en
Feedback
Amex Den

Amex Den

Open in Telegram

Christian Views; Life Experiences & Stories; Funny stuff; Book Reviews; … and more

Show more
331
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-230 days
Posts Archive
ዮናስ 4:11 እኔስ ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ ከመቶ ሀያ ሺህ የሚበልጡ ሰዎችና ብዙ እንስሶች ላሉባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ አላዝንምን?” አለው። ——//—— ዶ/ር ቶኒ ኢቫንስ ትላንት የዮናስ መጽሐፍን ተመርኩዞ ሲያስተምር: https://tonyevans.org/podcast_sermons/your-obedience-and-your-calling/ “120ሺህ” የሚለው “ሕጻናት” ናቸው በማለት ተናገረ። ቤት ስገባ እንዲያ የሚተረጉሙ ኮሜንታሪዎችን አየሁ። / አልስማማም። ምክንያቱም፦ - (፩ኛ) ቃሉ መቶ ሀያ ሺህ “ሰዎች” ስለሚል! - (፪ኛ) እኛ “ሰዎች” እግዚአብሔር ፊት “ግራና ቀኛችንን” የማናውቅ ሕጻናት ነን። - (፫ኛ) አባባሉ በምምሳሌያዊ (metaphorical ) እንጂ፤ በቀጥታ (literally) መወሰድ የለበትም። ~ መልካም ቀን!

አቤቱ መልሰን፥ እኛም እንመለሳለን።

ማቴዎስ 6:28 “ስለ ልብስስ ስለ ምን ትጨነቃላችሁ? የሜዳ አበቦች እንዴት እንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ፤ ማቴዎስ 6:29 አይደክሙም አይፈትሉምም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ሰሎሞንስ እንኳ በክ
ማቴዎስ 6:28 “ስለ ልብስስ ስለ ምን ትጨነቃላችሁ? የሜዳ አበቦች እንዴት እንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ፤ ማቴዎስ 6:29 አይደክሙም አይፈትሉምም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከነዚህ እንደ አንዱ አልለበሰም። ማቴዎስ 6:30 “እግዚአብሔር ግን ዛሬ ያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን የሜዳን ሣር እንዲህ የሚያለብሰው ከሆነ፥ እናንተ እምነት የጎደላችሁ፥ እናንተንማ ይልቁን እንዴት?

Repost from Amex Den
ይገባዋል! ~ He Is Worthy.

ይገባዋል! ~ He Is Worthy.

የወሬ አደገኛነት

‎Sent from ‎WhatsApp wa.me/+12024154856?source=exsh

ምእራፍ 9- የእግዚአብሔር ልጆች (“የእግዚአብሔር ልጅ”: በጳውሎስ ፈቃዱ)

ዶሮ ሻጩ “አውራ ዶሮ በወረደ ዋጋ!” እያለ ገበያ ውስጥ ይጮሃል። አንዷ ሴት ቀረብ አለችና “ለምንድነው ነው እንዲህ በወረደ ዋጋ የምትሸጠው?” ስትል ጠየቀችው። “ያሉኝን ሴት ዶሮዎቹን ሁሉ እያባረረ
ዶሮ ሻጩ “አውራ ዶሮ በወረደ ዋጋ!” እያለ ገበያ ውስጥ ይጮሃል። አንዷ ሴት ቀረብ አለችና “ለምንድነው ነው እንዲህ በወረደ ዋጋ የምትሸጠው?” ስትል ጠየቀችው። “ያሉኝን ሴት ዶሮዎቹን ሁሉ እያባረረ በመድፈር ገደለብኝ” “ታዲያ ምን ችግር አለው? ይሄ’ኮ የጉልበተኛ አውራ ዶሮ ፀባይ ነው” “ልክ ነዎት እሜቴ! ችግሩ እርስዎ እንደሚሉት ብቻ አይደለም። ሴት ዶሮዎቼን ከጨረሰ በኋላ ሰሞኑን ሚስቴን እና እናቴን የሚያያቸው አስተያየት ደስ አላለኝም” ባሻዬ!… ——— (ገጽ 36) /// “የባሻዬ ውጎች” አማዞን ላይ አለላችሁ።

“All Quite in the Western Front” ——— እና፣ “Saving Private Ryan” /// የጦርነትን እጅግ አስጠሊነትና አስከፊነት ጥሩ አድርገው የሚያሳዩ (እኤአ 2000 ዓም በፊትና
+1
“All Quite in the Western Front” ——— እና፣ “Saving Private Ryan” /// የጦርነትን እጅግ አስጠሊነትና አስከፊነት ጥሩ አድርገው የሚያሳዩ (እኤአ 2000 ዓም በፊትና በኋላ የተሠሩ) ፊልሞች ናቸው። “All Quite…” ከጀርመን በኩል ሆኖ ስለ ፩ኛው የዓለም ጦርነት የሚተርክ ሲሆን፤ “Saving Private Ryan” ከአሜሪካን ሳይድ በ፪ኛው የዓለም ጦርነት ላይ የተመረኮ ነው። / “All Quite…” የ17 ዓመት ጀርመናዊ ወጣት በፈቃዱ ጦርነቱን ከሦስት የሀይ ስኩል ጓደኞቹ ጋር ተቀላቅሎ፥ ፈረንሳይ ተመድቦ የዕልቂት አይነት ባይነት ያጋጥመዋል። ታዋቂ የሆሊውድ አክተሮች የሚሳተፉበት የአሜሪካኑ ፊልም ደግሞ፣ ሦስት ወንድሞቹን በሞት ያጣውን Ryan ፈልጎ ለማግኘትና ወደ እናቱ ለመመለስ ለተልዕኮ የተላከ ቡድንን ትንቅንቅና ሞት ይተርካል። /// ሁለቱም በመጽሐፍ ላይ የተመረኮዙ ይመስለኛል። “All Quite…” ቀድሞ በመጽሐፍ የታተመ ስለመሆኑ እርግጠኛ ነኝ። የተጻፈው በ፩ኛው የዓለም ጦርነት ተሳታፊ በነበረች ሴት ነው። ናዚ ጀርመኒ ለ፪ኛ ጊዜ ሊበጠብጡ ሲነሣሡ፣ መጽሐፉን በሙሉ ሰብስበው አቃጥለውት ነበረ። /// መልካም አዳር!

“አንደበትም እሳት ነው” ~ (ያዕቆብ 3፥6) ———///——— - ፩ - በፈረንጅኛው “sticks and stones may hurt me, but words never hurt me” የሚባል አባባል አለ። “
“አንደበትም እሳት ነው” ~ (ያዕቆብ 3፥6) ———///——— - ፩ - በፈረንጅኛው “sticks and stones may hurt me, but words never hurt me” የሚባል አባባል አለ። “ዱላ እንጅ ቃላት አይጎዱኝም” ማለት ነው። አባባሉ ውሸት ነው። ቃላት አብዛኞቻችንን በጣም ይጎዱናል። ሊያሳምሙን፥ ሊያሳብዱን ይችላሉ። / - ፪ - ፎቶው የዶ/ር ጄሰን አርዴይ ነው። ወላጆቹ ከጋና ሆነው፣ ጄሰን የተወለደው የዛሬ 41 ዓመት እንግሊዝ ነው። ጄሰን ትላንት ቤቱ ውስጥ ሞቶ ተገኝቷል። የታወቀው የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ የሶሺዮሎጂ ፕሮፌሰር የነበረው ጄሰን፤ የዶክትሬት ድግሪ መመረቂያ ወረቀቱ ከሌሎች የተኮረጀ ነው የሚል ወሬ ተነዝቶበት ነበር። በተጨማሪም ማንበብና መጻፍ የጀመርኩት ቆይቼ ነው በማለት የተናገረውም ውሸት ነው የሚሉ ክሶችም ነበሩበት። / - ፫- ዓለም ስታደንቅና ወደ ላይ ስታወጣ ዐይን የላትም። ስታዋርድና ወደታች ስታወርድም ዐይን የላትም። ጌታ ከዚህ ይጠብቀን። /// ጄሰን የሁለት ልጆች አባት ነበር። ለውድ ሚስቱና ለልጆቹ እንዲሁም ለመላው ለቤተሰቡ ሁሉ መጽናናት ይሁን።

Jemal Abdulaziz አቶ ልዑልሰገድ ኩምሳ አቶ ልዑልሰገድ ኩምሳ በኢትዮጵያ በጋዜጠኝነት እና በተለይም በእንግሊዝኛ ዜና አንባቢነት ታዋቂ እና ትልቅ አሻራ ያሳረፉ አንጋፋ ባለሙያ ናቸው። አቶ ል
Jemal Abdulaziz   አቶ ልዑልሰገድ ኩምሳ አቶ ልዑልሰገድ ኩምሳ በኢትዮጵያ በጋዜጠኝነት እና በተለይም በእንግሊዝኛ ዜና አንባቢነት ታዋቂ እና ትልቅ አሻራ ያሳረፉ አንጋፋ ባለሙያ ናቸው። አቶ ልዑልሰገድ የቋንቋ እና የኮሙኒኬሽን ክህሎታቸውን በትምህርት ካዳበሩ በኋላ ወደ ጋዜጠኝነት ሙያ ተቀላቀሉ። የእንግሊዝኛ ቋንቋ ችሎታቸው፣ አነባበባቸው (pronunciation) እና የድምፅ አወጣጥ ችሎታቸው የሚስብና በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን ያተረፈ ነበር። አቶ ልዑልሰገድ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ኢቲቪ / አሁን ኢቢሲ) እና በኢትዮጵያ ሬዲዮ በዋናነት በእንግሊዝኛ ቋንቋ ክፍል ውስጥ ለብዙ ዓመታት አገልግለዋል። ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ዜናዎችን፣ አበይት ኩነቶችን እና የክብር እንግዶች ጉብኝቶችን በከፍተኛ ትኩረት እና ሙያዊ ብቃት ያስተላልፉ ነበር። የነበራቸው ግልጽ፣ ማራኪ እና የሚስብ የእንግሊዝኛ ድምፅ በወቅቱ የቴሌቪዥን ተመልካቾች እና የሬዲዮ አዳማጮች ዘንድ የእንግሊዝኛ ዜና ዋና መለያ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። አቶ ልዑልሰገድ ለብዙ ታዳጊዎች እና የጋዜጠኝነት ተማሪዎች በእንግሊዝኛ ቋንቋ አጠቃቀም እና በዜና አቀራረብ ረገድ ትልቅ አርአያ (role model) ሆነዋል። በጋዜጠኝነት ዘመናቸው ለሙያው የነበራቸው ታማኝነት፣ ታታሪነት እና ስነ-ምግባር በስራ ባልደረቦቻቸው እና በህዝብ ዘንድ ትልቅ ክብርን አትርፎላቸዋል። በአጠቃላይ አቶ ልዑልሰገድ ኩምሳ በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ታሪክ ውስጥ ከነበሩት ምርጥ የእንግሊዝኛ ዜና አቀራረብ ባለሙያዎች መካከል አንዱ ሆነው ሁልጊዜ ይታወሳሉ።

Tab Amex ምስኪኗ H: እግዚአብሔር ፈቅዶና ወድዶኝ በዚህች አጭር ሕይወቴ ብዙ ሰዎችን ተዋውቄያለሁ። ለቁጥር ባለፈ ከመልካም ከወንዶችም ከሴቶችም ጋር ተቀራርቤያለሁ። በወጣትነቴ በመልካቸው ዐይንን
Tab Amex ምስኪኗ H: እግዚአብሔር ፈቅዶና ወድዶኝ በዚህች አጭር ሕይወቴ ብዙ ሰዎችን ተዋውቄያለሁ። ለቁጥር ባለፈ ከመልካም ከወንዶችም ከሴቶችም ጋር ተቀራርቤያለሁ። በወጣትነቴ በመልካቸው ዐይንን ከሚስቡ፥ በባሕርይ ልብን ከሚያስደነግጡ እጅግ መልካም ጥቂት ልጃገረዶችም ጋር ጣፋጭ ጊዜያትን አሳልፌ አውቃለሁ። እስከ አሁን ድረስ ሴት ልጅን ለመጠቀሚያ ወይም ለሌላ ነገር ሆን ብዬ ስላልበደልኩኝ፣ ጥበቃና ምሕረቱን ያበዛልኝን የእስራኤል አምላክ እጅግ በጣም አመሰግነዋለሁ። ከኮሌጅ ምርቃት በኋላ የመጀመሪያ ሥራ በተቀጠርኩት ከጥቂት (ምናልባትም 2-3) ዓመታት በኋላ፣ አንዲት ውብ ወጣት ለዲፓርትመታችን ሴክሬታሪነት ተቀጠረች። ለጥቂት ጊዜም ጋር አብሬያት እሠራ ነበር። “H” ማለት ምንም የማይጎድላት ሴት የምትባል አይነት ነበረች። እያጋነንኩኝ አይደለም። ቡጉር ጣል ጣል ያደረገባት ጠይም ፊቷ፥ አጠር ያለ ቁመቷና እጅግ የሚያምረው ብዙና ረጅም ጠጉሯ! ዋው ያስብላል። ጠባይና ትሕትናዋ በጣም ልዩ ነው። ከአፏ ማር የሚንጠባጠብ የምትባል አይነት በጣም የምታምር ውብ ልጅ ነበረች። ከተራ ወሬዎችና በጣም ጥቂት ጊዜ አብሮ ሻይ ቡና ከማለት ያለፈ ነገር አልነበረንም። የትውልድና የጊዜውን ግለ ታሪኳን በጥቂቱ ነግራኝ ነበር። H. እኔ ከመውጣቴ በፊት ወደ አሜሪካን አገር ሄደች። ከአንድ ወይ ሁለት ዓመታት በኋላ እኔም ከአገር ወጣሁ። ከወደ ሁለት ዓመታት በኋላ: ——— አገር ቤት ተመለስኩኝ። ከጥቂት ቀናት በኋላም የድሮ መሥሪያ ቤቴ ብቅ አልኩኝ። ከዚያም ከውቧ H. ጋር አብራ ትሠራ የነበረችውን M. አገኘኋት። “M. ስለ H. ትሰሚያሽ? ደኅና ናት?” ብዬ ጠየቅኋት። M. እጅግ አሳዛኝ ነገርን ነገረችኝ። H. የሄደችበት አገር በወሊድ እንደሞተች አረዳችኝ! — “H.” ምስኪኗ ነፍስ !

TABLETALK (September 2026) ______ #መሪ_ርዕስ: “Assurance of Salvation” - (፩- Assurance of Salvation in Scripture and the Spirit’
+2
TABLETALK (September 2026) ______ #መሪ_ርዕስ: “Assurance of Salvation” - (፩- Assurance of Salvation in Scripture and the Spirit’s Witness (p.4) - (፪ The Ultimate Ground of Assurance (p.9) - (፫- The Fruit of Faith and the Evidence of Grace (p.12) - (፬- Assurance Distortions (p.17) - (፭- Why Christians Struggle with Assurance (p.23) - (፮- Growing in Assurance Through the Means of Grace (26) ___ ቀጣይ እትም: #እምነትና_ሥራ

Jemal Abdulaziz የሒሳብ ሊቅ ዶ/ር ሙላቱ ለማ ዶ/ር ሙላቱ ለማ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሒሳብ ትምህርት ያጠናቀቁ ሲሆን፣ የዶክትሬት (Ph.D.) ዲግሪ
+1
Jemal Abdulaziz የሒሳብ ሊቅ ዶ/ር ሙላቱ ለማ ዶ/ር ሙላቱ ለማ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሒሳብ ትምህርት ያጠናቀቁ ሲሆን፣ የዶክትሬት (Ph.D.) ዲግሪያቸውን ደግሞ በአሜሪካ ከሚገኘው 'Kent State University' አግኝተዋል። ዶ/ር ሙላቱ በአሜሪካ ጆርጂያ በሚገኘው 'Savannah State University' በፕሮፌሰርነት እና በምርምር ዘርፍ ለበርካታ አስርት ዓመታት አገልግለዋል/እያገለገሉ ይገኛሉ። የሒሳብ ቀመሮች እና ግኝቶች (Mathematical Contributions)፤ ዶ/ር ሙላቱ በሒሳብ ምርምር ዘርፍ በርካታ ሳይንሳዊ ጽሁፎችን ያቀረቡ ሲሆን፣ በስማቸው የሚጠሩ አዳዲስ የሒሳብ ቀመሮችን እና ንድፈ-ሃሳቦችን (Mathematical Patterns/Formulas) አፍልቀዋል። በተለይም በ'Number Theory' እና 'Fibonacci Numbers' ዙሪያ ባደረጓቸው ጥናቶች ይታወቃሉ። የሽልማትና የእውቅና ማዕረጎች፤ በወጣቶች ትምህርት እና በሒሳብ ማሳደግ ላይ ባሳዩት ላቀ መሪነት እና አደራጅነት በርካታ ታዋቂ ሽልማቶችን አግኝተዋል፦ • የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሽልማት (Presidential Award for Excellence in Science, Mathematics and Engineering Mentoring) – በሳይንስ፣ ሒሳብ እና ምህንድስና ዘርፍ ወጣቶችን በማብቃትና በማስተማር ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ከ'ኋይት ሐውስ' የሚሰጠውን ታላቅ ሽልማት ተጎናጽፈዋል። • ማስታወሻ፦ ዶ/ር ሙላቱ እ.ኤ.አ በ2011 በስማቸው የተሰየመ "የሙላቱ ቁጥር" የተሰኘ የሒሳብ ቀመር ለዓለም አስተዋውቀዋል።

Jemal Abdulaziz «ኢትዮጵያ አገርህ በእውነት ትልቅ ሳትሆንና ወንድሞችህም ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሳይደላቸው አንተ ብቻህን የምታገኘው ደስታ ገንዘብና ተድላ በሕልም እንደተገኘ ወርቅ መና ባዶ ሆኖ
Jemal Abdulaziz «ኢትዮጵያ አገርህ በእውነት ትልቅ ሳትሆንና ወንድሞችህም ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሳይደላቸው አንተ ብቻህን የምታገኘው ደስታ ገንዘብና ተድላ በሕልም እንደተገኘ ወርቅ መና ባዶ ሆኖ የሚቀር መሆኑን ልብህ አይዘንጋው።» ∞ ∞ «ፀሐይ ጥዋት ጥዋት የምትወጣው የሱን ድምጥ ሰምታ እየመሰለው በልቡ ሲኮራ የሚኖር እንዳንድ አውራ ዶሮ አለ ይባላል። በሕዝብም መካከል እንደዚሁ ሊሰሩት የማይችሉትን ትልቅ ሥራ የሰሩ እየመሰላቸው በከንቱ ሲመኩ የሚታዩ ሰዎች ይገኛሉ።»

በዮናስ ቀንቻለሁ፤ ግን አድንቄዋለሁም ________ https://www.bbc.com/amharic/articles/czrj14x5j08o