📚የታላላቅ ኡለማዋች ምክሮች እና አስተማሪ ታሪኮች 📢
✏️ለምን እንደተፈጠርክ ካላወቅህ ስለ መሞት እያሰብክ መጨነቅ አይጠበቅብህም።🔍 أَبُوبَکْرَ عَبْدَ الرَّحْمَانْ
Show more286
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+130 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
Photo unavailableShow in Telegram
🥣የዐሹራእ ቀን ፆም!
ለመልካም ሥራ አስተዋሽ እንሁን።
ከኢብኑ ዐባስ ተይዞ፡ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
﴿فَإِذَا كَانَ الْعَامُ الْمُقْبِلُ - إِنْ شَاءَ اللَّهُ - صُمْنَا الْيَوْمَ التَّاسِعَ﴾
«የሚቀጥለው ዓመት ከደረስኩ በአላህ ፍቃድ የዐሹራእን ቀን ፆም ዘጠነኛውን ጨምሬ እፆማለሁ።»
[ሙስሊም: 1134]
ከአቢ ቀታዳ ተይዞ፡ ነቢዩ እንዲህ ብለዋል፦
﴿صيامُ يومِ عاشوراءَ، إنِّي أحتَسِبُ على اللَّهِ أن يُكَفِّرَ السَّنةَ الَّتي قبلَهُ﴾
«የዐሹራእ ቀን ፆም ያለፈውን አመት ኃጢአት እንደሚያብስ ከአላህ እጠብቃለሁ።»
[ሙስሊም: 1162]
Photo unavailableShow in Telegram
ከሰኞ እስከ ሰኞ‼
=============
✍ ተከታታይ ወርቃማ ቀናት ከፊታችን፦
√ ሰኞ: የሙሐረም 9ኛ ቀን፣
√ ማክሰኞ: የሙሐረም 10ኛ ቀን → የዐሹራእ ጾም፣
√ ረቡዕ : የዐሹራእ ቀጣይ ቀን፣
√ ሐሙስ: ሥራዎች ወደ አላህ የሚቀርቡበት ቀን፣
√ ጁሙዓህ: የአያሙልቢዽ የመጀመሪያ ቀን (ሙሐረም 13)
√ ቅዳሜ: አያሙልቢዽ፣
√ እሁድ: አያሙልቢዽ፣
√ ሰኞ: ሥራዎች ወደ አላህ የሚቀርቡበት ቀን
አላህ አላህ!
እንኳን ተጨማሪ ሰበብ ኖሮት ሙሐረምን ሙሉውን መፆም ይወደዳል።
የቻልን እንጹም፣ ሌላውንም እናመላክት። አላህ ያግራልን።
||
t.me/MuradTadesse
#ብዛት_ሳይሆን ጥራት !
ከብዙ ጓደኞች ይልቅ አንድ የልብ የሆነ ወዳጅ ልብን ይሞላል ፣ ህይወትን ያ ቀናል! ያለ አግባብ ከሚጠፉ ብዙ ምሽቶች እና ከባከኑ ብዙ ቀናቶች በአግባቡ የተጠቀምንበት አንድ ቀን መንገዳችንን ለማቅናት ትልቅ አስተዋፅኦ አለው!
#የነገሮችን መጠን በጥቅማቸው በሚሰጡን ዋጋ እንጂ በብዛታቸው ልንለካቸው አይገባም። ብዛት ሊያጠፋ ይችላል ጥራት ግን ያለመልማል ! ጓደኛ ምረጡ!!!
03:27
Video unavailableShow in Telegram
የስልጤ ሙስሊሞች ሆይ እንንቃ
እንግዲህ ተመልከቱ በተውሂድ ያልታነፀ ማህበረሰብ መጨረሻው ምን እንደሚመስል። የጴንጤዎች ቁርስ ምሳ እራት ሲሆን ማየት በጣም ያሳዝናል። ጴንጤዎች ተውሂድ የማያውቀውን ህዝብ እንዴት እንደሚፈልጉት ብዙ ግዜ ለማህበረሰቡ ቢነገረውም ከቁም አልቆጠረውም ነበር፦፦ አኩ ሰቢ ገግክ ቢንጊርከ ቀጥ ባለ ሄደ ኢገቢኒማነን። መሰክ ሚንጊዝ ለሁልም የቻለን ጊዝ።
ይህቺ ሴት በቪዲዮው ላይ እንደሰማችሁት አንገቷ ላይ ያለውን ሙስባህ(ጨሌ ይመስለኛል) ፦
አንዱ የሰላት፦ አንዱ የዳዶ(የሽርኩ ማዕከል) የአርባ አራቱ አውሊያ አንዱ የአናጂና(የኑር ሁሴን)...... እያለች እያመለከች እንደነበረች ነው የተረዳሁት።
አብዛኛው ሰው ከውጭ ከሚነሱ የአክፍሮት ሀይላት መከላከል ብቻ እስልምና የሚጠበቅ ይመስለዋል ዋነው ነገር ግን የራስን የቤት ስራ መስራት መሆኑ ዘንግቶታል።
ኢብኑ ተይሚያህ(አላህ ይዘንለት) ያኔ እስልምናን በምን መልኩ ከሞንጎሎች ና ከተታሮች እንደታደገ ብናውቅ ይህ ችግር ባልተፈጠረ ነበር።
ማህበረሰቡ ተውሂድን ካልተማረ ሌላ ሀይማኖት ፍለጋ መዋለሉ አይቀርምና በግዜ ተውሂድ ላይ እንልፋ። ከእስልምና ውጪ ተቀባይነት የለምና።
وَمَن يَبْتَغِ غَيْرَ ٱلْإِسْلَٰمِ دِينًۭا فَلَن يُقْبَلَ مِنْهُ وَهُوَ فِى ٱلْءَاخِرَةِ مِنَ ٱلْخَٰسِرِينَ
ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከርሱ ተቀባይ የለውም፡፡ እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው፡፡
(2 : 85)።
በጣም ያሚየሳዝነው ይሄን ማህበረሰብ ይዘን ነው እንግዲህ የተውሂድ ግዜ አይደለም ተረጋጉ እያልን ያለነው ፥ የተውሂዱ ግዜ መቼ እንደሚመጣ ጥያቄው ለኛው የቤት ስራ ይሁን!!!
https://t.me/Ibnugarad
13.09 MB
ሱፍያን_ኢብኑ_ዑየይናህ ረሒመሁሏህ እንዲህ ይላሉ :-
«አስተዋይ ማለት መልካምና እና መጥፎን ያወቀ ሰው አይደለም።እነሆ አስተዋይ ማለት መልካምን ባየ ግዜ የተከተለና መጥፎን ባየ ግዜ ደግሞ የራቀው ማለት ነው።»
📚 ۞ حليـة الأوليـاء لأبي نعيـم【8/339】
ኢብኑል_ቀዪም ረሒመሁሏህ እንዲህ ይላሉ : -
«የወንጀልህን መዘዝ አሁኑኑ ባለማየትህ አትታለል፣ ምናልባች ከአርባ አመታት በኋላ ሊሆን ይችላል የምታየው።»
📚 ۞ الـداء والـدواء【130】۞
🌿🌿🌿🍃ጥቆማ🍃🌿🌿🌿
🔻የአንዳንድ ሰው ዝምታ ከጩኸት በላይ ይሰማል ትርጉሙን ለመረዳት ግን ግንዛቤ ይሻል።
🔻 ሁለት ነገሮች ማንነትህ ግልፅ ያደርጋሉ፦
1.ምንም ነገር ሳይኖርህ የምታደርገው ሰብር
2.ሁሉም ነገር ሲኖርህ የምታሳየው ስነ ምግባር
https://t.me/ibnukedir
ኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር(አቡ ዓማር)
የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ (ከሰዎች መካከል የመልካም በር ከፋች የሆኑና የመጥፎ በር ዘጊዎች የሆኑ አሉ ፤ እንዲሁም ከሰዎች መካከል የሸር በር ከፋች የሆኑና የመልካም በር ዘጊ የሆኑ አሉ። አላህ የመልካም በር መክፈቻ ቁልፍ በእጁ ላደረገለት ‘ጡባ’ አለለት ፤ አላህ የመጥፎ በር መክፈቻ ቁልፍ በእጁ ላደረገለት ‘ወይል’ አለለት።) [ኢብኑ ማጃህ (237) ዘግበውታል።
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.