en
Feedback
Ethiopian Lecturers Voice

Ethiopian Lecturers Voice

Open in Telegram
9 638
Subscribers
No data24 hours
-117 days
-5330 days
Posts Archive
በዚህ ገፅ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። Be a leader there. Join now

ጋሽ ኮራ
+1
ጋሽ ኮራ

😡
😡

ሰላም ከ 1997 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2017 ዓ.ም የነበረ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ደሞዝ መረጃ ያለው @MESSAGEELABOT ላይ ላኩልን ከ1997 ዓም እስከ 2017 የሀገሪቱ በጀት አሀዛዊ ቁጥር ያለውም ላኩልን።

የዩኒቨርሲቲ መምህር ለመሆን ከጎበዝም በጣም 'ሰቃይ' ተማሪ መሆን አለብህ። እንዲያ ለመሆን ከፍተኛ ልፋት ይጠይቃል። የሕክምና ተማሪ ሆነህ ሰቅለህ በዩኒቨርሲቲዎች 9k/month እየተከፈለህ ሕክምና ተማሪዎችን ስታስተምር ደሞ አስበው። ጎበዝ ተማሪነት + ልፋት በተከበሩ ሙያዎች (ሕክምና፣ መምህርነት ...) ለማገልገል ሲውል የተቀናጣ ኑሮ ባያስኖር እንኳን እንዴት መሠረታዊ ፍላጎቶችን ለማሟላት ያንሳል? ጎበዝ! ህመምህ ሲጠና refer የሚፃፍልህ ወደነዚህ ሐኪሞች ነው፤ መገኛቸው ደሞ ግብር ከፍለን ወይም በእኛ ሥም ተጠይቆ በሚመጣ እርዳታ ወይም ብድር በሚተዳደሩ የሕዝብ ጤና ተቋማት ውስጥ ነው። 'መሰረታዊ ፍላጎቴን ማሟላት አልቻልኩም፤ መፍትሔ ስጡኝ' የሚለውን genuine የጤና ባለሙያዎች ጥያቄ 'ፖለቲካዊ ፍላጎት ያላቸው ...' የሚል ፍቺ በ360° ቢታሰብ አንድ ቀዳዳ እንኳን አይገኝም። ይህንን ጥያቄ ጠምዝዞ ለራሱ ጥቅም ሊጠቀምበት የሚሞክር በየትኛውም ወገን የሚገኝ ፖለቲከኛ የቤተሰቡ አካል ታሞ 'ማጣፊያው ይጠረው' ተብሎ አይረገም ነገር! 😥 እኔ ግብር ከፋይ ነኝ! መብቴን እጠይቃለሁ! የሕዝብ ጤና ተቋማት ውስጥ አገልግሎት ማግኘት ስለምፈልግ (ሙሉ መብቴም ስለሆነ for that matter) absolutely genuine የሆነው የጤና ባለሙያዎች የሕልውና ጥያቄ መልስ ይሰጠው! ይህ ተፈጥሮአዊ እንዲሁም በህገ-መንግሥቱ የተቀመጠ የግብር ከፋዮች የመብት ጥያቄ ነው። It has nothing to do with 'dirty' politics! Via ሀውለት ሙሀመድ

የተከበራችዉ እህቶቼ እና ወንድሞቼ እንደምን አመሻችዉ። የዛሬ የትምህርት ሚኒስቴር ዉሎዬን በአጭሩ እንደሚከተለዉ ቀነበብኩት፡ 1. የተከበሩ አቶ ኮራ ቢሮ ገብቼ ከኢመማ በ4/6/2017፣ በ10/7/2017 የተፃፉ ደብዳቤዎች የትደርሰዉ እንደሆነ ጠይቄ:1. በ4/6/2017 የተፃፈዉ ከኢመማ ጉዳዩ ከ2013 ጀምሮ የዩንቨርሲቲ መምህራንን ጥያቄዎች ያወሳና በ2015 ጠቅላዩ የጠየቁትን ጥያቄ አጉልቶ መፍትሄ ይጠይቃል። የመሬት ይሰጣቸዉ ጥያቄ ማለት ነዉ።ከአቶ ኮራ ቢሮ ለዶር ሶሎሞን ተመርቶ ዶር ሶሎሞን ለት/ት ሚኒስቴር አስተዳደር መርተዉታል። እንዲህ እና እንዲያ አድርገዉ ግን አይልም። ይሄንን የሚያክል ግዙፍ ጥያቄ የያዘ ደብዳቤ የማይሆን ቦታ ተወሽቋል። ጉዳዩን ከዶር ሶሎሞን ጋር ተወያይተን በሚቀጥለዉ ሳምንት እነ አቶ ኮራ ሲመለሱ ለክልል ፕሬዚዳንቶች ደብዳቤ እንደሚፅፉ ቃል ገብተዉልኛል። ቀጣይ መከታተል እና ማስፈፀም የኛ ድርሻ ነዉ። 2. ሁለተኛዉ ደብዳቤ የኢዩመማ ተሳትፎን ይመለከታል። የወሎ ዩንቨርሲቲዉን አቤቱታ ተከትሎ ኢመማ በ10/7/2017 የፃፈዉ ደብዳቤ ነዉ። ጉዳዩ ተሳትፎን ይመለከታል። ለአቶ ኮራ ቢሮ ከኢመማ ተፃፈ። አቶ ኮራ ለዶር ሶሎሞን መራዉ። ዶር ሶሎሞን ፋይል ዉስጥ እንዲታሰር ለፀሀፊዉ ሰጣት። ታስሮ አገኘዉትና ወደ ዶር ሶሎሞን መልሼ አስመራዉት። በተለያዩ ቦታዎች ዉስጥ ማለትም (ዝርዝሩን ሲሳይን አማክሬ እኔ ነኝ ያስገባሁት)፡ ሴኔት ፕሬዚዳንቱ እና የሴቶች ጉዳይ እንዲገቡ፣ AC, recruitment,  housing, promotion, position, discipline, research and community engagement committee, በሚባሉ ቦታዎች እንዲያስገቡን ደብዳቤዉን ቁጭ ብዬ ካፃፍኩኝ በኋላ የበረራ ሰዓቴ ስለደረሰ ወጥቼ ወደጅማ መጥቻለዉ። በሚቀጥሉት ቀናት ይደርሳቸዋል። 3. ትላንትና ከምሽቱ ሁለት ተኩል የስራአስፈፃሚ ስብሰባ ነበረብን። እና በማደራጀት ስራችን ላይ እንቅፋት ከሆኑብን ጉዳዮች ዉስጥ የፕሬዚዳንቶች ፈቃደኝነት ማጣት ስለነበር በነዚህ ሰዎች ዙርያ ምን ማድረግ እንዳለብን ከዶር ሶሎሞን ጋር ተወያይተን አስቸግረዉናል ብላችዉ የምታስቧቸዉን ዩንቨርሲቲዎች ለይታችዉ ንገሩን እኛ እንደዉልላቸዋለን ብሎ ስልኩን ሰጥቶኛል። እንግዲህ ከሞላ ጎደል ከኢመማ ተፅፈዉ ስርቻ ስር ከተወረወሩት ደብዳቤዎች ሁለቱን ህይወት ዘርተንበታል ማለት ነዉ። ዝርዝር አበዛዉ ይቅርታ።

#ማስታወቂያ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ከዩኒቨርሲቲው መምህራንና ቋሚ የአስተዳደር ሠራተኞች ጋር አርብ ግንቦት 08/2017 ዓ.ም ከቀኑ 7:30 በዋና ግቢ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ አዳራሽ በተቋማዊ የስራ ጉዳዮች ዙሪያ የውይይትና የምክክር መድረክ ስለሚኖር ሁላችሁም እንድትገኙ እናሳውቃለን። የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር Let Your Light Shine in the Society!

ማንኛውንም የመምህራንን መብት ለማስከበር እና ለማታገል ያለመ የቴሌግራምም ሆነ ፌስቡክ ገፅ ግሩፕ ላይ ለጥፉልን። We will promote it. የተደበቃችሁ መሪዎች ብቅ በሉ። @EUASAs

በጣም ከሚያስገርሙ የሀኪሞች እንቅስቃሴ ውስጥ እጅግ በጣም ብዙ የሀኪሞች የፌስቡክ ገፆች አሉ። እርስ በርሳቸው ተመጋጋቢዎች ናቸው። እርስዎ ይሄን አስተውለዋል?
Anonymous voting

ትግል ዘርፈ ብዙ መሆኑ ጥሩ ነው። ተቀላቀሉ። ሁሉም ባመነበት ይቀጥል። 1ኛው. ዲፕሎማሲ 2ኛው. ሚዛን ማስጠበቅ እርስ በርስ ያለመፈራረጅ በአንድነት እንስራ። መልካም የትግል ምዕራፍ። #NowOrNever

የተከበራችሁ የዩንቨርስቲ መምህራን ሆይ ትላንት አብረውን የነበሩ የመምህሩን ጥያቄ ያስተባበሩ ዛሬ ኢመማ መድህናችን እያሉ አብረን በጋራ የምናስተዳድረው ቴሌግራም የተጠለፈ በመሆኑ ቁርጠኛ ለመታገል የወሰናችሁ በዚህ አዲስ ቴሌግራም ተቀላቀሉን።አንድ ሰው ለ50ሰው ሼር ያድርግ ወይ ቆርጠን መብታችን ለማስከበር እንነሳ ወይ ፀጥ እንበል ምርጫው በእጃችሁ ነው።መብትህን በነፃ አታገኝም።ቼ-ጉቬራው ከየት ይመጣል?ቼ-ጉቬራው እራስህ ነህ።https://t.me/+nqZomRhDtnFmY2Zk

"ለመምህራኑ በሚጠቅም አግባብ እየሰራን ነው በፊት የሄድንበትን መድገም አያስፈልግም !!!" ሰላም

ይህ ውይይት May 03 ገደማ የተደረገ ነው። የውይይቱ ፍሬ ጭብጥን ባልታወቀበት ሁኔታ "አጠቃላይ ስብሰባ መጥራትና አንድ አቋም እንደ ሀኪሞች እንያዝ ለሚሉ ሀሳቦች" ማነቆ ነው። የመምህራን ማህበር ፕሬዝዳንቶች የሚሰጡትን ሀሳብ መጠየቅና አብሮ መስራት ይሻላል። ሰላም

የዩኒቨርስቲዎች መምህራ ማህበር ፕሬዚደንትዎች የምክክር መድረክ በዚህ መልኩ በሳል ውይይቶች በማረግ ተጠናቋል!!!
+4
የዩኒቨርስቲዎች መምህራ ማህበር ፕሬዚደንትዎች የምክክር መድረክ በዚህ መልኩ በሳል ውይይቶች በማረግ ተጠናቋል!!!

ELA group ላይ ዉይይት እየተደረገ ነው። ሀሳባችሁን ማካፈል ትችላላችሁ። Join the group in the comment section and join the meeting.