያለቺኝን ባሰብኩ ጊዜ ኢርቫንን አልወደውም ብዬ ያባከንኳቸው ቀናት ቆጩኝ ቢያንስ በአላህ እዝነት ይህቺ እናት የልጅ ልጇን አይታ ነበር ከበር ለሚገቡት ቴምር እና ውሃ እየሰጠሁ ስቀበላቸው ቆይቼ ይህን ሳስብ ግን ራሴን መሆን አቃተኝ አትሮኖስ ውሃ እና ቴምሩን ተቀብላኝ እንድሄድ ነገረቺኝ <<ሂጂ በቃ ወደ ክፍልሽ ሂጂ>> ብዙ ከማልቀሴ የተነሳ ራስ ምታት ጀምሮኛል ወንዶቹን ሲያስተናግድ የነበረው ኢነብ መጥቶ <<ሚንሃ አላህን ፍሪ እንጂ ከመወለዳቸው በፊት አባታቸውን አጡ💔 በስድስት አመታቸው እናታቸውን አጡ💔 በስምንት አመታቸው አያታቸውን አጡ💔 ማንም ባላመናቸው ሰዓት ያመነቻቸው ሚስታቸው ኸዲጃን አጡ💔 የኛ ነብይ عليه سلام ይህን ሁሉ ሆነው ነበር ከጠማማዎች በስተቀር [{ከጌታው እዝነት የሚቆርጠው ማነው???}]>> ብሎ የቁርአን አያ አስታወሰኝ <<ማንም ማ……ን ማንም ነው?>> አልኩት እና ተቃቀፍን <<ኢርቫንን እንኳን እይው እናቱን አጥቶ በዚህ ደረጃ ሷብር አድርጓል>> ብሎ ከርቀት አሳየኝ ""ከሳምንታት በፊት ምርቃት ነበር ቀናት በፊት እኮ እዚህ ቤት ሰርግ ነበር አሁን አየሽ??? በልኩ ስላልተደሰቱ ገንዘባችንን በድግስ ወጪ እዩልኝ ስላሉ አሁን ደርሶ አልቃሽ አደረጋቸው'""" አያቴ እና የአያቴ ጓደኛ የሚያወሩትን ነገር ሰምቼ ገረመኝ ኢላሂ የሰው ልጅ ኢላሂ የአደም ልጅ ሞትን አይቶ እንኳን አይማርም? አያዝንም? የእድር አባላት የሰፈር ሰዎች በቃ ቤተ ዘመድ ተሰብስቦ በየራሱ የአፍም ሆነ የእጅ ስራ ተጠምዷል ይህም ቀን እለት ተብሎ እለትን ሆኖ መሸ እንድናድር ቢለምኑንንም ኢርቫ አናድርም ካልሄድን ብሎ ችክ አለ የእናቱ ሞት ባህሪውን አንድ በአንድ ቀይሮታል ማለት ይቀላል ከወላጆቼ ቤት ኢሻን ሰግደን ከምሽቱ 03:45 ወጥተን ራሳችን ቤት ደግሞ 04:10 ደረስን እኔ ለአይን የሚይዘውን ጨለማ በመኪናው መስኮት እያየሁ እና እያነባሁ ነገር የደረስነው ዝም ተባብለናል በቃ ዝምታ ረጅም ዝምታ ኢርቫ ደግሞ ሃዘን ሳይሆን እልህ በፊቱ ላይ ይነበባል ክፍላችን እንደገባን የከባድ ሚዛን ተፋላሚዎች የbox ring ውስጥ ከሚያደርጉት ትንቅንቅ ያልተሻለ ልፊያ ጀመረ <<ኢርቫ ልቀቀኝ…… ተውውውውው ኢርቫ ልክክክ አልመሰልከኝም ልቀቀኝ>> <<የዛሬው ቀን እንዳልተፈጠረ መርሳት እፈልጋለሁ>> <<ታዲ…ያ በዚህ መን…ገድ እኮ አይደለም በዱዐ ነው >> ከት ብሎ እየሳቀ ትቶኝ ወደ መታጠቢያ ክፍል ገባ ልብሴን አስተካክዬ ተቀመጥኩ ልቤ በፍርሃት ከቦታዋ ልትወጣ ምን እንዳገዳት ባላውቅም ሽምጥ እንደ ፈረስ መጋለብ ከጀመረች ቆየች አቢ ጋር ስለመደወል አሰብኩ እና ስልኬን ሳነሳው ከመታጠቢያ ክፍል የመስታውት መሰበር ድምፅ ተሰማኝ ቀጥ ድርቅ ብዬ ቀረሁ አሁንም ሲደገም ሄድኩ እጄ እየተንቀጠቀጠ የበሩን እጀታ ተጭኜ ስከፍተው አንድ የተረፈ እቃ አልነበረም ድቅቅ ያለ ቢሆን እንጂ የእጅ መታጠቢያ ገንዳው ተሰብሮ ወድቋል ስባሪውን አንስቶ ወደ መስኮቱ ሲወረውረው መስኮቱ ሙሉ ለሙሉ ረገፈ ፈራ ተባ እያልኩ <<ኢርቫን ምን እያደረግክ ነው?>> አልኩት ባልሰማ ፀጥ ብሏል ቀጥሎ   ፎጣዎች የሚደረደሩበትን ሳጥን ገነጠለው እና ዞረ <<ምን አልሺኝ?>> ሲለኝ ከመፍራቴ የተነሳ <<ም………ምን…ም>> አልኩት ሌላ ኢርቫ ሆነ <<የሆነማ ያልሺኝ ነገር ነበር…ጤነኛ አይደለህም አይደል ያልሺኝ?>> <<ኧረ እኔ እን…ደዛ አላልኩም>> <<ምን እያደረግክ ነው ማለት ምን ማለት ነው ታዲያ?!ኧ…? ትክክለኛውን ነገር ነው ያደረግኩት>> ሲጮህ ያየሁት ለመጀመሪያ ጊዜ ስለሆነ ይሁን እስከ ዛሬ የማውቀው ዝምታውን ስለሆነ ይሁን አላውቅም ግን ግራ ገባኝ የቆመበት ቦታ ላይ ደም ሲንጠባጠብ አስተዋልኩ ብደነግጥም ምንም እንዳልተፈጠረ ለመሆን እየሞከርኩ <<እሺ………አዎ ትክክለኛውን ነገር ነው ያደረግከው እ…… አሁን እጅህን ልይልህ ጎድተኸዋል መሰለኝ>> <<አስመሳይ>> ብሎኝ ከመታጠቢያ ክፍሉ ወጣ የመታጠቢያ ክፍሉን ሳየው እንባ እንባ አለኝ ይህን እንዲህ አድርጎ እያየሁ ዛሬን በሰላም እንቅልፍ በራሱ እንደማይወስደኝ ተሰማኝ ከመቼውም በላይ ፈራሁ በረጅሙ እየተነፈስኩ ዘጋሁት እና ስዞር ከጀርባዬ ቆሟል ክው ነበር ያልኩት <<አላሁ አክበር……… ኢርቫ ያምሃል እንዴ?……… ኢብሊስ ምን ትሰራለህ? ይህን ሁሉ ማድረግህ ሳያንስ……ቆይ አታስብም? አንተ እንቅልፍ የሌለህ እንደሆነ ሌላው መተኛት የለበትም ጎበዝ ይኸው ቁም ሳጥኑም አለልህ ትንሽ አለፍ ስትል ደግሞ መልበሻ መስታወቱ አለልህ እ ……ሌላ ደግሞ ሌላ ደግሞ ምን አለ መሰለህ? የእኔን ቁመት የሚያክሉ የሽቶ ጠርሙሶችም አሉልህ ሌላ የምታበላሸው እቃ ትፈልጋለህ?……ከጥቅም ውጪ የምታደርገው>> ፈገግ እያለ <<ባደርገው ጥሩ ነበር ግን ብሰብራቸውም ከጥቅም ውጪ ባደርጋቸውም ከጥቅም ውጪ የሆነውን ልቤን አይመልሱልኝም ልቤን አይጠግኑትም……ገባሽ?>> ወደ አልጋው ሄዶ ተኛ ምንም አልተሰማውም ያልኩት ውሸት ነው ማለት ነው? <<እጅህን ልየው?>> <<ደህና ነኝ>> ከሳጥን ውስጥ ፋሻ እና ቁስል ማድረቂያ አውጥቼ በዞረበት አቅጣጫ ሄጄ ተቀመጥኩ 10🥰 ይቀጥላል☆ ☆ ☆. . . . .

photo content
+2

Repost from N/a
የ12ኛ ክፍል ቅሬታ ምላሽ መሰጠት ጀምሯል፤ የሚዘዋወረው መቁረጫ ነጥብ ሐሰተኛ ነው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. እንደገለጸው፣ በ2018 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ውጤታቸው ላይ ቅሬታ ላቀረቡ ተፈታኞች ምላሽ እየተሰጠ ነው። በስልክ ወይም በአጭር የጽሑፍ መልእክት ቅሬታ ያቀረቡ በዚያው መንገድ ምላሽ አግኝተዋል፤ በበይነ መረብ ያቀረቡ ደግሞ ውጤታቸውን ባዩበት ቦታ ምላሹን ማንበብ ይችላሉ። በቁጥር የተወሰኑ ቅሬታዎች ገና በሂደት ላይ በመሆናቸው አገልግሎቱ እነዚያ ተፈታኞች እንዲጠባበቁ ጠይቋል። በዚያው መግለጫ ላይ በአንዳንድ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች የሚዘዋወረው የ12ኛ ክፍል መቁረጫ ነጥብ ሐሰተኛ መሆኑንና ትክክለኛውን አጣርቶ እንደሚያሳውቅ አክሏል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ቅሬታ ምላሽ እየሰጠ መሆኑን ገልጿል የቅሬታዎ ምላሽ የሚደርስዎት የት ነው? ምላሹ የሚመለሰው በላኩበት መንገድ ነው። በስልክ ወይም በአጭር መልእክት የቀረበ ቅሬታ በስልክ ወይም በአጭር መልእክት ይመለሳል። በበይነ መረብ የቀረበ ደግሞ በበይነ መረብ ይመለሳል፤ ይኸውም result.eaes.et ላይ ባለው የራስዎ የውጤት ገጽ ውስጥ My Complaints በሚለው ሥር ነው። የሚኬድበት ቦታም የሚደወልበት ስልክም የለም። 01 ምላሾቹ የሚመለሱበት መንገድ በስልክ ወይም በአጭር የጽሑፍ መልእክት ቅሬታ ያቀረቡ ተፈታኞች በስልክ ወይም በአጭር መልእክት ምላሽ ተሰጥቷቸዋል፤ አገልግሎቱም እነዚህ ምላሾች አሁንም እየተሰጡ መሆናቸውን ገልጿል። በበይነ መረብ ቅሬታ ያቀረቡ ተፈታኞች ምላሻቸውን የሚያገኙት በበይነ መረብ ነው። መግለጫው ይህን የሚያስቀምጠው ውጤትዎን ባዩበት መልኩ በ eaes.et ድረ ገጽ ላይ ማንበብ እንደሚችሉ ነው፤ በተግባር ግን result.eaes.et የተባለው የውጤት ገጽ ማለት ነው፦ ከመነሻ ገጹ በመግቢያ ቁጥርዎና በስምዎ ይግቡ፣ የራስዎን የውጤት ገጽ ይክፈቱ፣ ከዚያም My Complaints የሚለውን ይጫኑ። የ12ኛ ክፍል ውጤት ቅሬታ እንዴት እንደሚቀርብ ተመሳሳዮቹን ገጾች አንድ በአንድ ያሳያል፤ ገና ካላቀረቡ ማንበቡ ይጠቅማል፤ ምክንያቱም ማቅረቢያው ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ሰኞ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ይዘጋል። አንዳንድ ቅሬታዎች ገና ውሳኔ አላገኙም። አገልግሎቱ በቁጥር የተወሰኑት አሁንም በሂደት ላይ መሆናቸውን ገልጾ፣ እነዚያ ተፈታኞች ደግመው ከማቅረብ ይልቅ እንዲጠባበቁ ጠይቋል። 02 የሚዘዋወረው መቁረጫ ነጥብ እውነተኛ አይደለም ጥንቃቄ አገልግሎቱ ምንም መቁረጫ ነጥብ አላወጣም አገልግሎቱ እንዳለው፣ በአንዳንድ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች የሚዘዋወረውና የ2018 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆኗል የሚለው መልእክት ሐሰተኛ ነው። አገልግሎቱ መቁረጫ ነጥብ አላወጣም፤ ትክክለኛውን መረጃ አጣርቶ በቅርቡ እንደሚያሳውቅም ተናግሯል። አገልግሎቱ የትኛውን ቁጥር እንደተናገሩበት አልገለጸም። ገና ያልወጣው የሬሜዲያሉ መቁረጫ ነጥብ ነው፦ ሚኒስትሩ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. እንደተናገሩት፣ ዘንድሮ ያለፉት ተማሪዎች ስለበዙ የሬሜዲያል መቀበያ ቦታዎች ያንሳሉ፤ የሚወስነው ነጥብም ወደፊት ይገለጻል። ይህም የ12ኛ ክፍል ውጤት መቼ እንደሚደርስ ላይ ተቀምጧል። ሚኒስቴሩ እስከሚያሳውቅ ድረስ የሬሜዲያሉ መቁረጫ ነጥብ ነው ተብሎ የሚቀርብ ማንኛውም ቁጥር የተፈጠረ ነው። 03 ብቸኞቹ ይፋዊ አድራሻዎች result.eaes.et፤ ውጤትም የቅሬታ ምላሽም የሚገኙበት @eaesbot የተባለው የቴሌግራም ቦት ወደ 6284 የሚላክ አጭር መልእክት

☆Anahira☆ 🎀 ክፍል 16 ☆…በረጅሙ ተንፍሶ ንግግሩን ዘጋው <<በዱዐ ነው ዚክር አብዛ እንደዚህ መፍራት ጥሩ አይደለም አላህ ያሻውን ሰሪ በሆነው ጌታ ላይ እምነት ይኑርህ እንጂ ግን እናቴ ጋር በመሄድህ ደስ ብሎኛል እኔም ዛሬ እዛ ነበር የዋልኩት ደግሞ አንተ የሚያሳዝናትን ነገር እኮ እኔ ሳውቅ አድርገህ አታውቅም እንደዚህ አትፍራ>> <<እሺ ግን እስከ ሚነጋ መጥፎ ነገር ባልሰማን ብለሽ ዱዐ አድርጊ>> ግራ ገባኝ ምን እውነትም ከልቡ ፈርቷል እያቀፍኩት <<ኢንሻአላህ ምንም አይፈጠርም ቢፈጠርም ከውብ ነገሮች ሁሉ ውብ ሷብር ነውና ሷብር>> እሱም ግንባሬን እየሳመኝ <<መርሃባ አዚዘቲ ………ታውቂያለሽ? እኔ አላህን በምንም ባመሰግነው አንቺን እንደሰጠኝ ያህል ግን አላመሰግነውም አንቺ ማለት እህቴ ወንድሜ ጓደኛዬ ፍቅሬ ከምንም በላይ ሚስቴ ልጄ ማለት ነሽ በምንም ይፈትነኝ ባንቺ ግን ሁሌም አደራ እለዋለሁ ላጣሽ አልፈልግም>> <<እኔም>> አልኩት በዚህ መልኩ እንቅልፍ ከወሰደን ብዙም ሳይቆይ ከሌሊቱ 08:31 ላይ የኢርቫ የስልክ ጥሪ አነቃን ኢርቫ ግን በእንቅልፍ ሳቢያ የተጨፈኑትን እና አልገለጥ ያሉ አይኖቹን ጭፍን ግልጥ እያደረገ <<ማንሳት አልቻልኩም አንዴ ስልኩን አንሺልኝ>> እያነሳሁት ሳየው አቢ በሚል የአረብኛ ፅሁፍ save የተደረገ ስልክ ነው <<አባቴ ነው አናግረው>> እየተቀበለኝ <<ሄሎ አቢ አሰለሙ አለይክ?…………ምነው አቢ በሰላም ነው >> <<ወአንተ ሰላም ልጄ እናትህ………>> <<እናቴ ምን?………ኡሚዬ ምን ሆነች?>>ተስፈንጥሮ ከአልጋው ሲወርድ አብሬው ወረድኩ ገና እኮ ሶስት ቀናት ነበሯት አለቺኝ ልቤ <<አላ……ውቅም እ……ብቻ እንድትመጣ እፈልጋለሁ ድንገት ታማብን ሆስፒታል አስገብተናታል>> ኢርቫ ቁም ሳጥኑን ከፍቶ የሚለብሰውን ለማውጣት ማተረማመስ ይዟል ከሳጥኑ እያገለልኩ አልጋ ላይ አስቀመጥኩት እና ለሁለታችንም የሚሆን ልብስ ማውጣት ጀመርኩ ያለማቋረጥ ዚክር ሳደርግ ነበር <<እሺ መ……መጣሁ እዛው ጠብቀኝ በቃ>> ብሎ ዘጋው እና ድንብርብር እያለ <<ይህን ይሁን እንዴ ትላንት እንደዛ አድርጎ ያሳየኝ?>> ጀለቢያውን እንኳን በትክክል መልበስ አልቻለም እኔ ያወጣሁትን አባያ ለብሼ ስለጨረስኩ እሱን ወደ መርዳት ገባሁ ያለማቋረጥ ይለፈልፋል <<ኡሚን……ግንኮ ትላንት ሳገኛት ደህና ነበረች ምን ነክቶብኝ ይሁን?>> <<አይዞህ ምንም አትሆንም>> ድንገት እውነታውን ስለማውቅ እንባዬ መርገፍ ጀመረ <<አዚዘቲ ሞታለች እኮ አልተባልንም አታልቅሺ>>አለኝ ግን ትሞታለች ከደረስንባት ነው እሱንም አለች ልቤ ተስፋዋ ደቅቋል ተያይዘን ወጣን እሱ መኪና መንዳት እንደማይፈልግ ነግሮኝ በእኔ አሽከርካሪነት ሆስፒታል ደረስን ሙሉ ቤተሰቤን እዛ ነበር ያገኘሁአቸው ሁሉንም  ነገር ሰምተዋል ማለት ነው ኢርቫ እንደደረሰ አባቱን እና አባቴን በየተራ አቀፋቸው መረጋጋት እንዳለበት ነገሩት እሱም ደህና ነበር ያን ያህል አልደነገጠም አልፎ እነሱን ሲያረጋጋ ቆየ ከ02:00 በኋላ የቀጠሮው ቀን የተዋወቅኳት የሰሊመት ዶክተር ከቀዶ ጥገናው ክፍል እየወጣች <<ቤተሰቦች እ………ትንሽ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ በመሆኗ እስኪ ሃጂ መርዋን እና አቶ ኢርቫ ገብተው ይዩአት>> አለች በቃ እንደማትድን ሁሉም ነገር ይታየኝ ጀመር ግን በዛ ሁሉ ሰው መሃል ስሜታዊ ሆኜ የማውቀውን ነገር ማጋለጥ አልፈለግኩም <<አሽሃዱ አላኢላሃ ኢለሏህ>> እያለ መርዋን ከክፍሉ ወጣ በዛች ቅጽበት የሞተች መስሎኝ ነበር <<ሚንሃ እ……ትፈልግሻለች ገብተሽ እያት>> አለኝ አይኖቹን እያሻሸ ፈጠን ብዬ ስገባ ኢርቫ አንድ እጇን አጥብቆ ይዞ <<ምንም አትሆኚብኝም>> እያለ ይስማታል ስታየኝ የግዷን ፈገግ እያለች ቀኝ እጇን ዘርግታ <<መጣሽ?!!……ሚንሃ>> ቀኝ እጇን እየያዝኩ <<እ… አዎ መጥቻለሁ እናቴ>> እንባዬ ከአይኔ ሹልክ አለ ላስቆመው አልቻልኩም <<እ……የእናንተን ልጅ ማየት  ባለመቻሌ አዝናለሁ ግን ደግሞ የአላህ ተግባር ከእኔ እቅድ እና ሃሳብ በላይ ውብ ነው ሁሉም ነገር እኮ ከሁኔታው እና ከጊዜው አንፃር ነው እንጂ ውብ ነው………ስለዚህ ምናልባት እኔ መቆየት የለብኝም ይሆናል ያ ማለት ግን አልታደልኩም ማለት አይደለም አንድ ባሪያ ጌታውን መገናኘት የወደደ ባሪያ……>> <<ሞትን መፈለግ አለበት>> ብሎ ንግግሯን ጨረሰላት <<ስለዚህ ሞት ምንም አይደለም ማለት ነው ከአንድ አለም ወደ አንድ አለም የመሄድን ያህል ነው የህይወት መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ አይደለም ምናልባት ይህ ቀን የዱኒያ መጨረሻ የአኼራ ደግሞ መጀመሪያው እለት ይሆናል>> ኢርቫ እጆቿን ከመሳም ውጪ ምንም ነገር አላደረገም አለማልቀሱ ደግሞ በጣም ገርሞኛል እኔ እንባዬን የክረምት ዝናብ ያህል አወርደዋለሁ እናት እና ልጅ ግን ምንም አልሆኑም እየተቀባበሉ ሞትን አስታዋሽ ሃዲሶችን ያወራሉ እዷ ትጀምራለች እሱ ይጨርስላታል ምን አይነት መታደል ነው? አልኩ በልቤ መረጋጋት አልቻልኩም እነሱ ግን ቀጠሉ የማናቸውም ፊት ላይ ሃዘን አይታይም ደግመው የሚገናኙ ይመስል <<ልጄ እንዳታዝንብኝ እና ያንን ታሪክ እኮ አጫወትኳት ከ7 አመት በፊት……>> <<አይ ኡሚ ለምን ነገርሻት?>> <<እንጃ እንዲሁ አፌን ሲበላኝ ይሁን?>> ሁለቱም ከት ብለው ሳቁ ሰው እንዴት በእንደዚህ አይነት ሰዓት ይስቃል እየገረመኝ ነበር ቀጥላ <<የእኔ ልጅ ሸሃዳ ታስይዘኝ?>> አለችው <<እንንዴታ ኡሚዬ አሽሃዱ……>> <<አሽ…ሃዱ>> <<አላኢላሃ ኢለላህ>>ድራማ እየሰሩብኝ ይሁን እንዴ? ስል አሰብኩ እኔ ሰው ሲሞት እንደዛ ነው የማውቀው ሲለቃቀስ ምናምን እናት እና ልጅ ምን እየሆኑ ነው? አስይዟት እንደጨረሰ የረጅም ጊዜ ታሪክ ትተርክ ጀመር እያዳመጥናት ግማሽ ሰዓት አለፈ ህመም ሲሰማት "አሽሃዱ አላኢላሃ ኢለላህ……ወአሽሃዱ አነ ሙሃመደን ረሱሉላህ" ትላለች ከዛ ታሪኩን ታጫውተናለች በዚህ መሃል ግን እስከ ወዲያኛው አይኗን ገልጣ አሸለበች እጇን ከእጆቼ መሃል ነጠቀቺኝ ዝም ስትል ጊዜ <<ምን ሆነች?>> አልኩት እንደሞተች ገብቶኛል ግን ማመን አልፈለግኩም <<ወደ አኼራ ሄደች>> ብሎኝ አይኖቿን ከደናቸው ችክ ብዬ ቀረሁ ድምፅ አውጥቼ መጮህ አልቻልኩም እንጂ እያለቀስኩ በጣም እያለቀስኩ ነበር እውነት ሞተች ሞትን ሞተች?? ታዲያ ሰው አይደለች? አለኝ ደርሶ አንድ ድምፅ ከምንም በላይ የኢርቫ አለማልቀስ እና አለማዘን ገርሞኛል እንዴት አይነት ጎበዝ ነው እናቱ ሞታ እንኳን ሰው አያለቅስም? ግጥም መግጠም እና መፎከር ነው እንጂ የተከለከለው አታልቅሱ አይናችሁ ማንባት አይችልም አልተባለም ብቻ ገረመኝ ዶክተሮቹ ተሰክቶላት የነበረውን ግሉኮስ እና መሰል ፈሳሽ መድሃኒት ነቅለው እስከ ሚያስተካክሏት ወጥተን ጠበቅናቸው ሁሉም ያለቅሳል ያነባል መርዋን በራሱ ጥንካሬው ክዶታል <<ሰብር ይስጥህ አባቴ በጣም ያሳዝናል>> አልኩት ከጎኑ ጠጋ ብዬ የሰጠኝ መልስ ግን በጣም አስገረመኝ <<መሞቷ አይደለም ያሳዘነኝ ታሪኳ ነው ሳገኛት የነበራት ታሪክ ነው ያሳዘነኝ የፍዐሉ መን የሻዕ(ያሻውን ሰሪ የሆነ ጌታ ሁን ስላለው ሆነ)>> እኔም አርፍጄ የሰማሁት ቢሆንም እንኳን በጣም ልቤን ሰብሮታል Like 🥰

ዛሬ የግሩፓችን ሶስቱም ሴት አድማይነሮቻችን ተመርቀዋል እንኳን ደስ አላችሁ CONGRATULATION RABI HIKMA AND SEMIRA(BESMI)
ዛሬ የግሩፓችን ሶስቱም ሴት አድማይነሮቻችን ተመርቀዋል እንኳን ደስ አላችሁ CONGRATULATION RABI HIKMA AND SEMIRA(BESMI)

☆Anahira☆ 🎀 ክፍል 15 ((☆الصلاة خير من النوم الصلاة خير من النوم الله اكبر الله اكبر☆))        ከተጋባን 5ኛው የንጋት ጥሪ ነው የፈጅር አዛን ከሪልስቴቱ መሃል በሚገኘው መስጂድ ቀጥሎ በሁለታችንም ስልክ በሴኮንዶች ልዩነት ተሰማ እኔ መጀመሪያውንም ነቅቼ ነበር እንቅልፍ ያን ያህል አልወሰደኝም እናቴን በዛ ጭንቀት ውስጥ ትቻት እንደመጣሁ እያሰብኩ ነበር ኢርቫ ግን እስከ ወዲያኛው የማይነቃ ይመስላል ተነስቼ  ቀሰቀስኩት እና ለመታጠብ ወደ መታጠቢያ ክፍል ገባሁ ፈጅርንም በተለመደው መንገድ ሰገድን ትንሽ ስለቤቱ ልንገራችሁ እኔ ከነበርኩበት ቤት ፍፁም ተቃራኒ ነው እንዴት መሰላችሁ እኛ ካላወራን የሚያወራ አካል የለም ማንም ስለሌለ እኛም የምናወራውን ከአንዱ ክፍል ተደጋግሞ ይሰማናል  የዚህን ያህል ባዶ ነው? የሰውን ዋጋ የምናውቀው ሰው ስናጣ ነው ስለነበረን ነገር አስፈላጊነት የምናውቀው ስናጣው ነው ሶስቱን ቀን ኡሚ እና እናቴ(የኢርቫ) እናት እየመጡ ስለነበር ብዙም ፀጥታው አልተሰማኝም እነዚህን ሁለት ቀናት ግን ኡፍፍ…ብቻ ወደ ማዕድ ክፍል ገባን <<በመጀመሪያ ሳምንታችን ምግብ እንኳን ራሳችን ስናበስል አናሳዝንም?>> አልኩት ከፍሪጅ ውስጥ ውሃ አውጥቶ እየጠጣ ነበር ንግግሬ ቁም ነገር ስለመሰለው <<አፍወን እውነትሽን እኮ ነው ግን ወጥተን እንብላ አይደል?>> <<በቃ ቀልድ እና ቁም ነገር እንኳን መለየት ተስኖሃል ማለት ነው?>> <<አንቺ ነሻ እንደዛ ያደረግሺኝ አላህ ይይልሽ>> <<ሃ ሃ ሃ>> <<ሃ ሃ ሃ ምነው ተሳሳትኩ?>> የቁርሱ መርሃ ግብር ተጠናቀቀ ኢርቫ ወደ ስራ የሚመለስበት ቀን ነው እኔም ከእናቴ ጋር በተቀጣጠርነው ቀጠሮ መሰረት የእሱን ከቤት መውጣት እየተጠባበቅኩ ነው ለብሶ እንደጨረሰ ወረቀቶቹን ማስተካከል ጀመረ በእሱም ጥቂት አገዝኩት እና ሸኝቼው ቀጥታ ወደ እሷ ነበር ያቀናሁት በህክምናው ትንቢት የሚቀሯት ድፍን ሶስት ቀናት እና ሁለት ሌሊቶች ናቸው ግን ወደ እሷ ባደረግኩት ጉዞ ላይ አንድ የቁርአን አያ ሳዳምጥ ነበር አሁን ካለሁበት ሁኔታ ጋር ተመሳሰለብኝ ከምንም በላይ °°``ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት´´°° በጆሮዬ ላይ ሲያቃጭል ነበር ደረስኩ ዛሬ የእሷም ፊት በትንሹ ቀለል ብሎታል <<ዛሬን አብረን ምሳ እንድንበላ ነው>> አለቺኝ እኔም እንደዛ በድን ከሆነ ቤት ወጥቼ ከእሷ ጋር መገናኘቴን ወድጄዋለሁ ዙሁርን በጀመዓ ሰግደን በኻዲሟ አማካኝነት የተሰራውን ምግብ በልተን አሪፍ ጊዜ አሳለፍን የምትነግረኝ ነገር በሙሉ የድሮ ትዝታዎች ነበር  ከኢርቫ በፊት ሁለት ወንድ ልጆች እንደነበሯት ነገረቺኝ ከአባታቸው ጋር በጦርነት እንዳጣቻቸው ጭምር ታዲያ ከኢርቫ አባት ጋር እንዴት ተገናኙ¿?የእኔም ጥያቄ ነበር ስደተኛ ነበረች የስነልቦናዋ ሁኔታዋም ጥሩ አልነበረም ከአኢሻ መስጂድ በሴቶች መግቢያ በኩል ጁምዓን ጠብቃ በመስጂዱ በራፍ ላይ እጆቿን ሰዎች ሲያልፉ ከጣሉላት ሻርፕ ደግሞ አንዱን ዘርግታ ከጁምዓ ሙዕሚን ሰጋጆች የምትመፀወተውን ሳንቲም እና ገንዘብ መተዳደሪያዋ አድርጋ ትኖር ነበር  የመጀመሪያ ልጅ ስለሆነች እና ወላጆቿ ከእምነታቸው ይልቅ ለባህላቸው የተሰየሙ ስለነበሩ በልጅነቷ ነው የዳሯት ትምህርት ላይም ቢሆን ከማንበብ እና ከመፃፍ በዘለለ እውቀት የላትም ወላጆቿ የመረጡላት ሰው ከእሷ እድሜ እጅጉን የራቀ ከመሆኑም በላይ ወላጆቿን የሚያስተዳድረው እሱ ስለሆነ የሚስት ህይወት ሳይሆን የባሪያን ህይወት ያሳለፈች እስከ ሚመስል ድረስ ታሪኳ ዘግናኝ ነው የቀድሞ ባሏ ወታደር ነው ከውትድርና ግዳጁ በቀር ስለአላህ ስለ ኢስላም ምንም የማያውቅ ለማወቅ የማይጥር የማይሻ በጉልበቱ ሁሉንም ማድረግ የሚችል የሚመስለው  የነገን ሞት እንዳያስታውስ ይመስል አዕምሮውን የዘጉበት እና በሁለት አመታት የሚበላለጡ ወንድ ልጆችን ወለደች ያኔ 18ኛ አመቷን ይዛ ነበር ታዲያ የየመን የእርስ በርስ ጦርነት አይሎ የቀድሞ ባሏም ከፍተኛ የጦር እዝ አዛዥ ስለነበር ልጆቿን የገቡበት ገብተው ገደሉባት ብቻዋን ቀረች ወደ ወላጆቿ ብትመለስም የባሏ አመፀኞች ሊተዋት አልቻሉም ከአንድ ሃገር ወደ አንድ ሃገር በህገ ወጥ ነጋዴዎች በኩል ሲላት በስደተኞችም በኩል እያለች ኢትዮጵያ ትገባለች እና ኑሮን አሊፍ ብላ ጀመረች መርዋን ደግሞ ከሃብታም እና ከቅድመ አያቱ ጀምሮ ከቀለም ትምህርት ባለፈ በኢማምነት አባቱ በዳዒነት በቃ ዘራቸው በኢስላም እውቅና ውስጥ ያለፈ ነው አንድ ጊዜ የረመዷን ፊጥራ ላይ የመርዋን እህት ለሴቶች ምግብ ስታድል ከሴቶቹ መሃል አንዲት በቀለም ደረጃ ለየት ያለች ሴት በአይኗ ላይ ተከሰተች አዎ ያቺ ሴት ሰሊመት ናት በቋንቋ ስለማትግባባ ከማንም ጋር መግባባት አልቻለችም የባሏ ገዳዮችም የሚከታተሏት ይመስላታል በጥቅሉ እብድ የሚለው ስያሜ በጊዜው ይገልፃታል ጠጋ ብላ ስታናግራት እኩያዋ መሆኗን አስተዋለች በጣምም አዘነች ይህቺ ሴት የሃራም ፍቅር ተከትላ አልመጣችም ሰላምን ብላ ነፃነትን ብላ ቢሆን እንጂ ቤተሰቡ እየለመዳት ሲመጣ መርዋን ደግሞ ከመልመድም በላይ የሆነ ስሜት ነበረው በወቅቱ ለአባቱ ይህን ዜና ሲያስረዳው ተናደደበት አስተውላችሁ ከሆነ እኛ የቱንም ያህል እውቀት ቢኖረን ሰዋዊ ስሜታችን የሚያሸንፈን አጋጣሚ አለ እና የመርዋን አባት ለስንት መሻዪኾች እንደ ሴት ተጠይቀው አሻፈረኝ ያሉትን ለልጃቸው ስደተኛ እንስትን መዳር አልተዋጠላቸውም እሷም ብትሆን ለመርዋን የሆነ አይነት እይታ ነበራት ነገሮችን ባስተነተኑ ጊዜ ለመርዋን  ሰሊመትን ፈቀዱለት የሃላል ህይወት ተጀመረ የተቀጠፈችው ፅጌረዳ ዳግም ቅርንጫፎች ኖረዋት ማበብ ጀመረች ምንም እንኳን ከኢርቫ በኋላ ልጅ ባይሰጣቸውም በጌታዋ ላይ የነበራት ተስፋ ከማንም በላይ ደስተኛ አድርጓት ኖራለች ይህን ታሪክ አጫውታኝ ጊዜ ወስደን ብዙ አወራን በስተመጨረሻ  ተሰነባበትን በጣም ደስ የሚል ጊዜ ነበር ቤት እንደደረስኩ እራት እና መሰል የቤት ውስጥ ክንውኖችን በመስራት ተወጥሬ ነበር ኢርቫን ደውሎ ዛሬን እናቱ ጋር ሊያመሽ እንደፈለገ ነገረኝ እሺ ብዬው መጠበቁን ተያያዝኩት በግምት 04:40 አካባቢ ይመስለኛል መጣ እራት አልበላም አለ በጣም ከፍቶት ነበር እሷ እንዳለችው ምኑንም መለየት አይቻልም <<ይሄንን ሰው ማነው እንዲህ ያስከፋው?>> አልኩት በላፕቶፑ አዲስ የመኪና ሞዴሎችን እና አመራረት ሂደት እየተመለከተ ነበር <<ምንም አልሆንኩም>>አለኝ በአጭሩ <<ቅድም ስታናግረኝ እንዲህ አልነበርክም እኮ አሁን ምንድነው የሆንከው?>> ላፕቶፑን ዘግቶት ጀርባውን ሰጥቶኝ ተኛ እኔም አጥብቄ አልጠየቅኩትም ሲከብደው በራሱ ይናገራል ብዬ መብራቱን አጥፍቼ ተኛሁ ብዙ አልቆየም ዞረ Like 🥰

I apologized u,ረሳኋችሁ አይደል ያለፋችሁ sisters and brothers congratulation🥳  እያልኩ ያላለፋችሁም እንዲሁ አላህ ሰብር ይስጣችሁ አብሽሩ። ውጤት የመጣላችሁ ስለጊቢ many information ታገኙ ዘንድ comment ላይ ገብታችሁ ሊንኩን በመጫን ተጠቃሚ ትሆኑ ዘንድ በአክብሮት እጠይቃለሁ።

እናቴን የሚገዛኝ ማን ነው? coming soon......

እድሜና_ምርጫ አንብቡት ትጠቀሙበታላችሁ ቆንጆ ናት አፍላ 15 አመቷ ነዉ ጎረምሶች ሲያዩዋት አይናቸው ይጎለጎላል ጎልማሶች አይተው ይመኟታል ወንዶች ይከጅሏታል ሴቶች በቅናት እንደ ሽንኩርት ይልጧታል። አንድ ቀን እንዲህ ስል ጠየቅኳት። ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን መስፈርት እንዲያሟላ ትፈልጊያለሽ አልኳት ??? በፍጥነት መለሰችልኝ የተማረ መሆን አለበት፤ ማስተርስ ያለው ይመረጣል ከተቻለ የግል ቢዝነስ የሚሰራ፤ ኢንቨስተር ቢሆን አሪፍ ነው፤ ካልሆነ ግን አሪፍ ደሞዝ ሊኖረው ግድ ነው መኖሪያ ቤቱ G +2 ቢሆን ደስ ይለኛል፤ ከG+1 በታች ግን አልፈልግም። መኪና በጣም ነው የምወደው ምርጥ መኪኖች ቢኖሩት? ምርጥ መኪኖች ካልሆኑም ከተጋባን በኋላ እኔ እንዲገዛ አደርገዋለሁ ሙድ የገባው ቢሆን ደስ ይለኛል ሁሌ ግን የሚቅም፤ የሚጨብስ እና የሚያጨስ መሆን የለበትም ጨዋታ የሚያውቅ ሁሌ የሚያስቀኝ!! ቁመቱ በጣም እንዲረዝም አልፈልግም እኔ አጠር ስለምል በጣም እንዳይበልጠኝ ደረቱ ሰፋ ያለ ሆኖ ቦርጭ የሚባል እንዲኖረው አልፈልግም። ጸጉሩ ፍሪዝ ቢሆን ደስ ይለኛል፤ አይኑ የሚያምር፤መልኩ ጸይም መሆን አለበት በጣም ቀይ ወይም በጣም ጥቁር ወንድ አልወድም አለባበሱ ዘናጭ መሆን አለበት የሚወደኝ፤ የሚንከባከበኝ፤ ሮማንቲክ የሆነ፤ በሳምንት ቢያንስ ሁለቴ የሻማ እራት ያለበት ሆቴል የሚጋብዘኝ፤ ቢያንስ በወር ሁለቴ ጭፈራ ቤት የሚወስደኝ፤ ከበዓላት እና ከልደቴ ቀን በተጨማሪ ስጦታ እያመጣ ስርፕራይዝ የሚያደርገኝ፤ ፍቅር የሚያውቅ፤ በተለያየ ቁልምጫ ስም የሚጠራኝ እና ታማኝ ከእኔ ውጪ አንዲት ሴት የማያይ ....... ይበቃል አልኳት እንደማታቆም ስለገባኝ። እንዲህ አይነት ወንድ ኢትዮጵያ ውስጥ ቀርቶ አስቴር አወቀ ዘፈን ውስጥ እንኳን አይገኝም አልኩ በውስጤ ለሷ ግን አልነገርኳትም። ከአስር አመት በኋላ ሳገኛት 25 አመቷ ነበር አላገባችም ዩኒቨርስቲ ጨርሳ ስራ ይዛለች። ጥቂት ቦይ ፍሬንዶች ይዛ ለቃለች አሁንም ታምራለች እንደድሮው ግን የሰው ሁሉ አይን ማረፊያ አይደለችም። መልሼ ያንኑ ጥያቄ ጠየቅኳት። ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን አይነት ነገሮች ማሟላት አለበት ??? የማፈቅረው ሰው መሆን አለበት፤ ፍቅር ከሌለ ላገባው አልችልም። ከማልወደው ሰው ጋር አንድ ቀን ላድር አልችልም ታማኝ እንዲሆን እፈልጋለሁ። እንዲያከብረኝ እፈልጋለሁ። ጥሩ ስራ ቢኖረው፤ ማንበብ የሚወድና በሃሳብ የምንግባባ ቢሆን ደስ ይለኛል። ቆንጆና ሃብታም ከሆነ ጥሩ ነው፤ ካልሆነም ግን አብረን ሰርተን መለወጥ እንችላለን ዋናው መግባባት ነው። በተረፈ ቤተሰቡን የሚወድ እና የማይዋሽ መሆን አለበት ወንዱ ሁሉ የማይታመን ሆነብን እኮ ዋናው የሚታመን ከሆነ ሌላው ችግር የለውም። ጊዜው ይሮጣል!!! ከአስር አመት በኋላ ስንገናኝም አላገባችም 35 አመት እያለፋት ነበር ደግሜ ያንኑ ጥያቄ ጠይቅኳት። ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን አይነት ነገሮች ማሟላት አለበት??? ትንሽ አሰብ አደረገችና የምግባባው ሰው ከሆነ ሌላው ችግር የለውም አለችኝ። መልኩ፤ ጸጉሩ፤ ሃብቱ፤ እውቀቱስ አልኳት።??? ወንድ ልጅ ደግሞ መልክ ምን ያደርግለታል? ከቺምፓንዚ መለስ ካለ ሌላው ችግር የለውም አለች እየሳቀች። ከአስር አመት በኋላ ሳገኛት አግብታ ሁለት ልጆች ወልዳ ነበር። ባሏ አጭር፤ ጥቁር፤ መላጣ፤ የከባዳ መኪና ሾፌር አይነት ቦርጭ ያለው፤ ሱሪውን ቦርጩ መሃከል ላይ የሚታጠቅ፤ ሁልጊዜ መላጣውን የሚያልበው ዝጋታም ነገር ነው። እንዴት ነው ትወጂዋለሽ አልኳት ምን ማለትህ ነው ትዳር አይደል? ማለቴ ድሮ የነገርሽኝ አይነት ሰው አይደለም ብዬ ነው? ያኔማ አየር ላይ ነበርኩ፤ እድሜ መስታወት ነው፤ ብዙ ያስተምራል፤ አሁን ተምረን ልብ ገዝተን ነው አለች ተከዝ ብላ። ሁሌ የማይቀያየር አንድ መስፈርት ነበረሽ፤ ታማኝ መሆን አለበት ትይኝ ነበር። ባልሽ ታማኝ ነው? ታማኝ ፈጣሪ ብቻ ነው፤ በቃ ግን ትዳር ስለሆነ ከማይታመን ሰው ጋር መኖር ትለምዳለህ፤ አየህ አሁን የገባኝ ነገር ትዳር ማለት እንደ ፖለቲካ ነው። ፖለቲከኞች ውሸት እየነገሩን አብረን እንደምንኖረው ሁሉ ትዳር ውስጥም ይሄ ያጋጥማል አለች። በትዳርሽ ደስተኛ ነሽ? አልኳት እያዘንኩ ደስታ አንጻራዊ ነው፤ በልጆቼ ደስ ይለኛል፤ ትዳሬን አከብራለሁ። በተረፈ ግን እየኖርኩ ነው አለች ፈገግ ብላ። በዛች ቅጽበታዊ ፈገግታ ውስጥ ግን የጊዜን ኃይለኛነት አየሁ። What do u think ahbab?

Is there anyone who study biology with other field like chemistry,physics or technology .....,if so DM me @f_atir.

ሰወችን አጣለሁ ብለህ አትፍራ ራስህን እንዳታጣ ግን ፍራ ሁሉንም ሰወችን አስደስታለሁ ስትል!
ሰወችን አጣለሁ ብለህ አትፍራ ራስህን እንዳታጣ ግን ፍራ  ሁሉንም ሰወችን አስደስታለሁ ስትል!

ምላሳችሁን ያዙ…
አንዳንድ ጥያቄዎች ጥያቄ አይደሉም፤ በሰው ልብ ላይ የሚወረወሩ ቀስቶች ናቸው። “እስከዛሬ ለምን አልወለድሽም?” “እስከዛሬ ለምን አላገባሽም?” “ለምን እንዲህ ሆንሽ?” “በጣም ወፈርሽ… በጣም ከሳሽ…” አንተ ቀላል ብለህ የተናገርከው ነገር፣ ሌላው ሰው ዕድሜ ልክ በልቡ ሊሸከመው ይችላል። ❤️‍🩹 ስለዚህ ከመናገርህ በፊት አስብ፤ ቃልህ መድኃኒት ነው ወይስ ቁስል? አላህ ኒያችንን ያውቃል፤ እኛ ግን በቃላችን እንጠንቀቅ። ምላሳችንን እንጠብቅ… ምናልባት አንድ ቃል የአንድን ሰው ልብ ሊያድን ወይም ሊሰብር ይችላል። @soulview1

♻️የምሽት ውብ ስንቅ♻️ ዚክርና ዱዓ ሕይወታችንን ከሚያሳምሩ ኢባዳዎች ዋናዎቹ ናቸው አሏህ ያግራልን ያረብብብ ጁሙዓ 22/12/2018 💐የብስራት ለይል ተመኘሁላችሁ💐

☆Anahira☆ 🎀 ክፍል 14 ☆ከሁለት ቀን በፊት ከሰሊመት ጋር ተገናኝተን ከቀራት ሁለት ሳምንት የመጀመሪያውን ሳምንት ማጠናቀቋን ነገረቺኝ እየተላቀስን ነበር ስለዚህ የሰርጋችንን ጊዜ በተቻለ ብናሳጥረው  ብላ አማከረቺኝ እሺ እንጂ ሌላ መልስ አልነበረኝም በዛ ዙሪያ ለማውራት ዛሬን ተገኝተዋል ለወጉ ያህል እነሱ ሲያወሩ እኔ መኝታ ክፍሌ ውስጥ ከአትሮኖስ እና ሊጠይቋት ከመጡ የስራ አጋሮቿ ጋር  ተቀመጥኩ በአንዳንድ አጋጣሚ እየተሳሳቁ አረፈዱ ከተወሰነ ውይይት በኋላ ኡሚ አስጠርታኝ <<እኛ ለሰርግ ኸሚስን መረጥን አንቺስ መቼ ይሁን ትያለሽ?……… ዋናው ኒካህ ነበር እሱን ጨርሰናል በየሁለት ሳምንቱ ይደግሳሉም የሚል ወሬ እንዳይነሳ ቀለል እናደርገዋለን>> ሃቁን ለመናገር ምንም አይነት የደስታ ስሜት አልተሰማኝም እንባ እና ፈገግታ ደስታ እና ሃዘን ሞት እና ሰርግ ብቻ ከተመርቅኩ በኋላ እንደ አዲስ ህይወትን መላመድ የጀመርኩ ይመስለኛል ሁሉንም አንድ በአንድ አስተዋልኩ ሰሊመት እሺ እንድል በአይኖቿ ማባበል ይዛለች በረጅሙ ተንፍሼ <<ኡፍፍፍፍፍፍ እሺ ……እ ማለት ምንም ሃሳብ የለኝም ከኒካህ ቀን የተደረገው ድግስ ሳይበልጥም ሳይበዛ ይሁን>> አልኳቸው ግን የነኡሚ ነገር ሳይስተካከል ለሰርግ ዝግጁ አልነበርኩም ግን ደግሞ በአንድ በኩል ከየኛውም ሰው በላይ ከዛሬ ነገ የልጇን ሰርግ ለማየት የምትናፍቅ እናት አለች ስለዚህ አላህ ካለ ከሁለት ቀን በኋላ ስለሚውለው ሃሙስ ሰርጌ እንዲሆን ተስማማሁ ትክክለኛ ውሳኔ ይመስለኛል እንደዛ ቢሆን የሚሻል አይመስላችሁም?¿ ቀጥሎ እናት እና እናት አባት እና አባት ተነስተው መተቃቀፍ እና [""መብሩክ""] መባባል ጀመሩ እኔ እና ኢርቫ ግን ከአንድ ጥግ ወደ አንድ ጥግ ቆዝመን ቁጭ አልን እኔ እየተካሄደ ባለው ነገር ቆዝሜያለሁ ኢርቫ ደግሞ በእኔ መቆዘም ምክንያት ቆዝሟል ሁሉም እየተሳሳቀ የወዳጅነት ወሬያቸውን ሲያጧጡፉ የማንም ትኩረት በእኔ ላይ እንዳልሆነ ስለተረዳሁ ተነስቼ ወደ ክፍሌ ሄድኩ የአትሮኖስ ጓደኞች አትሮኖስን ትንሽ ተዝናንተን እንመለስ ብለዋት እየወጡ ነበር እንድቀላቀላቸው ጠየቁኝ ሶስት ሴቶች ናቸው ማረፍ እንደፈለግኩ ነግሬያቸው ገባሁ አትሮኖስ ከጓደኞቿ ግብዣ ተመልሳ ከተኛሁበት ስትቀሰቅሰኝ ብቻ ነው እንቅልፍ ውስጥ እንደነበርኩ የታወቀኝ ዙሁርን ከነሱና ሷላት ጋር  ሰግጄ ተመልሼ ተኛሁ ሁለቱ ቀናት በሽቅድድም አልፈው የረቡዕ ምሽት ላይ እንገኛለን   ከሳምንታት በፊት የነበሩት ወይዛዝርቶች ዳግም ቤቱን አውደውታል የሂና ባለሞያዋ የሂና ጥበብ ስራዋን በእጄ ላይ አሳርፋ ሄዳለች እኔ እና አትሮኖስ እስከ ሚደርቅ መጠበቅ ተያያዝን አንዳንድ በስም እንጂ በአካል የሚያውቁኝ የማያውቁኝ የሰፈራችን ሴቶች መብሩክ እያሉኝ ገብተው ይወጣሉ እንዲህ እንዲህ ሆኖ ረቡዕ ተጠናቅቆ በአላህ ቸርነት ሃሙስን ለመኖር ችለናል ገና በጠዋቱ መዘገጃጀት ጀመርኩ በቃ በህይወቴ የምጓጓለት ሰርጌን ዛሬ ተጠየፍኩት ይሁን አላውቅም ዝግጅቱ ቶሎ ባለቀ ብዬ ተመኘሁ እስከ ዙሁር ሙሽራው እና መሰል የስራ ባልደረቦቹ እንደ መጡ ተነገረን እኔ እንደሚዜ ያቀረብኳቸው በቅርበት የማውቃቸውን ኒሳዕን(የመድረሳችን የሴት አሚር ናት)እና አትሮኖስን ነው እኛም ዙሁርን ሰገድን ከምሳ በኋላ ስለነብዩ(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አቂዳ ሱና ትዳር ተርቢያ ሲራ አንድ ጊዜ በአቢ ሌላኛው ጊዜ ደግሞ በኢርቫን አባት መርዋን ሲነገረን ቆየ እና የመጨረሻ ወደ ቤታችን የምንሄድበት የቁርጡ ሰዓት ደረሰ አሱርን እዛው ሰግደን ወጣን ሁለታችንም ምንም ሳናወራ ሹፌሩ መኪናውን አንቀሳቀሰ እኔ የመሰለኝ የሆነ ሰው እንደሚከተለኝ ነው ግን ማንም አልነበረም ወደ የት እየሄድን እንደሆነ አላወቅኩም ግን ከአንድ ሰዓት በላይ የመኪና ጉዞ ላይ ነበርን ጀንበር የስንብት ተግባሯን ስታከናውን በመንገዳችን ላይ ከአንድ መስጂድ የአዛን ድምፅ ተሰማ እኔ በሴቶች መግቢያ ሹፌሩ እና ኢርቫ ደግሞ በወንዶች መግቢያ በኩል ገብተን ሰገድን መንገዱ በጣም ተዘጋግቶ ነበር ድጋሚ ለግማሽ ሰዓት መንገድ ላይ ከቆየን በኋላ ወደ አንድ መኖሪያ መንደር መኪናው ታጠፈ ቁመታቸው ከመርዘሙ የተነሳ ጣራቸውን ማየት አይቻልም ከየበረንዳው ላይ ብርሃን የሚተፉ ውብ ውብ አምፑሎች ከጨረቃዋ ብርሃን ጋር ተደምረው አሪፍ ውበት አላቸው በስተመጨረሻ የደረስን መሰለኝ ሹፌሩ የመኪናው ፍጥነቱን አቀዝቅዞ ቆመ እና ወርደን ወደ ቤቱ ገባን የግቢው ስፋት የሚውጥ ይመስላል ፀጥ ያለ ቦታ ነው የቤቱ መግቢያ በር መግቢያ ላይ እንደቆምን ከፍቶ እንድገባ በእጆቹ ጋበዘኝ እሺ በማለት ተከትዬው ገባሁ መብራቱን ሲያበራ በጊዜ ክፍተት አምፑሎቹ ቦግ ቦግ ማለት ጀመሩ ፊት ለፊት የሳሎኑ መጅሊስ ተቀበለን <<እ……ኢሻ አዛን ብሏል ልብስሽ ለመስገድ ነፃነት ይሰጥሻል?>> አለኝ እሱ ከወትሮው የተለየ ጀለቢያ ለበሰ እንጂ ጀለቢያነቱን አልጣለም <<እ…… አዎ መቀየር ሳያስፈልገኝ አይቀርም>> አልኩት እንድከተለው አዞኝ ሄደ ተከተልኩት አንድ የበር እጀታ ተጭኖ ሲከፍተው ወደ ጥቁር የተጠጋ ብራማ ቀለም ያለው መኝታ ክፍል ጠበቀኝ የሙሽራ ቀሚሴን እየጎተትኩ ገባሁ ለሁሉም ነገር ለአመታት ሲዘጋጅበት የኖረ ይመስላል ከቁም ሳጥኑ ውስጥ ልብስ እና ፎጣ አውጥቶ እየሰጠኝ <<መታጠቢያ ክፍሉ ይህ ነው ሳሎን እጠብቅሻለሁ>> አለኝ በእሺታ ገብቼ ታጠብኩ እና የቀረበልኝን ልብስ ለብሼ ወጣሁ እሱ ቀድሞ ከለበሰው ጀለቢያ ሌላ ነበር የለበሰው ቤቱ ውስጥ ሌሎች መታጠቢያ ክፍሎች እንዳሉ ተረዳሁ መስገጃ ላይ ተቀምጦ ተስቢህ እየቆጠረ ጠበቀኝ ጀርባውን ሰጥቶኝ ስለተቀመጠ አላየኝም <<መጥቻለሁ>> አልኩት ዘወር ብሎ <<እሺ……እንስገድ>> አለኝ ፊት እና ኋላ ሆነን ከኢሻ ሷላት በፊት ረከዐተይኒ ሰገድን ቀጥለን ኢሻን ከመጀመሪያው ጊዜ በላይ ዝም ተባባልን <<ምግብ ትበያለሽ?>> ሲል አንደበቱን አላቀቀ <<አልራበኝም>> አልኩት                                  ቀጥሎ               <^> <^> <^>                      👇 [By The Order Of Allah~ In The Sunnah Of Our Prophet] 10🥰 ይቀጥላል☆ ☆ ☆. . . .

Once you leave home you only return as a guest. But the fact is we left home to build our own home 🖤
Once you leave home you only return as a guest. But the fact is we left home to build our own home 🖤

♻️የምሽት ውብ ስንቅ♻️ ወሳኝና መሳጭ ኹጥባ አሏህ ቀልባችንን ሰላም ያድርግልን ኢላሂ ቀልባችንን ካንተ በሆነ ብርሀን አብራልን በወንጀል ብዛት የጠቆረውን ልባችንን አንፃልን ያረብብብ ረዳታችን አንተ ብቻ ነህ ረቡዕ 20/12/2018 💐የብስራት ለይል ተመኘሁላችሁ💐

☆Anahira✨         🎀ክፍል 13 ☆ዝም ተባባልን መረጋጋቱን ሳይ <<እ…… እና አሁን እንሂድ ወደ ሳሎን እንሂድ>> <<ምነው ትንሽ ብንቆይስ?>> <<አይ ምንም ችግር የለም ግን እዚህ ……ብቻ…ችንን>> <<ብንሆንስ? ማ……ማለ…ት ኒካህ አለን አይደል?>> ንግግሩ እያስደነገጠኝ ዝም ብዬው ወደ በሩ ሄድኩ እና እስከ መጨረሻው ከፈትኩት ፊቱ ላይ መምታታት እየተነበበ <<ምን እያደረግሽ ነው?>> <<ምንም ያው አየር ይግባ ብዬ ነው>> <<መስኮቱ አይበቃም?>> <<በመስኮት የሚገባው አየር ሳይሆን ብርድ ነው>>ሳቀ እና  <<ቀልደኛ ነሽ ሲጀመር እኔ ብትዪኝም እንደዛ አላደርግም ነበር አሁን መታጠብ እፈልጋለሁ መታጠቢያ ቤቱ ይህ ነው?>> መታጠቢያ ክፍሉን ሲከፍተው ተንደርድሬ የበሩን እጀታ ያዝኩት ደንግጬ ነበር  <<እ… እ …እ…? እዚህ? አ…ይ አይቻ…ልም>> እየሳቀ ሹክሹክታ በሚመስል ድምፅ <<ቆይ ዛሬ ምን ነክቶሻል? ፊቴን እኮ ነው የምታጠበው እንዲህ እንባ በእንባ አድርገሺኝ ልሂድ?>> <<እ…… ነው እንዴ? እሺ ግባ>> ብዙም ሳይቆይ ወጣ ፎጣ ይዤ ጠበቅኩት ፊቱን አድርቆ ሲጨርስ ሄድን ሁሉም እኛን ሰጠብቁ የነበሩ ይመስላል የቀረበውን እራት ከበላን በኋላ አቢ <<ኧ……ኢርቫ አሁን ምን አሰባችሁ? ምን……ማለት በፍቺው ፀናችሁ?>> ሲለው ዞሮ የጎኒዮሽ አየኝ እኔም <<አቢ ትቼዋለሁ>> <<ማለት?……አሁን ኢርቫንን ተቀብለሽዋል?>> <<እ……አዎ>> ከመጀመሪያው በተለየ ፈገግ እያለ <<መር……ሃባ እንዲህ ነው እንጂ የእኔ ልጅ አንቺ በፍቅር ስም የሰየምሽው ህይወት ቆሻሻነቱ እንዴት እንዳልታየሽ አላውቅም እንጂ መጥፎ ነበር የነቢያችንም ሱና አልነበረም>> እሺ በሚል ራሴን አንቀሳቀስኩለት ከሃዲስ ጋር ስለነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሲያወራልን ቆይተን ኢርቫን ለመሸኘት ወጣሁ ምንም ሳንነጋገር መኪናው ካለበት ቦታ ደርሰን ቆምን <<በቃ ግባ>> አልኩት ወደ ቤት ዞሬ እያየሁ <<እሺ አንቺም ግቢ ብርድ ነው>> እንደ ተመካከረ ሰው በእኩል ሰዓት ተቃቀፍን እና ተሰነባብተን ወደ ቤት ገባሁ ስገባ ኡሚ <<ኧረ እነዚህ ሰዎች የበላቸው ጅብ እኮ አልጮህ አለ>> አለች ስልክ እየሞከረች አቢም ስልኩን ይቀጠቅጣል ኢነብ እና አትሮን ግን አያነሱም የኢነብ ስልክ አይጠራም የአትሮን ይጠራል ግን አይነሳም በዚሁ ጭንቀት ላይ እንዳሉ የኢነብ የመኪና ድምፅ ከውጪ ተሰማ ወደ ውስጥ ሲገባ ከአትሮኖስ ጋር አብረው ይቆዩ ይመስል <<አትሮኖስስ?>> አልነው በአንድ ድምፅ እሱም <<ሸይጧን መስጂድ አይገባም>> አለን ያውመስጂድ ነበርኩ ለማለት ነው ኡሚ በአይኗ ገላምጣው ስልኩን ለመጨረሻ ጊዜ ጆሮዋ ላይ ስታሳርፍ ወደ ግቢ ውስጥ አንድ ታክሲ ገባ አትሮኖስን የያዘ ታክሲ ነው ወርዳ ስትመጣ ደነገጥን የጭንቅላቷ ግማሽ ክፍል በፋሻ ታስሯል እስከ ዛሬ ተሸፍኖ የኖረው ፀጉሯ ዛሬን በማን አለብኝነት ተዝለፍልፏል ወደ ውስጥ ደግፈን ከኡሚ ጋር አስገባናት በጣም ተደካክማብን ነበር <<አትሮን ምን ሆነሽ ነው ማነው እንዲህ ያደረገሽ?>> አልኳት እያቃሰተች <<አንድ ደንበኛ ነበረኝ ሚስቱ ህመምተኛ ናት እና ዛሬ ህክምና እያደረግኩላት ድንገት ተነስታ ከባሌ ጋር አመንዝረሻል በሚል በብርጭቆ ፈነከተቺኝ…ኡፍፍፍፍፍ በጣም ሳልጎዳ እቀራለሁ ብለሽ ነው?>> <<እሺ እሷስ?>> <<እሷ……ሷማ ወዲያው ጣቢያ ወስደዋታል ደግሞ እኮ ልመጣ ስል አሱር አዛን እያለ ነበር ደግሞ ዛሬ ቀጠሮዋ በራሱ አልነበረም ድንገት ስትመጣ ጊዜ የነገውን ቀጠሮዋን በዛሬ ታሳቢ አድርጌ ላስቀረው ነበር አሁን ይኸው እንደምታዪው አደረገቺኝ>> አለች በንግግሯ መሃል በጣም ልብ በሚነካ መንገድ ታቃስታለች አቢ ከጎኗ ተቀምጦ አቀፋት እሷም እያቀፈችው <<አቢ ሞቼብህ ነበር የመጀመሪያውን ስታሳርፍብኝ አዞረኝ ደግሞ እላፊ ሰዓት ስለነበር ሁሉም ሰው ወጥቷል ስጮህ እንኳን ቶሎ  የሚሰማኝ አልነበረም>> እንባዋ መርገፍ ጀመረ ውስጤ እንዴት እንደሆነ ልነግራችሁ አልችልም በቃ እለቱ የለቅሶ ቀን እስከ ሚመስለኝ ድጋሚ የምስቅ እስከማይመስለኝ ድረስ ምግብ በልታ ከክሊኒክ የተሰጣትን መድሃኒት ሰጥቻት ወደ ክፍላችን ሄድን እና አስተኛኋት ወዲያው ነበር እንቅልፍ የወሰዳት ብዙም ሳይቆይ ኢነብ ወደ ክፍሉ መጣ በሩን ከፍቶ እየዘጋ ሹክሹክታ በሚመስል ድምፅ <<ተኛች?>> አለኝ እንደዛ እንዳልሰደባት ዛሬን በጣም አሳዝናዋለች <<አዎ ተኝታለች ግባ>> አልኩት ገባ እና አልጋዬ ላይ እየተቀመጠ <<ቆይ እሷስ ምን ሆና ነው? ከእብድ ጋር እንደዚህ አይነት ቀልድ የጀመረችው?>> <<ኢነብ ደግሞ አንተን በምንም ቋንቋ ማስረዳት አይቻልም ስራዋ ምንድነው?>> <<ታዲያ እንዲህ እስከ ምትሆን ድረስ ብትተወውስ እንድትሰራ ያሰገደዳት አለ? ታውቂያለሽ ግን በዛው ብትቀር አስተغፊሩላህ>> <<አንተ እኮ ከቤት የምትወጣበት መንገድ የሚናፍቅህ አይነት ሰው ነህ ታዲያ አሁን ደርሰህ የአዛኝ ገፀባህሪን ስትጫወት አይጋጭብህም?>> <<እኔ በዚህ መንገድ ነው እንዴ ትውጣ ያልኩት አግብታ የራሷ ህይወት ኖሯት እንጂ ምንድነው ሁልጊዜ እንደ ሸረኛ የምታዪኝ?>> <<እንደዛ አላሰብኩትማ ደግሞ……>> ተናግሬ ሳልጨርስ ""… ወደ የት ነው የ……ምትሄጂው ይሄ…ቤት…ታውቀዋለች……ወለደቺኝ……አቢ ወሰዱት……ደብረ ዘይት……"" ስለእናቷ መቃዠት ጀመረች ሃሳቧ ሁሉ እናቷ ናት እኔ ሰው በእንቅልፍ ልቡ ሲያወራ የምፈራውን ያህል ምንም አልፈራም ኢነብ ወደ አልጋዋ ሄዶ የሚወራጩ እጆቿን እየያዘ (ሃያተል ኩርሲዩን) ይቀራላት ጀመር ከጥቂት ጊዜ በኋላ ድምጿ እየቀነሰ ሄዶ እንቅልፍ ወሰዳት <<አንተ ክርስቲያን መሆኗን ረሳኸው እንዴ?>> <<ቁርዓን ለአለም ነው የተላከው ጋርዶባቸው ነው እንጂ ደግሞ ጂን ሊጠጋት ስለሚችል እንዲህ ስትሆን እና ከነቃች እየቀራሽ አስተኛት>> አለኝ <<አይ መጥቼ እጠራሃለሁ እንጂ እኔ እፈራለሁ>> ከደቂቃዎች በፊት እኮ ሸይጧን እያላት ነበር አሁን ከማንም በላይ ሲንከባከባት ሳይ እየገረመኝ <<ኢነብ አትሮኖስ እኮ ላንተ አጂ ነብይ ናት>> <<እና ምን ይሁን? ለምን አየሃት ነው?>> <<ኧረ ስትነካት ነበር እኮ>> <<ሚንሃ ስርዐት ቀለድኩ ብለሽ በማይሆን ነገር  ደግሞ አሟታል ኡዙር አላት>> <<ቢሆንም…>> <<ሲጀመር ማነሽ ብዬ እንደማብራራልሽ እኮ ነው አልገባህ ያለኝ እያየሻት አይደል እንዴ እንዴት እንደሆነች?………አታስጩሂኝ አሁን ልጅቷ ትተኛበት>> ተቆጥቶኝ ወጣ ""የአላህ አይ አንተ ስንቱን ታሳያለህ? አሁን ክፍሌን የረገጠው ሰው ኢነብ ነበር? ወንድሜ አትሮኖስን ከመጠየፍ ባልዘለለ የሚያንቋሽሸው ኢነብ"" እየሳቅኩ ወደ አልጋዬ አመራሁ አትሮኖስም ሳትነቃ ሌሊቱ ወደ ንጋት መሸጋገር ጀመረ 1o🥰 ይቀጥላል☆ ☆ ☆