የተ/ኢ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል
Open in Telegram
ይህ የቴሌግራም ገጽ በቦሌ ደ/ም/ቅ/ሚካኤል እና ጻ/አ/ጎርጎርዮስ ቤተ ክርስቲያን ተስፋ ኢየሩሳሌም ሰንበት ትምህርት ቤት ፈቃድ ለትምህርት ክፍል ጥቅምት 13 ቀን 2015 ዓ.ም ተከፈተ ። በዚህ ገጽ - በአምድ የተከፋፈሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት የጠበቁ ትምህርቶችን እናሰራጫለን፡፡
Show more436
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+2030 days
Posts Archive
እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች! እንኳን ለሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በሰላም አደረሳችሁ።
📌 እንደ አምላካችን ፈቃድ ነገ እሑድ ጳጉሜን 03/2016 ዓ.ም ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
• ካልዓይ ክፍሎች:- የቤ/ክ ታሪክ በኢትዮዽያ
መርሐግብር መሪ:- ቅዱስ ሙሉጌታ
• ሣልሳይ ክፍል: የቤ/ክ ታሪክ በኢትዮጲያ በመ/ር ዮናስ
መርሐግብር መሪ: ሀብታሙ ድንቁ
• ራብዓይ ክፍል: የሕይወት ትምህርት በዲ/ን አብርሐም
መርሐግብር መሪ:- አቶ አብርሐም ቲመርጋ
✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨
#ትምህርት_ክፍል
እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች!
📌 እንደ አምላካችን ፈቃድ ነገ እሑድ ነሐሴ 19 ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
• ካልዓይ ክፍሎች:- የቤ/ክ ታሪክ በዓለም በኢትዮዽያ የመጨረሻ ክፍል
መርሐግብር መሪ:- ሚኪያስ ተስፋነህ
• ሣልሳይ ክፍልእና ራብዓይ ክፍል: መንፈሳዊው ሰው ክፍል 4 (የመጨረሻ ክፍል)
መርሐግብር መሪ:- ዲ/ን አቤሜሌክ ጌታቸው
✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨
#ትምህርት_ክፍል
✞✞✞ 🌷በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞🌷
❖ ነሐሴ ፲፮ ❖
✞✞✞ እንኩዋን ለእመቤታችን
#ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የትንሳኤና የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞
+"+ #🌷ዕርገተ_ድንግል_ማርያም🌷 +"+
=>ይሕች ዕለት እጅጉን ታላቅና ክብርት ናት:: ምክንያቱም
የድንግል ማርያም ሥጋዋ ተነስቶ ዐርጐባታልና:: ድንግል
እመቤታችን ተነሳች: ዐረገች ስንል እንደ እንግዳ ደርሶ:
እንደ ውሃ ፈሶ: ወይም በአጋጣሚ የተደረገ አይደለም::
ጥንቱን በአምላክ ልቡና ታስቦ: ሁዋላም ትንቢት
ተነግሮለት ነው::
¤ታሪኩ: ነገሩ: ምሥጢሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅድመ ዓለም
በአምላክ ልቡና ታስባ ትኖር ነበር:: ከነገር ሁሉ በፊት
#እግዚአብሔር እናቱን ያውቃት ነበር::
¤ዓለም ተፈጥሮ: አዳምና ሔዋን ስተው: መርገመ ሥጋና
መርገመ ነፍስ አግኝቷቸው: በኃዘን ንስሃ ቢገቡ
"እትወለድ እም ወለተ ወለትከ - ከ5 ቀን ተኩል (5500
ዘመናት) በሁዋላ ካንተ ባሕርይ ከምትገኝ #ንጽሕት_ዘር
ተወልጄ አድንሃለሁ" ብሎ ተስፋ ድኅነት ሰጠው::
¤ከአዳም አንስቶ ለ5500 ዓመታት አበው: ነቢያትና
ካህናት ስለ ድንግል ማርያም ብዙ ሐረገ ትንቢቶችን
ተናገሩ:: መዳኛቸውን ሱባኤ ቆጠሩላት:: ምሳሌም
መሰሉላት:: ከሩቅ ዘመን ሁነውም ሊያገኟት እየተመኙ
እጅ ነሷት::
"እምርሑቅሰ ርእይዋ: ወተአምኅዋ" እንዲል::
+"+ የድንግል ማርያም ሐረገ ትውልድ +"+
*ከአዳም በሴት
*ከያሬድ በሔኖክ
*ከኖኅ በሴም
*ከአብርሃም በይስሐቅ
*ከያዕቆብ በይሁዳና በሌዊ
*ከይሁዳ በእሴይ: በዳዊት: በሰሎሞንና በሕዝቅያስ
ወርዳ ከኢያቄም ትደርሳለች::
¤ከሌዊ ደግሞ #በአሮን: #አልዓዛር: #ፊንሐስ:
#ቴክታና_በጥሪቃ አድርጋ ከሐና ትደርሳለች::
¤አባታችን #አዳም ከገነት በወጣ በ5,485 ዓመት
#ወላዲተ_አምላክ ንጽሕና ሳይጐድልባት: ኃጢአት
ሳያገኛት: ጥንተ አብሶ ሳይደርስባት ከደጋጉ
#ኢያቄም_ወሐና ትወለዳለች:: (ኢሳ. 1:9, መኃ. 4:7)
"ወኢረኩሰት በምንትኒ እምዘፈጠራ" እንዳለ::
(#ቅዱስ_ቴዎዶጦስ_ዘዕንቆራ)
¤ከዚያም ከእናት ከአባቷ ቤት ለ3 ዓመታት ቆይታ ወደ
#ቤተ_መቅደስ ትገባለች:: በቤተ መቅደስም ለ12
ዓመታት ፈጣሪዋን እግዚአብሔርን እያመሰገነችና
እያገለገለች: እርሷን ደግሞ #መላእክተ_ብርሃን
እያገለገሏት: ሕብስት ሰማያዊ: ጽዋዕ ሰማያዊ
እየመገቧት ኑራለች:: 15 ዓመት በሞላት ጊዜ ጻድቅ
#አረጋዊ_ዮሴፍ ያገለግላት ዘንድ ወደ ቤቱ ወሰዳት::
¤በዚያም መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ዜና
ድኅነትን ነግሯት አካላዊ ቃልን በማሕጸንዋ ጸነሰችው::
ነደ እሳትን ተሸከመችው: ቻለችው:: "ጾርኪ ዘኢይትጸወር:
ወአግመርኪ ዘኢይትገመር" እንዳለ::
(#ሊቁ_ቅዱስ_ኤፍሬም #ለብሐዊ)
¤ወልደ እግዚአብሔርን ለ9 ወራት ከ5 ቀናት ጸንሳ:
እንበለ ተፈትሆ (በድንግልና) ወለደችው:: (ኢሳ. 7:14)
"#ኢየሱስ" ብላ ስም አውጥታለት በናዝሬት ገሊላ ለ2
ዓመታት ቆዩ::
¤አርዌ ሔሮድስ "እገድላለሁ" ብሎ በተሳበት ወቅትም
ልጇን አዝላ በረሃብ እና በጥም: በላበትና በድካም:
በዕንባና በኃዘን ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት ከገሊላ እስከ
#ኢትዮዽያ ተሰዳለች:: ልጇ ጌታችን 5 ዓመት ከ6 ወር
ሲሆነው: ለርሷ ለድንግል ደግሞ 21 ዓመት ከ3 ወር
ሲሆናት ወደ ናዝሬት ተመለሱ::
¤በናዝሬትም ለ24 ዓመታት ከ6 ወራት ልጇን ክርስቶስን
እያሳደገች: ነዳያንን እያሰበች ኑራለች::
እርሷ 45 ዓመት: ልጇ 30 ዓመት ሲሆናቸው ጌታችን
ተጠምቆ በጉባኤ ትምሕርት: ተአምራት ጀመረ:: ለ3
ዓመታት ከ3 ወራትም ከዋለበት እየዋለች: ካደረበትም
እያደረች ትምሕርቱን ሰማች::
¤የማዳን ቀኑ ደርሶ ልጇ ክርስቶስ ሲሰቀልም
የመጨረሻውን ፍጹም ሐዘን አስተናገደች:: አንጀቷ በኃዘን
ተቃጠለ:: በነፍሷም ሰይፍ አለፈ:: (ሉቃ. 2:35) ጌታ
በተነሳ ጊዜም ከፍጥረት ሁሉ ቀድማ ትንሳኤውን አየች::
ለ40 ቀናትም ሳትለይ ከልጇ ጋር ቆየች::
¤ከልጇ #ዕርገት በሁዋላ #በጽርሐ_ጽዮን ሐዋርያትን
ሰብስባ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ አበቃች:: በጽርሐ ጽዮን
ከአደራ ልጇ ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ለ15 ዓመታት ኖረች::
በእነዚህ ዓመታት ሥራ ሳትፈታ ስለ ኃጥአን ስትማልድ:
ቃል ኪዳንን ከልጇ ስትቀበል: ሐዋርያትን ስታጽናና:
ምሥጢርም ስትገልጽላቸው ኑራለች::
¤ዕድሜዋ 64 በደረሰ ጊዜ ጥር 21 ቀን #መድኃኒታችን
አእላፍ ቅዱሳንን አስከትሎ መጣ:: ኢየሩሳሌምን
ጨነቃት:: አካባቢውም በፈውስ ተሞላ:: በዓለም ላይም
በጐ መዓዛ ወረደ:: እመ ብርሃን ለፍጡር ከዚያ በፊት
ባልተደረገ: ለዘለዓለምም ለማንም በማይደረግ ሞገስ:
ክብርና ተአምራት ዐረፈች:: ሞቷ ብዙዎችን አስደንቁአል::
"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ:
ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ" እንዲል::
¤ከዚህ በሁዋላ መላእክት እየዘመሩ: ሐዋርያቱም
እያለቀሱ ወደ ጌቴሴማኒ: በአጐበር ሥጋዋን ጋርደው
ወሰዱ:: ይሕንን ሊቃውንት:-
"ሐራ ሰማይ ብዙኃን እለ አልቦሙ ሐሳበ:
እንዘ ይዜምሩ ቅድሜኪ ወመንገለ ድኅሬኪ ካዕበ:
ማርያም ሞትኪ ይመስል ከብካበ" ሲሉ ይገልጡታል::
¤በወቅቱ ግን አይሁድ በክፋት ሥጋዋን እናቃጥል ስላሉ
#ቅዱስ_ገብርኤል (ጠባቂ መልአክ ነው) እነርሱን ቀጥቶ
እርሷን ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ወስዶ በዕጸ ሕይወት ሥር
አኑሯታል::
በዚያም #መላእክት እያመሰገኗት ለ205 ቀናት
ቆይታለች::
¤#ቅዱስ_ዮሐንስ መጥቶ ለሐዋርያቱ ክብረ ድንግልን
ቢነግራቸው በጐ ቅንአት ቀንተው በነሐሴ 1 ሱባኤ
ጀመሩ:: 2ኛው ሱባኤ ሲጠናቀቅም ጌታ የድንግል
ማርያምን #ንጹሕ_ሥጋ ሰጣቸው:: እየዘመሩም
#በጌሴማኒ ቀብረዋታል::
¤በ3ኛው ቀን (ነሐሴ 16) እንደ ልጇ ባለ #ትንሳኤ
ተነስታ ዐርጋለች:: ትንሳኤዋንና ዕርገቷንም ደጉ ሐዋርያ
#ቅዱስ_ቶማስ አይቶ: መግነዟን ተቀብሏል:: ሐዋርያቱም
መግነዟን ለበረከት ተካፍለው: እንደ ገና በዓመቱ ነሐሴ
1 ቀን ሱባኤ ገቡ::
¤ለ2 ሳምንታት ቆይተው: በዚህች ቀንም ሁሉንም ወደ
ሰማይ አወጣቸው:: በፍጡር አንደበት ተከናውኖ
የማይነገር ተድላ: ደስታና ምሥጢርንም አዩ:: ጌታ ራሱ
ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው:: የበዓሉን ቃል ኪዳን
ሰምተው: ከድንግል ተባርከው ወደ #ደብረ_ዘይት
ተመልሰዋል::
=>ጽንዕት በድንግልና: ሥርጉት በቅድስና #እመቤታችን:
ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን:
ለብዎውን: ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን::
እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች!
እንኳን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ወርሐዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
📌 እንደ አምላካችን ፈቃድ ነገ እሑድ ነሐሴ 12 ለሁሉም ክፍላት የሕይወት ትምህርት በዲ/ን አብርሐም ስለሚኖር በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
• መርሐግብር መሪ :-ቴዎድሮስ አለምሰገድ
✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨
#ትምህርት_ክፍል
እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች!
📌 እንደ አምላካችን ፈቃድ ነገ እሑድ ሐምሌ 28 ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
• ካልዓይ ክፍሎች:- የቤ/ክ ታሪክ በዓለም በኢትዮዽያ
መርሐግብር መሪ:- ብስራት ቴዎድሮስ
• ሣልሳይ ክፍል እና ራብዓይ ክፍል: መንፈሳዊው ሰው ክፍል 3 (የመጨረሻ ክፍል)
መርሐግብር መሪ:- ዲ/ን ዘሪሁንወ/ማርያም
✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨
#ትምህርት_ክፍል
📌16ኛ ዙር የርቀት ትምህርት
ነገረ ክርስቶስ
በዲ/ን ያደሳ
⏰ እሑድ ሐምሌ 28/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8-10 ሰዓት
በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ ⛪️
#ትምህርት_ክፍል
https://t.me/tmhrt12
እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች!
📌 እንደ አምላካችን ፈቃድ ነገ እሑድ ሐምሌ 21 ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨
#ትምህርት_ክፍል
†††✝ እንኳን ለቅዱሳኑ ገብርኤል ሊቀ መላእክት: ቂርቆስ ወኢየሉጣ: በጥላን ጠቢብ እና ሰማዕታተ እስና ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††
††† ✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን✝! †††
†††✝ ቅዱሳን ቂርቆስ ወኢየሉጣ: ወቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት †††✝
††† ቅድስት ኢየሉጣ እናታችን በዘመነ ሰማዕታት ከነበሩና በዚህ ስም ከሚጠሩ ቅዱሳት አንዷ ናት:: በወቅቱ ቅዱስ ቂርቆስ የሚባል ደግ ልጅ ወልዳ ባሏ ባለመኖሩ በመበለትነት ትኖር ነበር:: የዚያ ዘመን ክርስቲያኖች ለክርስቶስ የነበራቸው ፍቅር ከመነገር በላይ ነው:: በዛው ልክ ደግሞ መከራው በጸጉራቸው ቁጥር ልክ ነበር::
ከሮም ግዛት በአንዱ ከቅዱስ ልጇ ጋር የምትኖረው ቅድስት ኢየሉጣ የስደቱ ዘመን ሲመጣ እርሷም እንደ ሌሎቹ ክርስቲያኖች ተሰደደች:: እስክንድሮስ የተባለው ከሃዲ ንጉሥ ግን ያለችበት ድረስ ተከትሎ እንድትያዝና እንድትቀርብ አደረገ::
ወዲያውም "ስምሽ ማን ይባላል?" ቢላት "ክርስቲያን እባላለሁ" አለችው:: ንጉሡ ተቆጣ:: "መዋቲ ስሜን ከፈለክ ኢየሉጣ ይባላል" አለችው:: ንጉሡ መልሶ "አሁን ለጣዖት ካልሠዋሽ ሲጀመር ስቃይ: ቀጥሎም ሞት ይጠብቅሻል" ቢላት ቅድስቲቱ መልሳ "በከተማ ውስጥ የሦስት ዓመት ሕፃን አለና እርሱን አምጣው:: ማንን ማምለክ እንዳለብን ይነግረናል" አለችው::
አስፈልጐ ቅዱስ ቂርቆስን አስመጣው:: "ስምህ ማን ይባላል?" አለ ንጉሡ:: "ከማይደፈርስ ከንጹሕ ምንጭ የተቀዳ ጥሩ ምንጭ ስሜ ክርስቲያን ይባላል:: መዋቲ ስሜን ከፈለግህ ግን ቂርቆስ ይባላል" አለው::
ንጉሡ ሊያታልለው "ደስ የተሰኘህ ሕፃን" ቢለው ቅዱሱ ሕፃን "ትክክል ተናገርክ: ለእኔ በሰማያት ደስታ ይጠብቀኛል:: አንተ ግን እውነተኛው አምላክ ይፈርድብሃል" አለው:: በሦስት ዓመት ሕፃን አንደበት ዘለፋ የገጠመው ከሃዲ ተቆጣ::
እናትና ልጅን በብዙ መክፈልተ ኩነኔ አሰቃያቸው::
ሰውነታቸውን ቸነከረ: አካላቸውን ቆራረጠ: ዓይናቸውን አወጣ:: ሌላም ሊናገሩት የሚጨንቅ ስቃይን አሰቃያቸው:: በዚህች ቀን ግን ትልቅ ድስት አሰርቶ ባሩድ: አረር: ስብና የመሳሰሉትን ጨምረውበት በእሳት አፈሉት::
የእሳቱ ወላፈን አካባቢውን በላው:: በድስቱ ውስጥ ያለው ነገር እየፈላ ሲገላበጥ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ይጮህ ነበር:: የስድስት ሰዓት የእግር መንገድ ድረስም ተሰምቷል:: ቅድስት ኢየሉጣ ይሔኔ ነበር ልቧ ድንግጥ ያለው:: ሕፃኑ ቂርቆስ የእናቱን ፍርሃት ሲመለከት ጸለየ::
"ፈጣሪዬ! ፍሬው ያለ ግንዱ አይቆምምና እኔን እንዳጸናሕ እናቴንም አጽናት" ሲል ለመነ::
"እግዚኦ ትፈቅድኑ ለፍሬሁ ተአልዶ:
እንዘ በእሳት ታውኢ ጉንዶ" እንዲል::
በዚያች ሰዓት ቅድስት ኢየሉጣ ዓይኖቿ ተከፍተው ሰማያዊ ክብርን ተመለከቱና ልቧ ወደ ድፍረቱ ተመለሰ::
ልጇንም "አንተ አባቴ ነህ: አንተን የተሸከመች ማኅጸኔ የተባረከች ናት" አለችው:: ከዚያም ሁለቱንም ወደ ፈላው ድስት ውስጥ ቢጨምሯቸው ፍጡነ ረድኤት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደላቸው:: በበትረ መስቀሉ ባርኮ የፈላውን አቀዘቀዘው:: የነደደውን ውኃ አደረገው:: ቅዱሳኑ ቂርቆስና ኢየሉጣ ከብዙ መከራ በኋላ በሰማዕትነት አልፈዋል::
††† "ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ: ወይስ ጭንቀት: ወይስ ስደት: ወይስ ራብ: ወይስ መራቆት: ወይስ ፍርሃት: ወይስ ሰይፍ ነውን?
'ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን:: እንደሚታረዱ በጐች ተቆጠርን::' ተብሎ እንደተጻፈው ነው::
በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን::" †††
(ሮሜ. ፰፥፴፭-፴፯)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††
እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች!
📌 እንደ አምላካችን መልካም ፈቃድ ነገ እሑድ ሐምሌ 14 ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
• ካልዓይ ክፍሎች:- የቤ/ክ ታሪክ በዓለም በኢትዮዽያ
መርሐግብር መሪ:- ዲ/ን ኤልያስ
• ሣልሳይ ክፍል:- የቤ/ክ ታሪክ በኢትዮዽያ
መርሐግብር መሪ: ሀብታሙ
• ራብዓይ ክፍል: መንፈሳዊው ሰው ክፍል
መርሐግብር መሪ:- ዲ/ን አቤሜሌክ
✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨
#ትምህርት_ክፍል
እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች!
📌 እንደ አምላካችን መልካም ፈቃድ ነገ እሑድ ሐምሌ 07 ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
• ካልዓይ ክፍሎች:- የቤ/ክ ታሪክ በዓለም በኢትዮዽያ እና ፈተና
መርሐግብር መሪ:- ዳዊት አረጋ
• ሣልሳይ ክፍል:- የቤ/ክ ታሪክ በኢትዮዽያ
መርሐግብር መሪ: ኃይለ ኢየሱስ
• ራብዓይ ክፍል: መንፈሳዊው ሰው
መርሐግብር መሪ:- ሀብታሙ አበበ
✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨
#ትምህርት_ክፍል
እንደምን አመሻችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች?
ይህ መልዕክት ካልዓይ ክፍሎችን የሚመለከት ነው።
📍በባለፈው ሳምንት ሊሰጥ የነበረው የቤ/ክ ታሪክ ፈተና በነበረው ጉዞ ምክንያት ሊሰጥ ስላልቻለ የፊታችን እሑድ በ07/2016 ዓ.ም ስለሚሰጥ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
#ትምህርት_ክፍል
እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች!
እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓነታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
📌 እንደ አምላካችን መልካም ፈቃድ ነገ እሑድ ሰኔ 30 ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
• ካልዓይ ክፍሎች:- የቤ/ክ ታሪክ በዓለም መድረክ ፈተና
መርሐግብር መሪ:- ቅዱስ ሙሉጌታ
• ሣልሳይ ክፍል:- የቤ/ክ ታሪክ በኢትዮዽያ
መርሐግብር መሪ: ሱራፌል ፈቃዱ
• ራብዓይ ክፍል:የሕይወት ትምህርት
መርሐግብር መሪ:- መለሰ ፈይሳ
📍ሣልሳይ እና ካልዓይ ክፍሎች ነገ ከሰ/ት/ቤቱ ጽሕፈት ቤት ጋር በአገልግሎት ዙሪያ ውውይት ስለሚኖር ከኮርስ በኃላ ትቆዩ ዘንድ በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨
#ትምህርት_ክፍል
❗️ማሳሰኒያ ለካልዓይ ክፍሎች።
እንደ አምላካችን መልካም ፈቃድ እሑድ በ30 የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ የማጠቃለያ ፈተና ይኖራል፡፡ መቅረት እንዳማቻል በጥብቅ እያሳሰብን በዕለቱ ፈተና ላመለጣችሁ ደግመን አንፈትንም።
#ትምህርት_ክፍል
•ጉባኤ ኄራኒ•
ሴቶች በጓደኝነትሕይወት
ከኤልሳቤጥ አያሌውጋር
🗓 እሑድ 30/10/2016 ዓ.ም
⏰12 ሰዓት
📍በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ
📌 ማሳሰቢያ:
ማስታወሻ ያዙ።
በማኅበራዊ ሚድያ ገጾቻችን ቤተሰብ ይኹኑ:
የቴሌግራም ገጻችን: https://t.me/tjss12
የfacebook ገጻችን: https://www.facebook.com/profile.php?id=100066679875652&mibextid=PzaGJu
የቲክ ቶክ ገጻችን: https://www.tiktok.com/@tesfajerusalem?_t=8l9xP7zCJID&_r=1
የyoutube ገጻችን: https://youtube.com/@tesfajerusalem?si=RX3EqYGfWW8EDqtu
የሰ/ት/ቤቱ ስልክ ቁጥር: +251921247777
ኢሜል አድራሻ: tesfajerusalem1221@gmail.com
📌15ኛ ዙር የርቀት ትምህርት
ነገረ ቅዱሳን
በዲ/ን አለምሰገድ
⏰ እሑድ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8-10 ሰዓት
በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ ⛪️
#ትምህርት_ክፍል
https://t.me/tmhrt12
