Amex Den
Open in Telegram
Christian Views; Life Experiences & Stories; Funny stuff; Book Reviews; … and more
Show more331
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-230 days
Posts Archive
331
Jemal Abdulaziz
o͏d͏t͏e͏o͏S͏s͏r͏n͏p͏c͏l͏a͏9͏9͏g͏m͏c͏0͏1͏3͏4͏t͏1͏a͏6͏3͏c͏c͏5͏h͏i͏0͏4͏8͏c͏t͏4͏3͏i͏5͏5͏i͏2͏4͏2͏6͏m͏0͏i͏0͏5͏c͏0͏1͏9͏6͏9͏i͏c͏
ፕሮፌሰር አቻምየለህ ደበላ
ዶ/ር አቻምየለህ የተወለዱት በ1949 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) አዲስ አበባ መርካቶ አካባቢ ነው።
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤት እና በናይጄሪያ ከሚገኘው አህማዱ ቤሎ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል። በበለፀገው ትምህርታቸው ከሞርጋን ስቴት ዩኒቨርሲቲ በሙዚየም ጥናትና የኪነ-ጥበብ ታሪክ (MA) እንዲሁም ከሜሪላንድ ኢንስትቲዩት ኮሌጅ ኦፍ አርት በሥዕል ሙያ የሁለተኛ ዲግሪያቸውን (MFA) አግኝተዋል። በተጨማሪም በኦሃዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ በዲጂታል አርትስና ኮምፒውተር ግራፊክስ የዶክትሬት ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።
በአዲስ አበባ ሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤት በነበሩበት ወቅት በታዋቂዎቹ አርቲስቶች አለፈለገ ሰላም፣ ገብረክርስቶስ ደስታ እና እስክንድር በጎሲያን ስር ተምረዋል።
ፕሮፌሰር አቻ በኮምፒውተርና ዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ሥነ-ጥበብን በመፍጠር ረገድ ፈር ቀዳጅ ከሆኑት የአፍሪካ አርቲስቶች አንዱ ናቸው።
በሥራዎቻቸው ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ጥበብን፣ የባህል ምልክቶችን፣ የቀለም አጠቃቀምን እና አፍሪካዊ-አሜሪካዊ የታሪክ ትረካዎችን ከዘመናዊ ዲጂታል ቴክኒኮች ጋር አዋህደው ያቀርባሉ።
ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት ባዘጋጇቸው ንድፎች (Designs) የ11ኛው እና 12ኛው ክፍለ ዘመን የቤተክርስቲያን ሕንፃዎችን በማስተዋወቅ በዩኔስኮ (UNESCO) እና ዩኒሴፍ (UNICEF) እውቅና አግኝተዋል።
ፕሮፌሰር አቻምየለህ በሰሜን ካሮላይና ሴንትራል ዩኒቨርሲቲ (NCCU) ከ30 ዓመታት በላይ በፕሮፌሰርነት ያገለገሉ ሲሆን፣ የዩኒቨርሲቲውን
331
#ፍቅር!
ከዓመታት በፊት አንድ ፓስተር፣ ኢየሱስ መስቀል ላይ ሆኖ “አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ?” ባለበት ዙሪያ ሲያስተምር፤ አብ ዝም እንዳለ ተናገረ። አያይዞም፣ (am paraphrasing) ልጁ መስቀል ላይ መሞቱ የግድ መሆኑን ካስታወቀ በኋላ፤ አብ፣ “አለበለዚያ እኔና አንተ አልኖርናትም! ምርጫ የለም!” በማለት ጨመረበት።
“ወጣት” ክርስቲያን ብሆንም፣ ይህ አባባል ይኸው እስከዛሬ እንደቆረቆረቆረኝ አለ። እግዚአብሔር ልጁን በመስቀል ላይ እንዲሞት አሳልፎ የሰጠው ለእኛ ብሎ እንጂ፣ ለራሱ ወይም ለልጁ “መኖር” ብሎ አይደለም። በፍጹም!
የሥነ መለኮት ሊቃውንት፣ እግዚአብሔርን “Self-Existent” እና “Self-Sufficient” ነው በሚል ይገልጡታል። እንዲህ የሆነው እርሱና እርሱ ብቻ ነው። ይህ ቅዱሳት መጻሕፍት በግልጥ የሚያስተምሩት ነገር ነው።
እግዚአብሔር ልጁን ለሞት አሳልፎ የሰጠው፣ መድኃኒትና ድነት እንዲሆነን ብሎ ነው። የእኛ መኖር ወይም አለመኖር ለእግዚአብሔር የሚጨምረው የሚቀንሰውም ነገር የለም። የፈጠረን እኛ ፈልገን ሳይሆን በራሱ ፈቃድና ጥበብ ነው። በመልኩና በአምሳሉ ልዩ አድርጎ ለፈጠረን ከጸጋውና ከሕይወቱ ሊያካፍለን ወደደ። ነገር ግን፣ በእሱና እኛ በመኻል ኃጢአት የሚባል ነገር ገባና ለያየን። እርሱ ቅዱስ ስለሆነ፥ እኛ ወደ እርሱ እንድንቀርብ ከኃጢአታችን መንጻት አለብን። ራሳችንን ማንጻት ስለማንችል፤ እግዚአብሔር ራሱ የድነት መፍትሔን አዘጋጀ። በልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት በኩል በነጻ ሰጠን።
ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል የሞተው የአባቱን ፈቃድ ለመፈጸም ነው። ነፍሱን አሳልፎ የሰጠውም ወዶና በፈቃዱ ነው። እግዚአብሔር አባት ልጁን ወደ ዓለም የላከው ለእኛ ካለው ትልቅ ፍቅር የተነሣ እንጂ፤ እርሱ አንዳች ጎሎበት አይደለም።
331
ፍቅር ብቻ ነው!
ከብዙ ዓመታት በፊት አንድ ፓስተር፣ ጉባኤ ላይ ኢየሱስ መስቀል ላይ ሆኖ “አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ?” ባለበት ዙሪያ ሲያስተምር፤ አብ ዝም እንዳለ ተናገረ። አያይዞም፣ (am paraphrasing) ልጁ መስቀል ላይ መሞቱ የግድ መሆኑን ካስታወቀ በኋላ፤ “አለበለዚያ እኔና አንተ አልኖርናትም! ምርጫ የለም!” በማለት ጨመረበት።
በጣም “ወጣት” ክርስቲያን ብሆንም፣ ይህ አባባል ይኸው እስከዛሬ እንደቆረቆረቆረኝ አለ። እግዚአብሔር ልጁን በመስቀል ላይ እንዲሞት አሳልፎ የሰጠው ለእኛ ብሎ እንጂ፣ ለራሱ ወይም ለልጁ፥ ወይም ለልጁና ለእርሱ “መኖር” ብሎ አይደለም። በፍጹም!
የሥነ መለኮት ሊቃውንት፣ እግዚአብሔርን “Self-Existent” እና “Self-Sufficient” ነው በሚል ይገልጡታል። እንዲህ የሆነው እርሱና እርሱ ብቻ ነው። ይህንን ቅዱሳት መጻሕፍት በግልጥ የሚያስተምሩት ነገር ነው።
እግዚአብሔር ልጁን ለመስቀል ሞት አሳልፎ የሰጠው፣ መድኃኒትና ድነት እንዲሆነን ብሎ ነው። የእኛ መኖር ወይም አለመኖር ለእግዚአብሔር የሚጨምረውም የሚቀንሰው አንዳች ነገር የለም። የፈጠረን እኛ ፈልገን ሳይሆን በራሱ ፈቃድና ጥበብ ነው። በመልኩና በአምሳሉ ልዩ አድርጎ ለፈጠረን፣ ከጸጋውና ከሕይወቱ ሊያካፍለን ወደደ። ነገር ግን፣ በእሱና እኛ በመኻል ኃጢአት የሚባል ነገር ገባና ለያየን። እርሱ ቅዱስ ስለሆነ፥ እኛ ወደ እርሱ እንድንቀርብ ከኃጢአታችን መንጻት አለብን። ራሳችንን ማንጻት ስለማንችል፤ እግዚአብሔር ራሱ የድነት መፍትሔን አዘጋጀ። ይህንንም በልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት በኩል በነጻ ሰጠን።
ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል የሞተው የአባቱን ፈቃድ ለመፈጸም ነው። ነፍሱን አሳልፎ የሰጠውም ወዶና በፈቃዱ ነው። እግዚአብሔር አባት ልጁን ወደ ዓለም የላከው ለእኛ ካለው ትልቅ
331
#መዝሙር 62
ተስፋ በእግዚአብሔር ላይ ብቻ
________
መዝሙር 62:1 ነፍሴ ለእግዚአብሔር የምትገዛ አይደለችምን? መድኃኒቴ ከእርሱ ዘንድ ናትና።
2 እርሱ አምላኬ መድኃኒቴም ነውና፤ እርሱ መጠጊያዬ ነው፥ እጅግም አልታወክም።
3 እስከ መቼ በሰው ላይ ትቆማላችሁ? እናንተ ሁላችሁ እንዳዘነበለ ግድግዳ፡ እንደ ፈረሰም ቅጥር ትገድላላችሁ።
4 ነገር ግን ክብሬን ይሽሩ ዘንድ መከሩ፥ ሐሰትንም ይወድዳሉ፤ በአፋቸው ይባርካሉ፥ በልባቸውም ይረግማሉ።
5 ነገር ግን፥ ነፍሴ ሆይ፥ አንቺ ለእግዚአብሔር ተገዢ፥ ተስፋዬ ከእርሱ ዘንድ ናትና።
6 እርሱ አምላኬ መድኃኒቴም ነውና፤ እርሱ መጠጊያዬ ነው፤ አልታወክም።
7 መድኃኒቴና ክብሬ በእግዚአብሔር ነው፤ የረድኤቴ አምላክ ተስፋዬም እግዚአብሔር ነው።
8 የሕዝብ ማኅበር ሁላችሁ፥ በእርሱ ታመኑ፥ ልባችሁንም በፊቱ አፍስሱ፤ እግዚአብሔር ረዳታችን ነው።
9 ነገር ግን የሰው ልጆች ከንቱ ናቸው፥ የሰው ልጆችም ሐሰተኞች ናቸው፤ በሚዛንም ይበድላሉ፥ እነርሱስ በፍጹም ከንቱ ናቸው።
10 ዓመፃን ተስፋ አታድርጉ፥ ቅሚያንም አትተማመኑት፤ ባለጠግነት ቢበዛ ልባችሁ አይኵራ።
11 እግዚአብሔር አንድ ጊዜ ተናገረ፥ እኔም ይህን ብቻ ሰማሁ፤ ኃይል የእግዚአብሔር ነው፥
12 አቤቱ፥ ምሕረትም ያንተ ነው፤ አንተ ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው ፍዳውን ትሰጣለህና።
331
Jemal Abdulaziz
የማይክል አንጄሎ ሥዕል በባዕታ ለማርያም
በአዲስ አበባ በሚገኘው ባዕታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን (በቀዳማዊ ምኒልክ ቤተ መንግሥት ግቢ ውስጥ በሚገኘው የታሪካዊው እምነትና የመቃብር ስፍራ) ውስጥ የሚገኘው የMichelangelo (ማይክል አንጄሎ) “Madonna and Child” (እመቤታችን ማርያም ከሕፃኑ ኢየሱስ ጋር) ሥዕል/ቅጂ ልዩ የታሪክ፣ የጥበብ እና የዲፕሎማሲ ትስስር መግለጫ ነው።
በአጼ ምኒልክ II ዘመነ መንግሥት ኢትዮጵያ ከአውሮፓ አገራት (በተለይም ከጣሊያን፣ ፈረንሳይ እና ሩሲያ) ጋር ጠንካራ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ነበራት። በዚህ ዘመን ከውጭ ሀገራት መሪዎች እና የሃይማኖት አባቶች ለንጉሠ ነገሥቱ በርካታ ውድ የጥበብ ሥራዎች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ሥዕሎች እና የቤተ ክርስቲያን ንዋያተ ቅድሳት በገጸ-በረከትነት (ስጦታ) ይላኩ ነበር። ይህ የ“Madonna and Child” ሥዕልም በዚህ መልኩ ወደ ቤተ መንግሥቱ ቤተ ክርስቲያን ከገቡት አውሮፓውያን ድንቅ የጥበብ ሥራዎች አንዱ ነው።
331
“ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።”
________
(ኢሳ• 53፥7)
————————
“ተጪነቆ ተሥቃዮማ አፈዋን አልክፈተማ፤ ለዎታረድ ይነዶሆም ጠቦቲ፥ ቢሺልትሙማ ይፍት እም ይብልኮም ኸጣይ፥ አዚሆም አፈዋን አልክፈተ።”
331
From #Danny’s pen:
🌟የምሽቱ መልዕክት✨💫
"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል፤ ከመከራም ሥጋት ያርፋል።"— ምሳሌ 1፥33
በሕይወት ውስጥ አውሎ ነፋሶች አይጠፉም። የሰዎች ቃል፣ የጦርነት ወሬ፣ ለጆሮ የሚከብዱ ዜናዎች፣ የነገው ጭንቀት፣ ያልተመለሱ ጥያቄዎች እና ያልተፈጸሙ ምኞቶች ልባችንን ሊያውኩ ይችላሉ።
ነገር ግን ዛሬ ምሽት የእግዚአብሔር ቃል አንድ ቀላል፣ ግን እጅግ ኃይለኛ ማረጋገጫ ይሰጠናል፤ እግዚአብሔርን የሚሰማ ሰው በእርጋታ ይኖራል።
እውነተኛ ሰላም ችግሮች በመጥፋታቸው አይመጣም፤ ከእግዚአብሔር ጋር በመሆናችን ይመጣል። የሰላም ንጉሥ የሆነውን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ስንለብስ ልባችን እረፍትን ያገኛል። እርሱን ስናምንና ስንታመንበት፣ የልባችን ሸክም ወደ እርሱ ይሸጋገራል፤ ፍርሃት በተስፋ ይተካል፣ ጭንቀትም በሰላም ይለወጣል።
ስለዚህ ዛሬ ምሽት ያልተፈቱ ጉዳዮቻችሁን በጸሎት ለጌታ አደራ ስጡ። እርሱ ዛሬን እንደረዳን ነገንም ይመራናል፤ ዛሬ የጠበቀን አምላክ ነገም ታማኝ ሆኖ ይጠብቀናል።
🌟 የዛሬ ቁልፍ መልዕክት (Core Message)
"እግዚአብሔርን የሚሰማ ሰው በፍርሃት አይኖርም፤ በእምነት ይኖራል፣ በሰላምም ያርፋል።"
መልካም ምሽት!💫
የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁን ይጠብቅ፤ ጸጋው ያጽናችሁ፤ ነገያችሁንም በተስፋ ይሙላው።
ሰላሜን እተውላችኋለሁ፤ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ሰላም ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም ይለናል ሕያው ቃል።
"ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።"— ዮሐንስ 14፥27
🌙 መልካም አዳር! የጌታ ሰላም ከእናንተ ጋር ይሁን።
እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካችሁ!🙏🏽
