ሕያው ቃል
በየ እለቱ የሚተላለፉ የሚጣፍጡ ከእግዚአብሔር ቃል የሚወጡ ክፍሎችን ይዘንላቹ መጥተናል። ይህ" ከክርስቶስ ወንጌል"channel ጋር link በማድረግ የሚገለገል አገልግሎት ነው። @christology_GC ..FOR more teaching🙏
Show more198
Subscribers
-324 hours
-57 days
-1030 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
🔶 እኛን ወደ እግዚአብሔር ያስጠጋን ጥሩነታችን፣ የዋህነታችን፣ መልካሙ ድርጊታችንም አይደለም።
🔶 ደካሞቹን ኃጢአተኞቹን እኛን ወደራሱ ያቀረበንና የሳበን የእርሱ የፍቅር ኃይል ነው።
👉 ከሞት ያዳነን፣
👉 ከሲዖል ያስመለጠን፣
👉 ከጨለማ ያወጣን፣
👉 እስራታችንን የፈታ የናዝሬቱ ኢየሱስ ብቻ ነው። አሜን፤ ሃሌ ሉያ!
🔶 ዘመን የተጨመረልን ከጊዜና ከዘመን ቁጥር ውጭ ለሆነው ጌታ ክብርን እንድናመጣ ነው። በምድራችን ላይ ያለው ነገር ሁሉ እግዚአብሔር የሚያየውና የሚቆጣጠረው አይመስልም።
🔶 ነገር ግን እንዳንዘንጋ! በዙፋኑ የተቀመጠው ጌታ ዛሬም አለ፤ እርሱ ልጆቹን ብቻ ሳይሆን፣ መንግሥታትንም ያያል፤ ይመለከታል፤ በፍርዱም ያጠራቸዋል።
🔶 በእርሱ የሚታመኑና ለእርሱ በመገዛት የሚኖሩ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ በረከትና ዕረፍት አላቸው።
🔶 የሰው ልጅ ከተባለውም ከኢየሱስ ጋር በአንድነት ይገዛሉ፥ ያሸንፋሉ፥ ድል ይነሣሉ፤ ከእርሱ የተነሣም ከዘላለም እስከ ዘላለም በሕይወት ይኖራሉ። በመሲሑና ለዘመናት በሸመገለው ጌታ ክብር ይሁንለት። አሜን!!!
"ዘመናት የማይለዋውጡት ርዕስ"
✔️ “መዳንም በሌላ በማንም የለም፤
እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።”(ሐዋርያት 4፥12)
👉 የማንጠቅም ያለ ምክንያት የተወለድን የለንም።
👉 ሁላችንም ለእግዚአብሔር እንጠቅመዋለን። ሰለምንጠቅመውም ከሞት አስመለጠን። ጌታ ይባረክ!!!