en
Feedback
Bashewam Primary & Junior School 1-8

Bashewam Primary & Junior School 1-8

Open in Telegram

Bashewam School Grade 1-8

Show more
2 748
Subscribers
-224 hours
+207 days
+4230 days
Posts Archive
photo content
+9

👉.ዛሬ በቀን 23/03/2018 ዓ. ም በባሽዋም ት/ቤት በክፍለ ከተማ እና በወረዳ ደረጃ:-የተሰጡ የእዉቅና ሽለማቶች (ዋንጫ እና ሰርተፍኬት)መላ የባሽዋም ት/ቤት:- ተማሪዎች, መ/ራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች በተገኙበት ለተሽላሚዎች የርክክብ ስነ-ስርዓት በሞቀ እና በደመቀ ሂደት ተካሂዷል::

photo content

👉.ዛሬ ህዳር 18/2018 ዓ/ም የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 13  ትምህርት ጽ/ቤት ዓመታዊ የትምህርት ጉባኤ አካሄደ፡፡ 👉.በጉባኤዉ:- 1.✅   የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት 2.✅  የ2018 በጀት ዓመት እቅድ እና የ1ኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን  በ2017 ዓ.ም አፈጻጸምን መሠረት በማድረግ በወረዳዉ ለሚገኙ:- ✅.በከተማ አቀፍ  6ኛ እና 8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ዉጤት ላስመዘገቡ  ተማሪዎች:- ✅. ጥናት እና ምርምር ላደረጉ የ1ኛ ደረጃ መምህራን:- ✅. የተሻለ የስራ አፈፃፀም ላሳዩ ር/መምህራን ✅. የተሻለ የስራ አፈፃፀም እና ከፍተኛ የተማሪ ዉጤት ላስመዘገቡ የትምህርት ተቋማት ዕውቅናና ሽልማት ተሠጥቷል። 👉.በዚህ መሠረት የባሽዋም ት/ቤት:- 👉. ከ6ኛ ክፍል:- ✅. ተማሪ ደሊል ማስረሻ በወረዳ ደርጃ= 1ኛ በክፍለ ከተማ ደረጃ=2ኛ 👉.ከ8ኛ ክፍል :- ✅. ተማሪ ሄለን ቀኔ በወረዳ ደረጃ=1ኛ ✅.ተማሪ ህሩይ ደምላሽ በወረዳ ደረጃ=3ኛ በመዉጣት ተሽላሚ ሆነዋል:: ✅. ጥናትና ምርምር የሠሩና ጽብረቃ ካደረጉ መ/ራን መካከል:- ✅. መ/ር ጌቱ ሙሉጌታ በወረዳ ደረጃ= 2ኛ ✅.መ/ር አዴሳ ከተማ በአፋን ኦሮሞ በወረዳ ደረጃ=1ኛ በመዉጣት ተሽላሚ ሆነዋል:: 👉. ከር/መምህራን መካከል:- ✅. ወ/ሮ አዳነች በየነ ከቅድመ አንደኛ=2ኛ ✅.  አቶ አሳመረ ለማ ከአንደኛ ደረጃ=2ኛ በመዉጣት ተሽላሚ ሆነዋል:: 👉. ከትምህርት ተቋማት ✅. ባሽዋም ት/ቤት :- ባስመዘገበዉ   የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ከፍተኛ የተማሪዎች ዉጤት እና የተሻለ የስራ አፈፃፀም በ እንስፔክሽን ዉጤት =ሁለት (2)ዋንጫዎችን እና የሠርተፍኬት እዉቅና ሽልማት በቅድመ አንደኛው እና በአንደኛ እና መካከለኛ ደረጃዉ ተሽላሚ ሆኗል::  ለመላው የባሽዋም ማህበረሰብ በሙሉ(መ/ራን, ተማሪዎች, ወላጆች እና የአስተዳደር ሰራተኞች የጋራ የርብርብ ዉጤት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ!!! ባሽዋም ት/ቤት ሁሌም ለለዉጥ ዝግጁ ነን!!!

የ2018ዓም የመጀመሪያው ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር በ3ኛ እና በ4ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል
የ2018ዓም የመጀመሪያው ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር በ3ኛ እና በ4ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል

ባሸዋም ትምህርት ቤት ከ1ኛ - 4ኛ ክፍል የፈተና መረሐ ግብር
ባሸዋም ትምህርት ቤት ከ1ኛ - 4ኛ ክፍል የፈተና መረሐ ግብር

የተማሪዎች የሥነ ምግባር ረቂቅ መመሪያ በውስጡ ምን ምን አካቷል ? ➡️ " Crazy day ፣ olds day ፣ Valentine day " እና ሌሎችም አላስፈላጊ የሆኑ ባህልን የማይገልፁ ድርጊቶችን ማክበር ይከለክላል። መመሪያው በመንግስት ፣ መንግስታዊ ባልሆኑ ፣ የግል ፣ በኃይማኖት ተቋማት የሚተዳደሩ ትምህርት ቤቶችና ከኢትዮጵያ ውጪ ባሉ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት በሚማሩ ተማሪዎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል። በመመሪያው የተማሪዎች መብትና ግዴታዎች ሲቀመጡ በተማሪዎች ግዴታ ስር ፀጉርን በአግባቡ መሰራት/ማሳጠር፣ ከተፈጥሯዊ ጸጉራቸው ውጪ እንዳይጠቀሙ ተቀምጧል። የሴቶቾ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ ቀሚስ ቁመት ከባት በታች መሆን ያለበት ሲሆን ከአካባቢው ባህል ጋር የማይቃረን ልብስ መልበስ የሚለውም ተካቷል። በመመሪያው ከተከለከሉ ተግባራት መካከል ሲጋራ ማጨስ፣ አልኮል መጠጣት፣ ጫት መቃም፣ ዕፆችን መጠቀም/ማዘዋወር እንደዚሁም ሞባይልና የሙዚቃ ማዳመጫዎችን ወደ ትምህርት ቤት ይዞ መምጣት ይገኙበታል። በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ኃይማኖታዊ አምልኮ ስርዓትና የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችን ማከናወንም በመመሪያው ተከልክሏል። በመመሪያው ሀገራዊ እሴት ያልሆኑ መጤ ነገሮችን በሰውነት ላይ መነቀስ ሲከለከል፤ ሴት ተማሪዎች የጥፍር፣ የፀጉርና የከንፈር ቀለም ከመቀባትና ከመኳኳል እንደዚሁም አላስፈላጊ ጌጥ ከማድረግ ይከለክላል። በተጨማሪም በረቂቁ  በትምህርት ቤት ውስጥ አላስፈላጊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነት ባህልን የማይገልፁ ያላቸውን ድርጊቶች ፦ • Crazy Day, • Gentle Day, • Olds Day, • Baby Day, • Fruit Day, • Tomato Day, • Valentine Day, • April the full, • Color Day, • Pyjama Day…etc መፈጸም፤ እና ሌሎችም አላስፈላጊ የሆኑ ባህልን የማይገልፁ ድርጊቶችን ማክበር እንደማይቻል ተገልጿል። የተከለከሉ ተግባራትን በሚፈፅመት ላይ የተለያያ የእርምት እርምጃዎች ሲቀመጡ ቀላል እርምጃ ሊያስወስዱ በሚችሉ ጥፋቶች ስር ከፀጉር ጋር የተያያዙ እና ሌሎች ቀላል ጥፋቶች ተካተዋል። የትምህርት ቤት ፕላዝማና ኮምፒውተር ለሌላ አላማ መጠቀም፣ በአጥር መዝልና መሽሎክ፣ ከላይ የተጠቀሱ አላስፈላጊ ባህሎችን ማክበር፣ አሉታዊ ምልክቶችን መነቀስ፣ ድብድብ እንደዚሁም ኃይማኖታዊ ስርዓት መፈፀምና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ በከባድ ጥፋት ውስጥ ተካተዋል። የቅጣት እርከኑ እንደ ተማሪዎች የትምህርት ደረጃና ጥፋቱ ሲለያይ ለከባድ የስነ ምግባር ግድፈት በመደበኛ ህግ መሰረት የህግ ተጠያቂነት ይኖራል። መመሪያው የዲሲፕሊን ክስ አመሰራረት፣ የዲስፕሊን ኮሚቴ ስብጥር እንደዚሁም ተግባርና ኃላፊነትን በዝርዝር አስቀምጧል። ከዚህ ባለፈ ፦ • ትምባሆ (ሲጋራ፣ ሺሻ) • ጫት • አልኮል • የናርኮቲክ እና ሳይኮትሮፒክ ዝርያ ያላቸው አደገኛ ህገ ወጥ መድኃኒቶችና ሱስ አስያዥ ዕፆች በትምህርት ቤቶችና አካባቢ መገኘት፣ መጠቀም፣ መሸጥ፣ ማብቀል፣ ማምረት ወይም መለወጥ የተከለከለ እንደሆነ መመሪያው ላይ ተቀምጧል። እንዲሁም ፦ • የአልኮል መሸጫና ማከፋፈያ ቤቶች • የሲጋራ መሸጫ ሱቆች • ሺሻ ቤቶች • ጫት መሸጫና መቃሚያ ቤቶች • ጭፈራ ቤቶች • ቁማር ቤቶች • የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች • የሰውነት መታሻ (ማሳጅ) ቤቶች • የፊልም ማጫዎቻ ቤቶች • ፕሌይ ስቴሽን ቤቶች • ዲ.ኤስ.ቲቪ ቤቶች • ከረንቡላ ፑል •  ጆተኒ • ቢንጎ እና የስፖርት ቁማር መጫወቻ ቤቶችም እገዳ ተጥሎባቸዋል። በተጨማሪም መመሪያው በየደረጃው ያሉ የባለድርሻ አካላትን ተግባርያ ኃላፊነትም ዘርዝሮ ሲያስቀምጥ ማንኛውም ትምህርት ቤት ያለ መሸኛ ተማሪዎችን ተቀብሎ መመዝገብንም ከልክሏል። ትምህርት ሚኒስቴር በመመሪያው ላይ ምክረ ሃሳብ ያላቸው ሰዎች በ  https://forms.gle/R72ai6EiMnzZtGsC6 እንዲያቀርቡ ጠይቋል።