en
Feedback
Amex Den

Amex Den

Open in Telegram

Christian Views; Life Experiences & Stories; Funny stuff; Book Reviews; … and more

Show more
331
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-230 days
Posts Archive
Jemal Abdulaziz መ ን ግ ሥ ቱ ኃ ይ ለ ማ ር ያ ም (ኮ ሎ ኔ ል) ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ግንቦት 19 ቀን 1933 አዲስ አበባ ውስጥ አራዳ ጊዮርጊስ አካባቢ ከአባታቸው ከአቶ ኃይ
Jemal Abdulaziz መ ን ግ ሥ ቱ ኃ ይ ለ ማ ር ያ ም (ኮ ሎ ኔ ል) ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ግንቦት 19 ቀን 1933 አዲስ አበባ ውስጥ አራዳ ጊዮርጊስ አካባቢ ከአባታቸው ከአቶ ኃይለማርያም ወልዴ እና ከእናታቸው ወ/ሮ ብዙነሽ ወልደአማኑኤል ተወለዱ። የሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ትዝታዎች በተባለው መፅሃፍ ውስጥ እራሳቸው ኮሎኔል መንግሥቱ ተጠይቀው እንዳብራሩት "መንግሥቱ" የሚለው ስም የወጣላቸው የጣልያን የወረራ አገዛዝ አብቅቶ የኢትዮጵያ መንግሥት እንደገና ተቋቁሞ የአንድ ወር ጊዜ እንኳን ሳይቆዩ የመወለዳቸው ያንን ታሪካዊ ክስተት ለማስታወስ ሲባል ነው። ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም በሆለታ የወታደራዊ አካዳሚ የውትድርና ትምህርት ተከታትለዋል። ኮሎኔል መንግሥቱ በውትድርናው ዓለም በሚያገለግሉ ጊዜ የቁጡነት ባህሪ ያንጸባርቁ እንደነበር የሚናገሩ አሉ። ለበላይ አለቆች በቀላሉ የማይታዘዙ፣ በበላይ አለቆችም ላይ አስፈላጊ መስሎ ከታያቸው ከመሳደብም የማይመለሱ፣ ለሚሰነዘርባቸው ኃይለ ቃልም አስበልጠው አፀፋውን የሚመልሱ እንደሆኑ አድርገው ይገልፁኣቸዋል። ኮሎኔል መንግሥቱ ለ17 ዓመታት ኢትዮጵያን በርዕሰ ብሔርነት መርተዋል። የትዳር ጓደኛና የቤተሰብ ምሥረታ ህይወታቸውን ስንመለከት በአንድ የትዳር ጓደኛ ተወስነው እንደመኖራቸው ኮሎኔል መንግሥቱ የጭምትነት ባህሪ የሚታይባቸው ነበሩ ለማለት ይቻላል። ኮሎኔል መንግሥቱ ከወ/ሮ ውባንቺ ቢሻው ጋራ ትዳር መስርተው ትምህርት፣ ትዕግስት እና አንድነት የተባሉ ሶስት ልጆችን አፍርተዋል። ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም በስልጣን ዘመናቸው ከሰሯቸው መልካም ተግባራት ውስጥ ጥቂቱን ብቻ ይጥቀሱ ቢባሉ ምን ብለው ይመልሳሉ?

Jemal Abdulaziz0͏ እቴጌ መነን አስፋው የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ባለቤት የነበሩት እቴጌ መነን አስፋው የተወለዱት መጋቢት 25 ቀን 1883 ዓ.ም ነበር፡፡ ‹‹መነን›› የሚለው ቃል
Jemal Abdulaziz  እቴጌ መነን አስፋው የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ባለቤት የነበሩት እቴጌ መነን አስፋው የተወለዱት መጋቢት 25 ቀን 1883 ዓ.ም ነበር፡፡ ‹‹መነን›› የሚለው ቃል በአማርኛ ቋንቋ የሴት ልጅ ስም ሲሆን ታላቁ ምሁር ዓለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ‹‹ቀጭን ፈታይ፣ ባለሟያ፣ መልከ መልካም፣ ትክክል፣ ፍጽምት፣ ሕጸጽ የሌለባት›› ማለት እንደሆነ ጽፈዋል። እቴጌ ማለትም የንጉሠ ነገሥቱ ሚስት፣ ባለዘውድ ማለት ነው። ግርማዊት እቴጌ መነን መጋቢት 25 ቀን 1883 ዓ.ም በወሎ ጠቅላይ ግዛት፣ በአምባሰል አውራጃ ልዩ ስሙ ዕጓ በተባለ ቀበሌ ከዣንጥራር አስፋው እና ከወይዘሮ ስኂን ሚካኤል ተወለዱ፡፡ በልጅነት ዘመናቸው በወላጆቻቸው ቤት መምህር ተቀጥሮላቸው አማርኛ ማንበብና መፃፍ ጠንቅቀው አወቁ፡፡ በተጓዳኝነትም ልዩ ልዩ የቤት ባልትና ሙያዎችን ተምረው በማጠናቀቃቸው ‹‹የቤት ራስ›› ለመባል በቅተዋል፡፡ ወይዘሮ መነን አስፋው ባለቤታቸው ልዑል አልጋ ወራሽ ንጉሥ ተፈሪ መኮንን ጥቅምት 23 ቀን 1923 ዓ.ም ‹‹ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ስዩመ እግዚአብሔር ንጉሰ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ›› ተብለው ሲነግሱ እርሳቸውም የእቴጌነት ዘውድ ጫኑ፡፡ ከጋብቻቸውም ልዕልት ተናኘወርቅን፣ ልዑል አስፋ ወሰንን፣ ልዕልት ዘነበወርቅን፣ ልዕልት ፀሐይን፣ ልዑል መኮንንንና ልዑል ሳህለሥላሴን አፍርተዋል፡፡ እቴጌ መነን አሰፋው የካቲት 9 ቀን 1954 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተው፤ ሥርዓተ ቀብራቸውም በአዲስ አበባ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈፅሟል፡፡

Tab Amex Shared with Public አሜሪካኖቹ የበፊት መሪዎቻቸውን የሚያነሱት ከአድናቆትና ከታላቅ ክብር ጋር ነው። የመጀመሪያው ፕሬዝዳንታቸው ጆርጅ ዋሺንግቶንን Father of the Nat
Tab Amex Shared with Public አሜሪካኖቹ የበፊት መሪዎቻቸውን የሚያነሱት ከአድናቆትና ከታላቅ ክብር ጋር ነው። የመጀመሪያው ፕሬዝዳንታቸው ጆርጅ ዋሺንግቶንን Father of the Nation (የአገራችን አባት) ይሉታል፤ ሰው ሁሉ እግዚአብሔር ፊት እኩል ነው በማለት Declaration of Independence (የነጻነት አዋጅ እንበለው) የጻፈው ቶማስ ጄፈርሰን፥ እናም የባርያ ንግድን ያስቀረው አብርሃም ሊንከን አቤት ሲኮሩቧቸው! ///——////——-///// ዛሬ 6 መጻሕፍትን ተቀበልኩ። ያመጣችልኝን ቅን እና ገዝታ የላከችው ታናሼ በብዙ ተባረኩ። መጻሕፍቱ እጄ በመግባታቸው ደስ ቢለኝም፤ የጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድን ምስል ሳይ ግን በጣም አዘንኩ። /// የእኚህ ድንቅ ሰው ድንቅ ጭንቅላት፥ ለሚወዷት አገራቸው የሠሩት፥ ያደረጉት ብዙ መልካም ነገሮችና ስኬቶች ሁሉ ከንቱ መሆናቸው በጣም በጣም ያሳዝናል። የኢትዮጵያ ወርቃማ ዘመን መሠረትን ይጥሉ የነበሩ ምጡቅ አእምሮ የነበራቸው ምሁራንን አገሪቷ ቅርጥፍ አድርጋ በልታ! ከዚያም ነገራችን ሁሉ ቁልቁል!

ዝናብ (Wheaton, MD)

የአማካሪዎቹ ቁንጮ:_______ እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ አንዳንድ ሰዎች እግዚአብሔር የሰጣቸውን ድንቅ አእምሮ፥ ጥበብና እውቀት ለተንኮልና ለጥፋት ያውሉታል። ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በግልጽ የማስታውሳቸ
የአማካሪዎቹ ቁንጮ:_______ እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ አንዳንድ ሰዎች እግዚአብሔር የሰጣቸውን ድንቅ አእምሮ፥ ጥበብና እውቀት ለተንኮልና ለጥፋት ያውሉታል። ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በግልጽ የማስታውሳቸው: ከብሉይ ኪዳን በለዓምና #አኪጦፌል፤ ከአዲስ ኪዳን ደግሞ፣ አስቆሮቱ ይሁዳ ናቸው። በተለይ የአኪጦፌልና የይሁዳ ታሪካቸውና ባሕሪያቸው ተመሳሳይ ነው። / ለምሳሌ፦ #አኪጦፌል የዳዊት አማካሪ እንደነበረው ሁሉ፤ ይሁዳ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ነበር። #አኪጦፌል ዳዊትን እንደከዳው፥ ይሁዳም ኢየሱስን አሳልፎ በመስጠት ከዳው። #አኪጦፌል አቤሴሎም ምክሩን እንዳልተቀበለው ሲረዳ፥ ተሰቅሎ ራሱን በራሱ ገደለ። ይሁዳም የጌታው የኢየሱስ በግፍ እንደተሰቃየ ሲያይ፥ እርሱም ራሱን ሰቅሎ ሞተ። #አኪጦፌል የሚለው ስም ትርጉሙ፣ “የሞኝ ወንድም” (brother of the folly) ማለት ነው። #አኪጦፌል (ልክ እንደ በለዓም) የተመሰከረለት አዋቂና ጥበበኛ ነበረ። ቀድሞ የንጉሥ ዳዊት አማካሪም ይመስላል። ከዕብራውያኑ ጸሐፍት እንዳነበብኩት፣ #አኪጦፌል ዳዊት በቸገረው ነገሮች መፍትሔዎችን በማቅረብ የረዳው የቤተ መንግሥት ባለሟል ነበር ይላሉ። ነገር ግን፣ አኪጦፌል በዳዊት ላይ ድብቅ #ቂም፥ ወይም ከፍተኛ #ቅናት ነበረበት በማለትም ጽፈዋል። የአኪጦፌል ንቁና የሰላ አእምሮ ለበረከትና ለሰላም ሳይሆን ለውርደትና ለጥፋት ዳረገው! አብሴሎም ሌላኛውን ምክር ተቀብሎ አባቱን ቆይቶ ጦር እንደሚገጥመው ሲወሰን፣ #አኪጦፎል ዳዊት እንደሚያሸንፍ እርግጠኛ ሆነ። ዳዊት ኢየሩሳሌም በድል ሲገባም፣ አንገቱ በካራ እንደሚቆረጥ እርግጠኛ ነበር። ስለዚህ ራሱን ለራሱ ችሎት አቅርቦ፤ በራሱ ላይ የሞት ፍርድን ፈረደ። ፍርዱንም ራሱ በራሱ ነፍስ ላይ ፈጸመው።

የአማካሪዎቹ ቁንጮ:_______ እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ አንዳንድ ሰዎች እግዚአብሔር የሰጣቸውን ድንቅ አእምሮ፥ ጥበብና እውቀት ለተንኮልና ለጥፋት ያውሉታል። ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በግልጽ የማስታውሳቸ
የአማካሪዎቹ ቁንጮ:_______ እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ አንዳንድ ሰዎች እግዚአብሔር የሰጣቸውን ድንቅ አእምሮ፥ ጥበብና እውቀት ለተንኮልና ለጥፋት ያውሉታል። ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በግልጽ የማስታውሳቸው: ከብሉይ ኪዳን በለዓምና #አኪጦፌል፤ ከአዲስ ኪዳን ደግሞ፣ አስቆሮቱ ይሁዳ ናቸው። በተለይ የአኪጦፌልና የይሁዳ ታሪካቸውና ባሕሪያቸው ተመሳሳይ ነው። / ለምሳሌ፦ #አኪጦፌል የዳዊት አማካሪ እንደነበረው ሁሉ፤ ይሁዳ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ነበር። #አኪጦፌል ዳዊትን እንደከዳው፥ ይሁዳም ኢየሱስን አሳልፎ በመስጠት ከዳው። #አኪጦፌል አቤሴሎም ምክሩን እንዳልተቀበለው ሲረዳ፥ ተሰቅሎ ራሱን በራሱ ገደለ። ይሁዳም የጌታው የኢየሱስ በግፍ እንደተሰቃየ ሲያይ፥ እርሱም ራሱን ሰቅሎ ሞተ።#አኪጦፌል የሚለው ስም ትርጉሙ፣ “የሞኝ ወንድም” (brother of the folly) ማለት ነው። #አኪጦፌል (ልክ እንደ በለዓም) የተመሰከረለት አዋቂና ጥበበኛ ነበረ። ቀድሞ የንጉሥ ዳዊት አማካሪም ይመስላል። ከዕብራውያኑ ጸሐፍት እንዳነበብኩት፣ #አኪጦፌል ዳዊት በቸገረው ነገሮች መፍትሔዎችን በማቅረብ የረዳው የቤተ መንግሥት ባለሟል ነበር ይላሉ። ነገር ግን፣ አኪጦፌል በዳዊት ላይ ድብቅ #ቂም፥ ወይም ከፍተኛ #ቅናት ነበረበት በማለትም ጽፈዋል። / የአኪጦፌል ንቁና የሰላ አእምሮ ለበረከትና ለሰላም ሳይሆን ለውርደትና ለጥፋት ዳረገው! ዳዊት እንደሚሸነፍ ርግጠኛ ሆኖ ያቀረበው ምክር በአቤሴሎም ዘንድ ተቀባይነት ማጣቱ፣ ቅስሙን ሰበረው። አብሴሎም ሌላኛውን ምክር ተቀብሎ አባቱን ቆይቶ ጦር እንደሚገጥመው ሲወሰን፣ #አኪጦፎል ዳዊት እንደሚያሸንፍ እርግጠኛ ሆነ። ዳዊት ኢየሩሳሌም በድል ሲገባም፣ አንገቱ በካራ እንደሚቆረጥ፥ ወይም በገመድ ተንጠልጥሎ እንደሚሞትም እርግጠ

ከብሉይ ኪዳን ሰዎች -፲፱: #አኪጦፌል ማነው?
ከብሉይ ኪዳን ሰዎች -፲፱: #አኪጦፌል ማነው?

ፍቅር ዕዳ አይደለም። ——— ፍቅር ምንድነው? ፍቅር ፩ኛ ቆሮንቶስ ምእራፍ 13 ነው። (1) አንድ አስተማሪ ስለ የትራፊክ ሕግ ሲያስረዳ ሰዎችን አንድ ማስተማሪያ መንገድ ከኪሳቸው ገንዘብ በቅጣት መው
ፍቅር ዕዳ አይደለም። ——— ፍቅር ምንድነው? ፍቅር ፩ኛ ቆሮንቶስ ምእራፍ 13 ነው። (1) አንድ አስተማሪ ስለ የትራፊክ ሕግ ሲያስረዳ ሰዎችን አንድ ማስተማሪያ መንገድ ከኪሳቸው ገንዘብ በቅጣት መውሰድ ነው አለ። በምትኩ ምንም ሳይጠብቁ ገንዘብ የሚሰጧቹህ ሰዎች በጣም ይወዷችኋል። (2) ለሰው ብር አልሰጥም ብዬ አጉል ትሑት መሆን አልፈልግም። ነገር ግን፣ በዚች አጭር ሕይወቴ ብዙ ቸር ሰዎችን አውቃለሁ። /// (3) ለምሳሌ፦ “እምነት፥ ተስፋ፥ ፍቅር” መጽሐፍን ለፊርማ በተቀመጥኩበት ጊዜ፣ ቅዳሜና እሑዱን ብቻ ከ3ሺህ ብር በላይ ተሰጥቶኝ ነበር! ሁለት/ሦስት? ወንድሞች ለአንዱ መጽሐፍ 200 ዶላር ሰጥተውኛል። አሁን በጌታው ዘንድ ያለው ሶልና የኪያው ቸርነትማ ልዩ ነው። ሀያ ሀያ መጻሕፍትን አስፈርመው ወሰዱልኝ። ከጥቂት ወራት በኋላ የተረፉትን መጻሕፍት ከኪያ ደግሜ ወስጄ ሸጥኳቸው። ብዙዎች መቶ መቶ ዶላራቸውን መዥረጥ አድርገው አሽገውኛል። ከዚህ ስፖንሰር አድርገው ሙሉ ሻንጣ መጻሕፍትን ኢትዮጵያ ልኬያለሁ። (4) ለሚቀጥለው መጽሐፍ አላስቀመጥኩትም እንጂ፤ የማሳተሚያው ሙሉ ተከፍሎ ብዙ ትርፍ ብር ሰብስቤ ነበር። እግዚአብሔር ይስጥልኝ! የሰማይ መስኮቱን ከፍቶ በረከቱን ያፍስስላችሁ። ———//———//—— (5) “እምነት፥ ተስፋ፥ ፍቅር” #ቅጽ ፪ የታል? ለምትሉኝ፤ ለእኔም ጥያቄዬ ነው።

ይህኛው ትክክለኛው መልስ ተገኝቷል። ቅኔው የተዋቀረው በሰባ በሬ፥ ሥጋ ሆኖ፤ ሻኛውን ገልጦ፥ ጅራቱስ ብሎ ይጠይቅና፥ ሻኛው ነው እንጂ ጅራቱ አይደለም። ጅራቱ አይረባም ብሎ ይደመድማል። —— ግን፣ ዋናው መልእክት የመጨረሻው መስመር (አንጓ) ላይ ነው። እናም ኅብረ-ሀረጉ “ከጅራት የለውም” የሚለው ነው። — ከሀዲ ሰው ራት አይሰጠውም ያሉ አሉ። ተጠጉ እንጂ ይቀራል። መልሱ ከሀዲ ሰው መጨረሻው አያምርም። በሰላም አያረጅም፤ በሽምግልናው ይቸገራል ነው። ከክህደት ራሳችሁን ጠብቁ ነው። ~ Happy Friday!

ይህንን ቅኔ የሞከረም የለም ~ ይገርማል። ብዙ ጊዜ የቅኔ ምሥጢሩ በመጨረሻው አንጓ (ወይ መስመር) ላይ የተቀመጠው ኅብረ-ቃል፥ ወይም ሀረግ ውስጥ ነው። አልፎ አልፎም አረፍተ ነገር (አሳቡ) ሊሆን ይችላል። የላይኛው የግጥሙ (ቅኔው) መንፈስ ስለ ጾም ሆኖ በፊት ሰው ጾም የሚገድፈው ዓሣ በመብላት ነበር ይልና፤ መቋጫው ላይ “በጾም ሽሮ ነው የሚበላ” ብሎ ያስቀምጠዋል። ለዛሬ ሰው በጾም ዓሣ መብላት ቁቡ አይደለም፤ አያፍርም፣ ወዘተ —- እና… (ምን ያደርጋል?

ይህ ጥቁር በሬ ስባቱ፤ ከሻኛው ነው ወይስ ከጅራቱ፤ ቢሆንም ከሻኛው፤ ከጅራት የለው።
ይህ ጥቁር በሬ ስባቱ፤ ከሻኛው ነው ወይስ ከጅራቱ፤ ቢሆንም ከሻኛው፤ ከጅራት የለው።

Jemal Abdulaziz ቀይ ቀበሮ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኝ አጥቢ እንስሳ ነው። በምስሉ ላይ እንደምንመለከተው ቀበሮው አደን ላይ ነው። እያደነ ያለው ደግሞ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘውን Giant mol
Jemal Abdulaziz ቀይ ቀበሮ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኝ አጥቢ እንስሳ ነው። በምስሉ ላይ እንደምንመለከተው ቀበሮው አደን ላይ ነው። እያደነ ያለው ደግሞ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘውን Giant mole ratን ነው። (ሀበሻ ለሀበሻ እንዲሁ ነው፣ መጥኔ!) 😀😀

ወያኔን በብዕሩ የታገለው ወዳጄ ተስፍሽ! ——— ብትገዙለት በጣም ደስ ይለኛል። /* ባትገዙ ግን እን… ______ https://www.amazon.com/YeBashaye-Wugoch-Keremata-%E1%
ወያኔን በብዕሩ የታገለው ወዳጄ ተስፍሽ! ——— ብትገዙለት በጣም ደስ ይለኛል። /* ባትገዙ ግን እን… ______ https://www.amazon.com/YeBashaye-Wugoch-Keremata-%E1%8A%A8%E1%88%A8%E1%88%9B%E1%89%B3-Afrikaans/dp/B0HBVGBTVC

ወያኔን በብዕሩ የታገለው ወዳጄ ተስፍሽ! ——— ብትገዙለት በጣም ደስ ይለኛል። /* ባትገዙ ግን እን… ______ https://www.amazon.com/YeBashaye-Wugoch-Keremata-%E1%8A%A8%E1%88%A8%E1%88%9B%E1%89%B3-Afrikaans/dp/B0HBVGBTVC

ወያኔን ለበዕሩ የታገለው ወዳጄ ተስፍሽ! ——— ብትገዙለት በጣም ደስ ይለኛል 🙏 /ባትገዙለት ግን … እን _____ https://www.amazon.com/YeBashaye-Wugoch-Keremata-%E1%8A%A8%E1%88%A8%E1%88%9B%E1%89%B3-Afrikaans/dp/B0HBVGBTVC

የዛሬ 90 ዓመት! ረፋድ አካባቢ... ክብድ ያለ ቀን ነበር፡፡ አደባባይ ላይ የተሰበሰበው የአዲስ አበባ ህዝብ የሚሆነውን ነገር ለማየት በጭንቀት ባህር ውስጥ ሆኖ ይጠባበቃል... • ወዲያው አንድ ቁ
የዛሬ 90 ዓመት! ረፋድ አካባቢ... ክብድ ያለ ቀን ነበር፡፡ አደባባይ ላይ የተሰበሰበው የአዲስ አበባ ህዝብ የሚሆነውን ነገር ለማየት በጭንቀት ባህር ውስጥ ሆኖ ይጠባበቃል... • ወዲያው አንድ ቁመታቸው ረዘም፣ ፊታቸው ዘለግ ያለ መልካቸው ጠየም ያለና አዋቂነታቸው ከገፃቸው ላይ የሚነበብ ሰው... በጭቃ የተለወሰ ጥቁር የጵጵስና ካባቸውን እንደለበሱ በከበቧቸው ፈርጣማ ወታደሮች እየተገፉ ከህዝቡ ፊትለፊት ቆሙ... • ደቂቃዎች ነጎዱ... አንዳች አስፈሪ ድባብ ሁኔታውን ለማየት በተሰበሰበው ህዝብ መሀል ነግሷል... በወታደሮች ተከበው የመጡት የጳጳስ ልብስ የለበሱት ቆራጥ ሰውዬ በችሎት ፊት ለብዙ ሰዓታት ቆመው ስለዋሉና ደክሟቸውም ስለነበር ለመቀመጥ ፈልገው አጠገባቸው ቆሞ የነበረውን ወታደር በትህትና ጠየቁት። እንዲቀመጡ ፈቀደላቸው... • ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩ የሞት ፍርዳቸው ለህዝቡ ተነበበ... ሰውዬው በፍርድ ችሎት ላይ እንዳሉ ሕዝቡ ሁሉ ስለእርሳቸው እያዘነ ሳለ መስቀላቸውን አውጥተው እየፀለዩ ሕዝቡን ባረኩ። ወዲያውም የሞታቸው ሰዓት መድረሱን አውቀው ሰዓታቸውን ከኪሳቸው አውጥተው ተመለከቱ። ምንም አይነት ፍርሃት በፊት ገፃቸው ላይ አይነበብም ነበር። የሞታቸውን ፍርድ ያነብ የነበረው ኢጣልያዊ ዳኛ ግን ይንቀጠቀጥና ታላቅ ፍርሃትም በፊቱ ይታይ ነበር... • ብዙም ሳይቆይ በአቅራቢያቸው ከነበረው ግንብ አጠገብ ጀርባቸውን ወደ ህዝቡ አዙረው እንዲቀመጡ ተደረገ... ከዚያ በኋላ 8 የታጠቁ ወታደሮች በስተጀርባቸው ሃያ እርምጃ ርቀው ተንበርክከው በተጠንቀቅ ቆሙ። ወዲያው አዛዡ «ተኩስ» በማለት ትእዛዝ ሲሰጥ ስምንቱም የታጠቁትን ጥይት በኢትዮጵያዊዩ ጳጳስ ላይ አዘነቡ፡፡ ንፁህ ደም ከጳጳሱ ገላ ላይ እየተንዠቀዠቀ ወደ መሬት ፈሰሰ... • በዚያች ሌሊት በአዲስ አበባ ውስጥ በየቤቱ ልቅሶና ዋይታ ሆነ..

ባለጠግነት ኃጢአት አይደለም። ሠርተን ወይ ኢንቨስት አድርገን ባገኘነው ሀብት መደሰትም እንችላለን። ለዚህ ደጋፍ የሚሆኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች - መክብብ 5፥18-20፤ እና ፩ኛ ጢሞቲዎስ 6፥17-19 ይመልከቱ። ______ ነገርግን፣ ከሀብትና ከባለጠግነትና ጋር በተያያዘ ጥንቃቄ የምናደርጋቸው ነገሮች አሉ፦ - (1ኛ) በሀብት ንብረትና በባለጠግነት ከመመካት ራስን መጠበቅ፤ - (2ኛ) ትዕቢተኛ እንዳንሆን፤ - (3ኛ) በሀብታችን ሌሎችን እንዳንበድል፥ ግፍን እንዳንሠራ፤ - (4ኛ) ተስፋና መመኪያችን እግዚአብሔር እንጂ፣ በሀብታችን ተስፋ እንዳናደርግ፤ - (5ኛ) በሀብታችን ሌሎችን መርዳትና ማካፈል ይጠበቅብናል። _____ * ይህን የሰንበት ስብከት ይስሙ: https://youtu.be/_vnalZTBVho?is=tKWXTycd_EI0_JWJ

ሐምሌ 19 ቀን 1985 ዓ.ም #በዛሬዋ_ዕለት ከ 30 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን አንጋፋው ወጣቱ ድምጻዊ ኬኔዲ መንገሻ በተወለደ በ 30 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየበት ዕለት ነበር። ድምጻዊ
+2
ሐምሌ 19 ቀን 1985 ዓ.ም #በዛሬዋ_ዕለት ከ 30 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን አንጋፋው ወጣቱ ድምጻዊ ኬኔዲ መንገሻ በተወለደ በ 30 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየበት ዕለት ነበር። ድምጻዊ ኬኔዲ መንገሻ /እኔ ደግሞ የኬኔዲ መሞቱን ዜና በራዲዮ የሰማሁት ነቀምት ከተማ፣ ወለጋ ውጋጋን ሆቴል ነበር/ (ህዳር 14 ቀን 1955 -- ሐምሌ 19 ቀን 1985 ዓ.ም) መጀምሪያ ከሰራዉ አልበሙ አንድ ነኝ (በመላነዉ) ጀምሮ ፣ እንደዉ የሆዴን፣ ምተኬ ስሜ ነዉ፣ ልሁን ደህና (እንባ ስንቅ አይሆነኝ) የተባሉ አራት አልበሞች የሰራ ሲሆን ልሁን ደህና የሚለዉን ሮሃ ባንድ አጅበዉት ሲሰራ ይህንኑ አልበም ዕንባ ስንቅ አይሆነኝ በሚል ድጋሚ የዜማና ግጥም ደራሲዉ አበበ መለሰ በኪቦርድ እያጀበዉ ሰርቶት ድሬድዋ የነበረዉ ነጋሪት ሙዚቃ ቤት አሳትሞለት ነበር። ከድምፃዊች የሺእመቤት ዱባለ ጋር አንድ የጋራ አልበም ፣ ከድምፃዊት ብርቱካን ዱባለ ጋር አንድ የጋራ አልበም ፣ አሰፉ ደባልቄ ፣ ኬኔዲ መነገሻ ፣ ራሔል ዮሐንስና ተሾመ አሰግድ ሆነዉ በጋራ ያወጡት አልበምን ጨምሮ በግል 4 በጋራ ደግሞ 3 በአጠቃላይ ሰባት አልበሞች ሰርቷል። የታዋቂዉ ድምፃዊ ፍሬዉ ኃይሉን እሽሩሩ የሚለዉን ሙዚቃም መልሶ ተጫዉቶ ነበር። በሙዚቃ ሕይወቱ በቆየባቸዉ 8 ዓመታት ማለትም በኢትዮጵያ አቆጣጠር 1977 -- 1985 ዓ.ም ድረስ በርካታ ሥራዎችን ሰርቶልን አልፏል። የኬኔዲ አያት የአፄ የኃይለ ሥላሴ የግቢ ባለሙዋል ነበሩ። የአፄ ኃይለ ሥላሴ ወዳጅ የነበሩት ጆን ኤፍ ኬኔዲ ሲሞቱ ኃይለሥላሴ በጣም ስለአዘኑ ቻርተር አዉሮፕላን ተዘጋጅቶላቸዉ ለቀብር ወደ ዩናይትድ ስቴት ሲሄዱ በዚያን ዕለት ደግሞ ድምፃዊ ኬኔዲ መንገሻ ተወለደ። የኬኔዲ አባት አጥናፉ የሚባል ሲሆን የኬኔዲ አያት መንገሻ ለጌታዬ ወዳጅ ማስታወሻ ይሁን ሲሉ “ኬኔዲ” የሚል ስም

ምሳሌ 27:1 “ቀን የሚያመጣውን ምን እንደ ሆነ አታውቅምና፡ ነገ በሚሆነው አትመካ።”
ምሳሌ 27:1 “ቀን የሚያመጣውን ምን እንደ ሆነ አታውቅምና፡ ነገ በሚሆነው አትመካ።”

Joni and Friends Why does Joni Eareckson Tada celebrate the anniversary of her 1967 diving accident? It might seem strange to
Joni and Friends Why does Joni Eareckson Tada celebrate the anniversary of her 1967 diving accident? It might seem strange to celebrate an event that led to a lifetime of paralysis, but 59 years later, as Joni looks back, she is astounded at the grace of God that has been with her through the hardest of seasons. “I will remember the deeds of the Lord; yes, I will remember your miracles of long ago. I will consider all your works and meditate on all your mighty deeds.” Psalm 77:11–12 We benefit greatly by remembering the deeds of the Lord and all the grace that He’s given us in years past, even through the worst of times. Whatever suffering you’re facing, you can join Joni in celebrating God’s unwavering faithfulness in the midst of grueling trials. Recall the countless ways the Lord Jesus has provided you grace in times of need, strength in times of weariness, and comfort in moments of deepest suffering… then share that grace with someone else!