en
Feedback
ፈውስ መንፈሳዊ ዘጣና ቅዱስ ቂርቆስ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Fewus Menfesawi / ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ / Aba Gebrekidan Girma

ፈውስ መንፈሳዊ ዘጣና ቅዱስ ቂርቆስ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Fewus Menfesawi / ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ / Aba Gebrekidan Girma

Open in Telegram

ይህ ፈውስ መንፈሳዊ የተሰኘ መንፈሳዊ ጉባኤ ሲሆን በርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅ/ቂርቆስ ገዳም የ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ቤት የሚሰጡምሥክር መምህር በሆኑት በ ርእሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረኪዳን ግርማ የሚሰጡ ትምህርቶች ይተላለፉበታል።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ፈውስ መንፈሳዊ ዘጣና ቅዱስ ቂርቆስ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Fewus Menfesawi / ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ / Aba Gebrekidan Girma

Channel ፈውስ መንፈሳዊ ዘጣና ቅዱስ ቂርቆስ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Fewus Menfesawi / ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ / Aba Gebrekidan Girma (@fewus_menfesawi) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 12 465 subscribers, ranking 7 091 in the Religion & Spirituality category and 2 728 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 12 465 subscribers.

According to the latest data from 08 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 225 over the last 30 days and by 27 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 185.56%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 46.01% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 23 128 views. Within the first day, a publication typically gains 5 735 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 131.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ ፈውስ መንፈሳዊ የተሰኘ መንፈሳዊ ጉባኤ ሲሆን በርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅ/ቂርቆስ ገዳም የ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ቤት የሚሰጡምሥክር መምህር በሆኑት በ ርእሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረኪዳን ግርማ የሚሰጡ ትምህርቶች ይተላለፉበታል።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 09 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

12 465
Subscribers
+2724 hours
+867 days
+22530 days
Posts Archive
https://www.youtube.com/live/ezAOtDd5bjw?si=DCXucEb0Mgm6Wu0e 🔴 ሥርዓተ ማኅሌት ከርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም | ቀጥታ ስርጭት | ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ | Aba Gebrekidan

ይህንን ዓላማ ለመፈጸም ለምንገነባው ሆስፒታል በቂ ቦታ ለማግኘት የረዳንን እግዘብሔርን እርሱም ያከበራቸው ቅዱሳንን እያመሰገንን በእውነተኛው መድኃኒታችን በመድኃኔዓለም ቀን የሆስፒታላችን የመሠረት ድንጋይ ልናስቀምጥ መሆናችን ደግሞ ደስታችንን ዕጥፍ ድርብ ያደርገዋል። ከዚህም የደረስነው ነገም የምንደርሰው በማይናወጸው መሠረት በእርሱ ላይ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቁመን ነውና። ከመስቀሉ ሥር እናቱን “እናት ትሁናችሁ” ብሎ ባይሰጠንስ ቋጠሮ ሲጸናብን ማን ለእርሱ ነግሮ ያስፈታልን ነበር? ልጅ እያለን ወደ ወላጅ እናታችን እናለቅስ ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ከመድኃኔዓለም እናት እያለቀስን የወደድነውን የምንቀበልባት እናት ድንግል ማርያምን ስለሰጠንም እናመሰግነዋለን ። ውድ ኦርቶዶክሳውያን ይህንን መሬት እንድናገኝ የረዱንን ሁሉ የጉባኤ አምላክ ይስጥልን በሰማይ ቦታ ይስጣችሁ እያላችሁ እንድትመርቁልን እየጠየቅን፤ ቀዳሚት ፳፯-፲-፳፲፰ ዓም ከጧቱ 3:00 ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በተገኙበት በባሕርዳር የመሠረት ድንጋዩን ስለምናስቀምጥ እንኳን አደረሳችሁ፣እንኳን ደስ አላችሁ፣ አብራችሁን ለቆማችሁ ሁለ መድኃኔዓለም ከእናንተ ጋር ይሁን። እግዚአብሔር ገባሬ ኩሉ ወጣኔ ኩሉ ወፈጻሜ ኩሉ አኃዜ ኩሉ ወጸባጤ ኩሉ ሁሉን የጀመርህ ሁለን የምትፈጽም ሁሉን የያዝህ ሁሉን የወሰንህ መድኃኔዓለም ሆይ ከአንተው ተጠግተን የጀመርነውን እንደምትፈጽምልን ፈጽመን እናምናለን ። ለአንተ ለባሕርይ አባትህ ለአብ ለማሕየዊ መንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን ! አባ ገብረ ኪዳን ግርማ የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር መምህር

፫. ሁለንተናዊ ፈውስ ለመስጠት ቤተ ጉባኤያችን የወንጌል ቤተ ጉባኤ እንደመሆኑ ወንጌል ደግሞ የፈውስ ሕግ ናት፣ ስለሆነም ቤተ ጉባኤያችን ኃጢአትን በንስሐ ፣ አለማወቅን በማስተማር እንደሚፈውስ ሁሉ የታመሙትን ደግሞ በማኅበር ጸሎት፣ በጸበል እንዲሁም እግዚአብሔር እጁ ሰፊ ነውና በሕክምና አገልግሎትና በሰብአዊነት ተግባር ለሰዎች ፈውስ ለመስጠት ይህንን ሆስፒታል ሊገነባ ዝግጅቱን እየፈጸመ ነው። ፬. ወንጌል የተስፋ ሕግ ናት። ከአበው አንዱ መከራን ምን ያቀለዋል ቢሉት “ እስመ ተስፋ ያቀልሎ ለምንዳቤ - መከራን የሚያቀለው ተስፋ ነው ብሏል። በመሆኑም ተስፋችሁ አልቋል የተባሉ ወገኖቻችንን ሁሉ በመንከባከብ ልቡናቸው በሰላም እንዲያርፍና በተስፋ ምርኩዝነት ዘመናቸውን በዕረፍት እንዲፈጽሙ ማድረግ። ፭.ሰው መሥራት ፦ በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱሳዊ አረዳድ መሠረት የሰው ልጅ የፍጥረታት ዘውድ ነው። እግዚአብሔርን መስሎ የተፈጠረ እርሱ ነው፣ ከሰማይ በታች ያሉ ፍጥረታትን እንዲያስተዳደር ሥልጣን የተሰጠው ሰው ነው፣ ክርስቶስ የሞተለት የዘለዓለም ተስፋ የተሰጠውም ሰው ነው። በመሆኑም ቤተ ጉባኤያችን ክቡሩን የሰው ልጅ የቅድመ ጋብቻ ትምህርት በመስጠት፣ የባለትዳሮች እና የልጅ አስተዳደግ ሥልጠና በመስጠት፣ በሱስ የተጎዱ ወንድሞቻችንን በመንከባከብና እንደገና አዲስ ሰውንት እንዲያገኙ በማድረግ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገራችን በጎና ባለ አእምሮ ትውልድ ለመፍጠር ይህንን ሆሰፒታል ልንገነባ እየተፋጠንን ነው።

እግዚአብሔር ያለው ነገር እርሱ በወደደው ትክክለኛው ሰዓት ይፈጽማልና ፕሮጀክቱን ይፋ ባደረግን በዓመቱ በዚያው ቀን በወላዲተ አምላክና በቅዱሳን ጸሎት፣ ቅን ልቡና ባላቸው ወንድሞቻችንና እኅቶቻችን ጥረት ሆስፒታሉን ለመገንባት የሚያስችል 30,000 ካሬ ቦታ በባሕር ዳር ከተማ ሰኔ ፲፱-፳፲፰ ዓም በጉባኤ ቤታችን ምሥረታ ቀን ስለተቀበልን አምላከ ቅዱስ ገብርኤልን እናመሰግነዋለን ። ሆስፒታሉን የምንገነባባቸው ዓላማዎቻችንም፦ ፩. ፍጥረትን ሁለ በእግዚአብሔር መንገድ ለማገልገል፦ እግዚአብሔር አምላካችን ለክፉዎችና ለደጎች፣ለኃጥአና ለጻድቃን ዝናምን እንደሚያዘንብ ፣ፀሐይን እንደሚያወጣ የሆስፒታላችን ዓላማም ለሁሉም በምሕረት፡ እምነትን፣ ዘርንና ማንነትን ሳይለይ፣ ለሰው ልጅ ሁሉ የሚታዘንበት የምሕረት ማረፊያ መሆን ነው። ፪.ለጥበብና ለሳይንስ፦ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በሀገራችን የነበራትን የጥበብ ታሪክ በዘመናዊ የምርምር ዐቅም ማስቀጠል።

እንኳን ደስ አላችሁ ! “ እግዚአብሔር ገባሬ ኩሉ ወጣኔ ኩሉ ወፈጻሜ ኩሉ አኃዜ ኩሉ ወጸባጤ ኩሉ - ሁሉን የጀመረ ሁሉን የፈጸመ ሁሉን የያዘ ሁሉን የወሰነ እግዚአብሔር ” ለመላው ኦርቶዶክሳውያን ፣
+2
እንኳን ደስ አላችሁ ! “ እግዚአብሔር ገባሬ ኩሉ ወጣኔ ኩሉ ወፈጻሜ ኩሉ አኃዜ ኩሉ ወጸባጤ ኩሉ - ሁሉን የጀመረ ሁሉን የፈጸመ ሁሉን የያዘ ሁሉን የወሰነ እግዚአብሔር ” ለመላው ኦርቶዶክሳውያን ፣ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ሁሉን የምትችል የእግዚአብሔር ሰላም ከሁላችን ጋር ትሁን እንደምን ሰነበታችሁ? እኛ አምላከ አበው እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን ደኅና ነን። የተወደዳችሁ የቤተ ጉባኤያችን ቤተሰቦች፦ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሚገኘው የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ትርጓሜ ምስክር ት/ቤት፣ ቀድሞ ጌታ ከመወለዱ ዘጠኝ መቶ ዓመት በፊት መጻሕፍተ ነቢያት ሲተረጎሙበት፣ ኋላም ቅዱስ ያሬድ ሲያስተምሩበት፣ መምህር ኤስድሮስ ምሥጢር ያገመሩበት ገዳም እንደመሆኑ ሰኔ ፲፱-፳፲፬ ዓም የቀደመ ታሪኩን ለመመለስ ቤተ ጉባኤው እንደገና ተመሥርቷል። በመሆኑም በነዚህ ያለፉት አራት ዓመታት ውስጥ ፷፬ ደቀ መዛሙርትን ተቀብሎ አራቱን ጉባኤያት እያስተማረ ይገኛል። በተጨማሪም ለምእመናን በፈውስ መንፈሳዊ ሚዲያ ወንጌልን በአበው ቅዱሳን ሊቃውንት አስተምህሮ በማዳረስ ላይ ነው። በዓመት ውስጥ ለመነኮሳት ሥርዓተ ምንኩስናን በሚመለከት፣ለካህናት ኦርቶዶክሳዊ ኖላዊነትን በሚመለከት፣ ለምእመናን ስለ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብእና ስለ ልጅ አስተዳደግ ሥልጠናዎችን ይሰጣል። ከዚህም ጋር ደግሞ በሚከተሉት ወርቃማ ምክንያቶች ጠቅላላ ሆስፒታል በባሕር ዳር ከተማ ለመገንባት ፕሮጀክቱን ይፋ ካደረግንበት ከሰኔ ፲፱- ፳፲፯ ጀምሮ ለአንድ ዓመት ያክል በሀገረ ስብከታችንና በጠቅላይ ቤተ ክህነት ፈቃድ እንቅስቃሴ ስናደርግ ከርመናል።