en
Feedback
የተ/ኢ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል

የተ/ኢ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል

Open in Telegram

ይህ የቴሌግራም ገጽ በቦሌ ደ/ም/ቅ/ሚካኤል እና ጻ/አ/ጎርጎርዮስ ቤተ ክርስቲያን ተስፋ ኢየሩሳሌም ሰንበት ትምህርት ቤት ፈቃድ ለትምህርት ክፍል ጥቅምት 13 ቀን 2015 ዓ.ም ተከፈተ ። በዚህ ገጽ - በአምድ የተከፋፈሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት የጠበቁ ትምህርቶችን እናሰራጫለን፡፡

Show more
436
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+2030 days
Posts Archive
እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች! እንኳን ለሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በሰላም አደረሳችሁ። 📌 እንደ አምላካችን ፈቃድ ነገ እሑድ ጳጉሜን 03/2016 ዓ.ም ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። • ካልዓይ ክፍሎች:- የቤ/ክ ታሪክ በኢትዮዽያ መርሐግብር መሪ:- ቅዱስ ሙሉጌታ • ሣልሳይ ክፍል: የቤ/ክ ታሪክ በኢትዮጲያ በመ/ር ዮናስ መርሐግብር መሪ: ሀብታሙ ድንቁ • ራብዓይ ክፍል: የሕይወት ትምህርት በዲ/ን አብርሐም መርሐግብር መሪ:- አቶ አብርሐም ቲመርጋ ✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨ #ትምህርት_ክፍል

እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች! 📌 እንደ አምላካችን ፈቃድ ነገ እሑድ ነሐሴ 19 ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። • ካልዓይ ክፍሎች:- የቤ/ክ ታሪክ በዓለም በኢትዮዽያ የመጨረሻ ክፍል መርሐግብር መሪ:- ሚኪያስ ተስፋነህ • ሣልሳይ ክፍልእና ራብዓይ ክፍል: መንፈሳዊው ሰው ክፍል 4 (የመጨረሻ ክፍል) መርሐግብር መሪ:- ዲ/ን አቤሜሌክ ጌታቸው ✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨ #ትምህርት_ክፍል

✞✞✞ 🌷በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞🌷 ❖ ነሐሴ ፲፮ ❖ ✞✞✞ እንኩዋን ለእመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የትንሳኤና የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞ +"+ #🌷ዕርገተ_ድንግል_ማርያም🌷 +"+ =>ይሕች ዕለት እጅጉን ታላቅና ክብርት ናት:: ምክንያቱም የድንግል ማርያም ሥጋዋ ተነስቶ ዐርጐባታልና:: ድንግል እመቤታችን ተነሳች: ዐረገች ስንል እንደ እንግዳ ደርሶ: እንደ ውሃ ፈሶ: ወይም በአጋጣሚ የተደረገ አይደለም:: ጥንቱን በአምላክ ልቡና ታስቦ: ሁዋላም ትንቢት ተነግሮለት ነው:: ¤ታሪኩ: ነገሩ: ምሥጢሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅድመ ዓለም በአምላክ ልቡና ታስባ ትኖር ነበር:: ከነገር ሁሉ በፊት #እግዚአብሔር እናቱን ያውቃት ነበር:: ¤ዓለም ተፈጥሮ: አዳምና ሔዋን ስተው: መርገመ ሥጋና መርገመ ነፍስ አግኝቷቸው: በኃዘን ንስሃ ቢገቡ "እትወለድ እም ወለተ ወለትከ - ከ5 ቀን ተኩል (5500 ዘመናት) በሁዋላ ካንተ ባሕርይ ከምትገኝ #ንጽሕት_ዘር ተወልጄ አድንሃለሁ" ብሎ ተስፋ ድኅነት ሰጠው:: ¤ከአዳም አንስቶ ለ5500 ዓመታት አበው: ነቢያትና ካህናት ስለ ድንግል ማርያም ብዙ ሐረገ ትንቢቶችን ተናገሩ:: መዳኛቸውን ሱባኤ ቆጠሩላት:: ምሳሌም መሰሉላት:: ከሩቅ ዘመን ሁነውም ሊያገኟት እየተመኙ እጅ ነሷት:: "እምርሑቅሰ ርእይዋ: ወተአምኅዋ" እንዲል:: +"+ የድንግል ማርያም ሐረገ ትውልድ +"+ *ከአዳም በሴት *ከያሬድ በሔኖክ *ከኖኅ በሴም *ከአብርሃም በይስሐቅ *ከያዕቆብ በይሁዳና በሌዊ *ከይሁዳ በእሴይ: በዳዊት: በሰሎሞንና በሕዝቅያስ ወርዳ ከኢያቄም ትደርሳለች:: ¤ከሌዊ ደግሞ #በአሮን: #አልዓዛር: #ፊንሐስ: #ቴክታና_በጥሪቃ አድርጋ ከሐና ትደርሳለች:: ¤አባታችን #አዳም ከገነት በወጣ በ5,485 ዓመት #ወላዲተ_አምላክ ንጽሕና ሳይጐድልባት: ኃጢአት ሳያገኛት: ጥንተ አብሶ ሳይደርስባት ከደጋጉ #ኢያቄም_ወሐና ትወለዳለች:: (ኢሳ. 1:9, መኃ. 4:7) "ወኢረኩሰት በምንትኒ እምዘፈጠራ" እንዳለ:: (#ቅዱስ_ቴዎዶጦስ_ዘዕንቆራ) ¤ከዚያም ከእናት ከአባቷ ቤት ለ3 ዓመታት ቆይታ ወደ #ቤተ_መቅደስ ትገባለች:: በቤተ መቅደስም ለ12 ዓመታት ፈጣሪዋን እግዚአብሔርን እያመሰገነችና እያገለገለች: እርሷን ደግሞ #መላእክተ_ብርሃን እያገለገሏት: ሕብስት ሰማያዊ: ጽዋዕ ሰማያዊ እየመገቧት ኑራለች:: 15 ዓመት በሞላት ጊዜ ጻድቅ #አረጋዊ_ዮሴፍ ያገለግላት ዘንድ ወደ ቤቱ ወሰዳት:: ¤በዚያም መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ዜና ድኅነትን ነግሯት አካላዊ ቃልን በማሕጸንዋ ጸነሰችው:: ነደ እሳትን ተሸከመችው: ቻለችው:: "ጾርኪ ዘኢይትጸወር: ወአግመርኪ ዘኢይትገመር" እንዳለ:: (#ሊቁ_ቅዱስ_ኤፍሬም #ለብሐዊ) ¤ወልደ እግዚአብሔርን ለ9 ወራት ከ5 ቀናት ጸንሳ: እንበለ ተፈትሆ (በድንግልና) ወለደችው:: (ኢሳ. 7:14) "#ኢየሱስ" ብላ ስም አውጥታለት በናዝሬት ገሊላ ለ2 ዓመታት ቆዩ:: ¤አርዌ ሔሮድስ "እገድላለሁ" ብሎ በተሳበት ወቅትም ልጇን አዝላ በረሃብ እና በጥም: በላበትና በድካም: በዕንባና በኃዘን ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት ከገሊላ እስከ #ኢትዮዽያ ተሰዳለች:: ልጇ ጌታችን 5 ዓመት ከ6 ወር ሲሆነው: ለርሷ ለድንግል ደግሞ 21 ዓመት ከ3 ወር ሲሆናት ወደ ናዝሬት ተመለሱ:: ¤በናዝሬትም ለ24 ዓመታት ከ6 ወራት ልጇን ክርስቶስን እያሳደገች: ነዳያንን እያሰበች ኑራለች:: እርሷ 45 ዓመት: ልጇ 30 ዓመት ሲሆናቸው ጌታችን ተጠምቆ በጉባኤ ትምሕርት: ተአምራት ጀመረ:: ለ3 ዓመታት ከ3 ወራትም ከዋለበት እየዋለች: ካደረበትም እያደረች ትምሕርቱን ሰማች:: ¤የማዳን ቀኑ ደርሶ ልጇ ክርስቶስ ሲሰቀልም የመጨረሻውን ፍጹም ሐዘን አስተናገደች:: አንጀቷ በኃዘን ተቃጠለ:: በነፍሷም ሰይፍ አለፈ:: (ሉቃ. 2:35) ጌታ በተነሳ ጊዜም ከፍጥረት ሁሉ ቀድማ ትንሳኤውን አየች:: ለ40 ቀናትም ሳትለይ ከልጇ ጋር ቆየች:: ¤ከልጇ #ዕርገት በሁዋላ #በጽርሐ_ጽዮን ሐዋርያትን ሰብስባ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ አበቃች:: በጽርሐ ጽዮን ከአደራ ልጇ ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ለ15 ዓመታት ኖረች:: በእነዚህ ዓመታት ሥራ ሳትፈታ ስለ ኃጥአን ስትማልድ: ቃል ኪዳንን ከልጇ ስትቀበል: ሐዋርያትን ስታጽናና: ምሥጢርም ስትገልጽላቸው ኑራለች:: ¤ዕድሜዋ 64 በደረሰ ጊዜ ጥር 21 ቀን #መድኃኒታችን አእላፍ ቅዱሳንን አስከትሎ መጣ:: ኢየሩሳሌምን ጨነቃት:: አካባቢውም በፈውስ ተሞላ:: በዓለም ላይም በጐ መዓዛ ወረደ:: እመ ብርሃን ለፍጡር ከዚያ በፊት ባልተደረገ: ለዘለዓለምም ለማንም በማይደረግ ሞገስ: ክብርና ተአምራት ዐረፈች:: ሞቷ ብዙዎችን አስደንቁአል:: "ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ: ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ" እንዲል:: ¤ከዚህ በሁዋላ መላእክት እየዘመሩ: ሐዋርያቱም እያለቀሱ ወደ ጌቴሴማኒ: በአጐበር ሥጋዋን ጋርደው ወሰዱ:: ይሕንን ሊቃውንት:- "ሐራ ሰማይ ብዙኃን እለ አልቦሙ ሐሳበ: እንዘ ይዜምሩ ቅድሜኪ ወመንገለ ድኅሬኪ ካዕበ: ማርያም ሞትኪ ይመስል ከብካበ" ሲሉ ይገልጡታል:: ¤በወቅቱ ግን አይሁድ በክፋት ሥጋዋን እናቃጥል ስላሉ #ቅዱስ_ገብርኤል (ጠባቂ መልአክ ነው) እነርሱን ቀጥቶ እርሷን ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ወስዶ በዕጸ ሕይወት ሥር አኑሯታል:: በዚያም #መላእክት እያመሰገኗት ለ205 ቀናት ቆይታለች:: ¤#ቅዱስ_ዮሐንስ መጥቶ ለሐዋርያቱ ክብረ ድንግልን ቢነግራቸው በጐ ቅንአት ቀንተው በነሐሴ 1 ሱባኤ ጀመሩ:: 2ኛው ሱባኤ ሲጠናቀቅም ጌታ የድንግል ማርያምን #ንጹሕ_ሥጋ ሰጣቸው:: እየዘመሩም #በጌሴማኒ ቀብረዋታል:: ¤በ3ኛው ቀን (ነሐሴ 16) እንደ ልጇ ባለ #ትንሳኤ ተነስታ ዐርጋለች:: ትንሳኤዋንና ዕርገቷንም ደጉ ሐዋርያ #ቅዱስ_ቶማስ አይቶ: መግነዟን ተቀብሏል:: ሐዋርያቱም መግነዟን ለበረከት ተካፍለው: እንደ ገና በዓመቱ ነሐሴ 1 ቀን ሱባኤ ገቡ:: ¤ለ2 ሳምንታት ቆይተው: በዚህች ቀንም ሁሉንም ወደ ሰማይ አወጣቸው:: በፍጡር አንደበት ተከናውኖ የማይነገር ተድላ: ደስታና ምሥጢርንም አዩ:: ጌታ ራሱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው:: የበዓሉን ቃል ኪዳን ሰምተው: ከድንግል ተባርከው ወደ #ደብረ_ዘይት ተመልሰዋል:: =>ጽንዕት በድንግልና: ሥርጉት በቅድስና #እመቤታችን: ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን: ለብዎውን: ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን::

📌 የየነሐሴ እና የጳጉሜን ወር የመርሐግብር መሪዎች ስም ዝርዝር። #ትምህርት_ክፍል https://t.me/tmhrt12
📌 የየነሐሴ እና የጳጉሜን ወር የመርሐግብር መሪዎች ስም ዝርዝር። #ትምህርት_ክፍል https://t.me/tmhrt12

በዓለ ደብረ ታቦር እና ቡሄ.docx9.03 KB

እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች! እንኳን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ወርሐዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። 📌 እንደ አምላካችን ፈቃድ ነገ እሑድ ነሐሴ 12 ለሁሉም ክፍላት የሕይወት ትምህርት በዲ/ን አብርሐም ስለሚኖር በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። • መርሐግብር መሪ :-ቴዎድሮስ አለምሰገድ ✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨ #ትምህርት_ክፍል

እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች! 📌 እንደ አምላካችን ፈቃድ ነገ እሑድ ሐምሌ 28 ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። • ካልዓይ ክፍሎች:- የቤ/ክ ታሪክ በዓለም በኢትዮዽያ መርሐግብር መሪ:- ብስራት ቴዎድሮስ • ሣልሳይ ክፍል እና ራብዓይ ክፍል: መንፈሳዊው ሰው ክፍል 3 (የመጨረሻ ክፍል) መርሐግብር መሪ:- ዲ/ን ዘሪሁንወ/ማርያም ✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨ #ትምህርት_ክፍል

📌16ኛ ዙር የርቀት ትምህርት ነገረ ክርስቶስ በዲ/ን ያደሳ ⏰ እሑድ ሐምሌ 28/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8-10 ሰዓት በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ ⛪️ #ትምህርት_ክፍል https://t.me/tmhrt12
📌16ኛ ዙር የርቀት ትምህርት ነገረ ክርስቶስ በዲ/ን ያደሳ ⏰ እሑድ ሐምሌ 28/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8-10 ሰዓት በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ ⛪️ #ትምህርት_ክፍል https://t.me/tmhrt12

እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች! 📌 እንደ አምላካችን ፈቃድ ነገ እሑድ ሐምሌ 21 ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። ✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨ #ትምህርት_ክፍል

†††✝ እንኳን ለቅዱሳኑ ገብርኤል ሊቀ መላእክት: ቂርቆስ ወኢየሉጣ: በጥላን ጠቢብ እና ሰማዕታተ እስና ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† ††† ✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን✝! ††† †††✝ ቅዱሳን ቂርቆስ ወኢየሉጣ: ወቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት †††✝ ††† ቅድስት ኢየሉጣ እናታችን በዘመነ ሰማዕታት ከነበሩና በዚህ ስም ከሚጠሩ ቅዱሳት አንዷ ናት:: በወቅቱ ቅዱስ ቂርቆስ የሚባል ደግ ልጅ ወልዳ ባሏ ባለመኖሩ በመበለትነት ትኖር ነበር:: የዚያ ዘመን ክርስቲያኖች ለክርስቶስ የነበራቸው ፍቅር ከመነገር በላይ ነው:: በዛው ልክ ደግሞ መከራው በጸጉራቸው ቁጥር ልክ ነበር:: ከሮም ግዛት በአንዱ ከቅዱስ ልጇ ጋር የምትኖረው ቅድስት ኢየሉጣ የስደቱ ዘመን ሲመጣ እርሷም እንደ ሌሎቹ ክርስቲያኖች ተሰደደች:: እስክንድሮስ የተባለው ከሃዲ ንጉሥ ግን ያለችበት ድረስ ተከትሎ እንድትያዝና እንድትቀርብ አደረገ:: ወዲያውም "ስምሽ ማን ይባላል?" ቢላት "ክርስቲያን እባላለሁ" አለችው:: ንጉሡ ተቆጣ:: "መዋቲ ስሜን ከፈለክ ኢየሉጣ ይባላል" አለችው:: ንጉሡ መልሶ "አሁን ለጣዖት ካልሠዋሽ ሲጀመር ስቃይ: ቀጥሎም ሞት ይጠብቅሻል" ቢላት ቅድስቲቱ መልሳ "በከተማ ውስጥ የሦስት ዓመት ሕፃን አለና እርሱን አምጣው:: ማንን ማምለክ እንዳለብን ይነግረናል" አለችው:: አስፈልጐ ቅዱስ ቂርቆስን አስመጣው:: "ስምህ ማን ይባላል?" አለ ንጉሡ:: "ከማይደፈርስ ከንጹሕ ምንጭ የተቀዳ ጥሩ ምንጭ ስሜ ክርስቲያን ይባላል:: መዋቲ ስሜን ከፈለግህ ግን ቂርቆስ ይባላል" አለው:: ንጉሡ ሊያታልለው "ደስ የተሰኘህ ሕፃን" ቢለው ቅዱሱ ሕፃን "ትክክል ተናገርክ: ለእኔ በሰማያት ደስታ ይጠብቀኛል:: አንተ ግን እውነተኛው አምላክ ይፈርድብሃል" አለው:: በሦስት ዓመት ሕፃን አንደበት ዘለፋ የገጠመው ከሃዲ ተቆጣ:: እናትና ልጅን በብዙ መክፈልተ ኩነኔ አሰቃያቸው:: ሰውነታቸውን ቸነከረ: አካላቸውን ቆራረጠ: ዓይናቸውን አወጣ:: ሌላም ሊናገሩት የሚጨንቅ ስቃይን አሰቃያቸው:: በዚህች ቀን ግን ትልቅ ድስት አሰርቶ ባሩድ: አረር: ስብና የመሳሰሉትን ጨምረውበት በእሳት አፈሉት:: የእሳቱ ወላፈን አካባቢውን በላው:: በድስቱ ውስጥ ያለው ነገር እየፈላ ሲገላበጥ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ይጮህ ነበር:: የስድስት ሰዓት የእግር መንገድ ድረስም ተሰምቷል:: ቅድስት ኢየሉጣ ይሔኔ ነበር ልቧ ድንግጥ ያለው:: ሕፃኑ ቂርቆስ የእናቱን ፍርሃት ሲመለከት ጸለየ:: "ፈጣሪዬ! ፍሬው ያለ ግንዱ አይቆምምና እኔን እንዳጸናሕ እናቴንም አጽናት" ሲል ለመነ:: "እግዚኦ ትፈቅድኑ ለፍሬሁ ተአልዶ: እንዘ በእሳት ታውኢ ጉንዶ" እንዲል:: በዚያች ሰዓት ቅድስት ኢየሉጣ ዓይኖቿ ተከፍተው ሰማያዊ ክብርን ተመለከቱና ልቧ ወደ ድፍረቱ ተመለሰ:: ልጇንም "አንተ አባቴ ነህ: አንተን የተሸከመች ማኅጸኔ የተባረከች ናት" አለችው:: ከዚያም ሁለቱንም ወደ ፈላው ድስት ውስጥ ቢጨምሯቸው ፍጡነ ረድኤት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደላቸው:: በበትረ መስቀሉ ባርኮ የፈላውን አቀዘቀዘው:: የነደደውን ውኃ አደረገው:: ቅዱሳኑ ቂርቆስና ኢየሉጣ ከብዙ መከራ በኋላ በሰማዕትነት አልፈዋል:: ††† "ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ: ወይስ ጭንቀት: ወይስ ስደት: ወይስ ራብ: ወይስ መራቆት: ወይስ ፍርሃት: ወይስ ሰይፍ ነውን? 'ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን:: እንደሚታረዱ በጐች ተቆጠርን::' ተብሎ እንደተጻፈው ነው:: በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን::" ††† (ሮሜ. ፰፥፴፭-፴፯) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††

እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች! 📌 እንደ አምላካችን መልካም ፈቃድ ነገ እሑድ ሐምሌ 14 ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። • ካልዓይ ክፍሎች:- የቤ/ክ ታሪክ በዓለም በኢትዮዽያ መርሐግብር መሪ:- ዲ/ን ኤልያስ • ሣልሳይ ክፍል:- የቤ/ክ ታሪክ በኢትዮዽያ መርሐግብር መሪ: ሀብታሙ • ራብዓይ ክፍል: መንፈሳዊው ሰው ክፍል መርሐግብር መሪ:- ዲ/ን አቤሜሌክ ✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨ #ትምህርት_ክፍል

እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች! 📌 እንደ አምላካችን መልካም ፈቃድ ነገ እሑድ ሐምሌ 07 ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። • ካልዓይ ክፍሎች:- የቤ/ክ ታሪክ በዓለም በኢትዮዽያ እና ፈተና መርሐግብር መሪ:- ዳዊት አረጋ • ሣልሳይ ክፍል:- የቤ/ክ ታሪክ በኢትዮዽያ መርሐግብር መሪ: ኃይለ ኢየሱስ • ራብዓይ ክፍል: መንፈሳዊው ሰው መርሐግብር መሪ:- ሀብታሙ አበበ ✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨ #ትምህርት_ክፍል

እንደምን አመሻችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች? ይህ መልዕክት ካልዓይ ክፍሎችን የሚመለከት ነው። 📍በባለፈው ሳምንት ሊሰጥ የነበረው የቤ/ክ ታሪክ ፈተና በነበረው ጉዞ ምክንያት ሊሰጥ ስላልቻለ የፊታችን እሑድ በ07/2016 ዓ.ም ስለሚሰጥ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። #ትምህርት_ክፍል

📌 የሐምሌ ወር የመርሐግብር መሪዎች ስም ዝርዝር። #ትምህርት_ክፍል https://t.me/tmhrt12
📌 የሐምሌ ወር የመርሐግብር መሪዎች ስም ዝርዝር። #ትምህርት_ክፍል https://t.me/tmhrt12

እንደምን ሰነበታችሁ ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች! እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓነታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። 📌 እንደ አምላካችን መልካም ፈቃድ ነገ እሑድ ሰኔ 30 ለሁሉም ክፍላት የኮርስ መርሐግብር ስለሚቀጥል በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ በየክፍላችሁ ትማሩ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። • ካልዓይ ክፍሎች:- የቤ/ክ ታሪክ በዓለም መድረክ ፈተና መርሐግብር መሪ:- ቅዱስ ሙሉጌታ • ሣልሳይ ክፍል:- የቤ/ክ ታሪክ በኢትዮዽያ መርሐግብር መሪ: ሱራፌል ፈቃዱ • ራብዓይ ክፍል:የሕይወት ትምህርት መርሐግብር መሪ:- መለሰ ፈይሳ 📍ሣልሳይ እና ካልዓይ ክፍሎች ነገ ከሰ/ት/ቤቱ ጽሕፈት ቤት ጋር በአገልግሎት ዙሪያ ውውይት ስለሚኖር ከኮርስ በኃላ ትቆዩ ዘንድ በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። ✨መልካም ዕለተ ሰንበት✨ #ትምህርት_ክፍል

❗️ማሳሰኒያ ለካልዓይ ክፍሎች። እንደ አምላካችን መልካም ፈቃድ እሑድ በ30 የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ የማጠቃለያ ፈተና ይኖራል፡፡ መቅረት እንዳማቻል በጥብቅ እያሳሰብን በዕለቱ ፈተና ላመለጣችሁ ደግመን አንፈትንም። #ትምህርት_ክፍል

•ጉባኤ ኄራኒ• ሴቶች በጓደኝነትሕይወት ከኤልሳቤጥ አያሌውጋር 🗓 እሑድ 30/10/2016 ዓ.ም ⏰12 ሰዓት 📍በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ 📌 ማሳሰቢያ: ማስታወሻ ያዙ። በማኅበራዊ ሚድያ ገጾቻ
ጉባኤ ኄራኒ• ሴቶች በጓደኝነትሕይወት ከኤልሳቤጥ አያሌውጋር 🗓 እሑድ 30/10/2016 ዓ.ም ⏰12 ሰዓት 📍በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ 📌 ማሳሰቢያ: ማስታወሻ ያዙ። በማኅበራዊ ሚድያ ገጾቻችን ቤተሰብ ይኹኑ: የቴሌግራም ገጻችን: https://t.me/tjss12 የfacebook ገጻችን: https://www.facebook.com/profile.php?id=100066679875652&mibextid=PzaGJu የቲክ ቶክ ገጻችን: https://www.tiktok.com/@tesfajerusalem?_t=8l9xP7zCJID&_r=1 የyoutube ገጻችን: https://youtube.com/@tesfajerusalem?si=RX3EqYGfWW8EDqtu የሰ/ት/ቤቱ ስልክ ቁጥር: +251921247777 ኢሜል አድራሻ: tesfajerusalem1221@gmail.com

📌15ኛ ዙር የርቀት ትምህርት ነገረ ቅዱሳን በዲ/ን አለምሰገድ ⏰ እሑድ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8-10 ሰዓት በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ ⛪️ #ትምህርት_ክፍል https://t.me/tmhrt12
📌15ኛ ዙር የርቀት ትምህርት ነገረ ቅዱሳን በዲ/ን አለምሰገድ ⏰ እሑድ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8-10 ሰዓት በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ ⛪️ #ትምህርት_ክፍል https://t.me/tmhrt12