313
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
እንኳን ለ2016 አንደኛ ሩብ አመት የወላጅ የመምህራን የተናጠል ዉይይት አደረሳችሁ አደረሰን። በመቀጠል ነገ አርብ ታህሳስ 05/2016 የተናጠል ዉይይት ስለሚካሄድ ለተማሪዎች ት/ት የለም። የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ከወላጆቻቸው ጋር ይመጣሉ።የዉይይት ጊዜ ከጧት2:00 - 5:40 & ከሰአት 7:30 - 9:00 መሆኑን እናሳዉቃለን። ስለሆነም ከነገ ዉጭ የማናስተናግድ መሆኑን ከወዲሁ እናሳዉቃለን። አብረዉን ስለሚሰሩ ምስጋናችን ከልብ ነዉ። ለልጀዎ ጊዜ ስለሰጡ እናመሰግናለን ሉቅማን ት/ቤት!
ዉድ የሉቅማን ት/ቤት ወላጆች ፣ ተማሪዎች እንዲሁም የት/ቤቱ ሠራተኞች ት/ቤቱ አሰራሩን አዘምኖ ዘመኑ ወደ ደረሰበት ቴክኖሎጂ ( Digital School Management System ) አሰራሩን ለመቀየር እንዲሁም በወላጆች ፣ ተማሪዎች ፣ መምህራን እና የት/ቤቱ አስተዳደር ክፍል ጋር ያለውን ግንኙነት ቀላል እና ዘመናዊ ለማድረግ ዝግጅቱን አጠናቋል ። አገልግሎቱን ለማስጀመር የተማሪዎች እንዲሁም የት/ቤቱ ሠራተኞች መረጃ መሰብሰብ ግድ ስለሆነ ሁላችሁም ከላይ በምስል ላይ በተጠቀሰው ድረ ገፅ በመግባት [ Sign Up ] የሚለውን ቁልፍ በመጫን በመቀጠል የምትገኙበትን ቅርንጫፍ ት/ቤት በመምረጥ ቀጥሎ የሚመጠጣውን የመረጃ መጠይቅ ሁሉንም በጥንቃቄ በመሙላት [ Submit ] የሚለውን ቁልፍ በመጫን መረጃውን ያስተላልፉ ። አገልግሎቱ ከሰኞ 03/03/2016 ጀምሮ አየር ጤና በዋና ቅርንጫፍ ት/ቤት በሚገኙ የ8ተኛ ክፍል ተማሪዎች የሙከራ መርሃ ግብር ስለሚጀመር በዋናው ግቢ የምትገኙ የ8ተኛ ክፍል ተማሪዎችና መምህራን በአስቸኩዋይ መረጃችሁን እንድታስተላልፉ እናሳስባለን ። በሌሎች ቅርንጫፍ ት/ቤት የምትገኙ ተማሪዎች እንዲሁም የት/ቤቱ ሠራተኞችም ከዚህ ሰዓት ጀምሮ መረጃችሁን ማስተላለፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን ። ከመረጃ አሞላል ጋር በተያያዘ የኢሜል አካውንት አከፋፈት የሚያሳይ አጋዥ ቪዲዮ የመረጃ መጠይቅ ገፅ ላይ የሚገኘውን [ Help ] የሚለውን ቁልፍ በመጫን መመልከት ይችላሉ። እናመሰግናለን!!
