en
Feedback
@Maria Rubatto primary catholic school

@Maria Rubatto primary catholic school

Open in Telegram
1 326
Subscribers
+424 hours
+187 days
+9830 days
Posts Archive
እንኳን ለ2017 ዓ.ም ት/ት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ!!! ለተማሪ ወላጆች በሙሉ የ2017 ዓ.ም ትምህርት የሚጀመረው ማክሰኞ 7/1/2017 ዓ.ም ስለሆነ ጠዋት 2:00ሰአት ተማሪዎች ት/ቤት እንድትገኙ እናሳውቃለን። ት/ት የሚሰጠው እስከ ምሳ ሰአት 6:30 ድረስ ይሆናል።

የመፅሐፍ ቅድመ ክፍያ የከፈላችሁ ወላጆች ከ1 እስከ 8 መፅሐፍ ስለመጣ ነገ አርብ 10/12/2016 ጠዋት 2:30 እስከ 6:30 ድረስ መውሰድ ትችላላችሁ።

በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ ማሪያ ሩባቶ ካቶሊክ ት/ቤት በ2016 ዓ.ም ከተማ አቀፍ ፈተና (MINISTRY) የተፈተኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ሁሉም በጥሩ ውጤት አልፈዋል።

ከ1 - 6ኛ ክፍል መፅሐፍ መግዛት ለምትፈልጉ ወላጆች በዚህ ሳምንት ት/ቤት መጥታችሁ ክፍያ እንድትከፍሉ።

የአንደኛ መንፈቅ አመት በትምህርት ቢሮ የተዘጋጀ የ6 እና 8ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና መርሐ ግብር ነው:: በዚህ መሰረት ወላጆች ለተማሪዎች ድጋፍ እንድታደርጉላቸው በትህትና እንጠይቃለን::

በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!🏆🏆🥈🥉 በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኙ 11 ወረዳዎች የተወከሉ 11 ት/ቤቶች መካከል በተደረገ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ጥያቄና መልስ ውድድር ወረዳ 4 ወክሎ የተወዳደረው ት/ቤታችን 1. በ 8ኛ ክፍል ተማሪ ገሊላ አሸብር 3ኛ በመውጣት የዋንጫ እና ሜዳልያ ተሸላሚ ሆናለች 2. በ 6ኛ ክፍል ተማሪ ቅዱስ ሙላት 2ኛ በመውጣት የዋንጫ እና ሜዳልያ ተሸላሚ ሆኗል።

ታህሳስ 18/4/2016ዓ.ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 እና 4 በሚገኙ ስምንት ት/ቤቶች በትደረገ ጥያቄና መልስ ውድድር በ6ኛ እና እና 8ኛ ክፍል ተወዳድረው ውጤት ላመጡ ተማሪዎቻችን ዛሬ የሽልማት ስነ ስርዐት በት/ቤታችን ተከናውኗል። 1.ተማሪ ገሊላ አሸብር በ8ኛ ክፍል ውድድር 1ኛ በመውጣት ሜዳልያ እና የ6 ወር ነፃ የትምህርት እድል ተሸልማለች 2.ተማሪ ቅዱስ ሙላት በ6ኛ ክፍል ውድድር 1ኛ በመውጣቱ የሜዳልያ እና የ6ወር ነፃ የትምህርት እድል ተሸላሚ ሆኗል 3.ተማሪ አቤኔዘር ተሻገር በ8ኛ ክፍል ተወዳድሮ ት/ቤታችን 1ኛ እንዲወጣ ስላደረገ የሰርተፍኬት እና የመፅሐፍ ተሸላሚ ሆኗል 4. ተማሪ ቅዱስ ዮሐንስ በ6ኛ ክፍል በተደረገ ውድድር ት/ቤታችን 3ኛ እንዲወጣ ስላደረገ የሰርተፍኬት እና የመፅሐፍ ተሸላሚ ሆኗል። አጠቃላይ የት/ቤታችን ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ።