ሐበሻ Creation
Open in Telegram
Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
677
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
May '24
May '24
+17
in 0 channels
April '24
+64
in 2 channels
Get PRO
March '24
+279
in 2 channels
Get PRO
February '24
+452
in 1 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 31 May | 0 | |||
| 30 May | 0 | |||
| 29 May | 0 | |||
| 28 May | 0 | |||
| 27 May | 0 | |||
| 26 May | +1 | |||
| 25 May | 0 | |||
| 24 May | 0 | |||
| 23 May | 0 | |||
| 22 May | 0 | |||
| 21 May | +1 | |||
| 20 May | 0 | |||
| 19 May | 0 | |||
| 18 May | 0 | |||
| 17 May | +1 | |||
| 16 May | 0 | |||
| 15 May | 0 | |||
| 14 May | 0 | |||
| 13 May | 0 | |||
| 12 May | +1 | |||
| 11 May | +1 | |||
| 10 May | +2 | |||
| 09 May | 0 | |||
| 08 May | +1 | |||
| 07 May | 0 | |||
| 06 May | +3 | |||
| 05 May | 0 | |||
| 04 May | +2 | |||
| 03 May | +1 | |||
| 02 May | +3 | |||
| 01 May | 0 |
Channel Posts
ለሰፈራችን ሰዎች የሰርግ መጥሪያ ካርድ ስጥ ተብዬ እኛ ሰፈር ያሉ ቤቶች በሙሉ እየገባው በየተራ እየሰጠሁ ነው በመጨረሻም ጥቂት የሚባል የሰርግ መጥሪያ ወረቀት ቀርቷል እጄ ላይ መጀመሪያ ላይ ያለውን አየሁት አቶ ሰይፈ ይላል ፈጠን ብዬ እየተራመድኩ ወደነ ጋሽ ሰይፈ ቤት ሄድኩ እዛም ስደርስ እንደለመደብኝ በሩን በስሱ ኳኳኳኳ አረኩት ከጊቢው ውስጥ ኸረ ቀስ በሉ በሩን ልትሰብሩት ነው እንዴ" የሚል ድምፅ ሰማው...አርግጠኛ ነኝ ጋሽ ሰይፈ ናቸው... ጋሽ ሰይፈ ማለት የሰፈር ሰው በሙሉ የሚያወቃቸው እና የሚፈራቸው ሰው ናቸው ይሄ ሁሉ እሳቸውን የመፍራታችንን ምክንያት ባላውቀዉም አንድ ጊዜ በማታ ወተው እኛ ሰፈር ያስቸግሩ የነበሩ ሌቦችን ከዘራ አፈር ከድሜ አብልተዋቸዋል የጋሸ ሰይፈ ባህሪ ነጭናጫ፣ተቆጪ፣ኮስታራ እና አንዳንዴ ደሞ ቀልደኛ ነገር ናቸው ግን ሁሌ በሁሉም ነገር መነጫነጭና መቆጣት ልማዳቸው ነው ፡በሩ ክፍት ስለነበር በትንሹ ከፈት አድርጌ አንገቴን ብቻ አጮልቄ ወደ ጊቢው ሳይ ጋሽ ሰይፈ በረንዳ ላይ ቁጭ ብለው አረቄ እየጠጡ ጋቢ ለብሰው ተቀምጠዋል በሩን በደንብ ከፍቼ "ሰላም ነው ጋሼ" እያልኩ ወደጊቢው ገባሁ እሳቸውም "እንዴ አንተ ነህ እንዴ ና ግባ" ብለው በትንሹም ቢሆን አቀባበል አደረጉልኝ እኔም ግርግር ሳላበዛ ለሳቸው ያመጣሁትን የጥሪ ካርድ አውጥቼ "ይኸው ጋሼ ይሄን ተልኬ ነወ" ብዬ ካርዱን የያዘውን እጄን ዘረጋሁት ከመቀበላቸው በፊት ምንድነው? ብለው ቆጣ አሉ...የሰርግ መጥሪያ ካርድ ነው ጋሼ" ብዬ ቁጣቸውንአበረድኩት "እእእእ ነው እንዴ" ብለው ከእጄ ላይ መንተፍ አርገው ወሰዱት...ያው እኔም ፀባያቸውን ስለማውቀው ምንም ሳይመስለኝ ፊቴን አዙሬ ልወጣ ስል "የማነው ሰርጉ? አሉኝ የኤፍሬም ነው ብዬ ቆምኩኝ
ኤፍሬም ይሄ ወጠጤው?
"አው ጋሼ ብዬ" ፈገግ አለኩ
ምን ያስገለፍጥሀል አንተም ከሱ የባስክ አደለህ ሲሉኝ ፈገግ ያለው ጥርሴ ወዲያው ሸፍን አለ...ስማ ደሞ ያ ለማ ሚባል ሰውዬ እዚ ሰርግ ላይ ተጠርቷል እንዴ?...ብለው አፈጠጠብኝ...ለማ ማን እንደሆነ ለማስታወስ እየሞከርኩ "አልተጠራም" ብዬ ዝም አልኩ
የታባቱ ይሄ ሌባ የእቁብ ብር ዘርፎ ድሮስ ማናባቱ ሊያስጠጋው...አረቄው ነው መሰለኝ እኔን አቁመው የባጥ የቆጡን ማውራት ጀመሩ... ለመሄድ ብፈልግም እሳቸው እያወሩ ሄድኩኝ ማለት የሚደርስብኝን መከራ እኔ ነኝ የማውቀው እሳቸው ሚያወሩትን ወሬ አንዱንም ሳልሰማ ጭልጥ ያለ ሀሳብ ውስጥ ገብቻለው...ድንገት ና ቁጭ በልና ከኔጋ አረቄ ጠጣ" የሚል ድምፅ ሰማው ...ደንገጥ ብዬ "አይ አልጠጣም ጋሼ" አልኩለኝ
ተናደዱ "ና ኮ ነው ምልህ" ብለው ፊታየወን አረገፋብኝ "እርሶ ሰውዬ ግን አላበዙትም እንዴ የሰፈር ልጆች ስለሚፈራዎት እኔም ግዴታ እርሶን መፍራት አለብኝ እንዴ? አሁን ደሞ ጭራሽ በግድ አረቄ ሊያስጠጠኝ ነው? አልጠጣም! ልል አሰብኩና አጠገባቸው ያለውን ታሪካዊ ከዘራ ሳየው ሀሳቤን ቀየርኩ ፡ እግሬ መሮጥ ቢያምረውም አጠገባቸው ያለው ትንሽዬ ወንበር ላይ ፈጠን ብዬ ቁጭ አልኩ ። ይኸው አሁን የአረቄ መጠጫ ላምጣልህ ብለው ሲሄዱ ነው ይሄን የፃፍኩት
አሁን ከዘራቸውን ይዤ ልጥፋ ወይስ አርፌ ልቀመጥ?
ከተቀመጥኩ ደሞ አረቄ ሊያስጠጡኝ ነው😭
መጡ.......መጡ......መጡ
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit
| 2 | ✅በዚ ጊዜ Online Money makers ከባንክ ቤት ሰራተኛ በላይ ገቢ እያገኙ ነው ያሉት🤑
🔋ነቃ እንበል እንጂ ወገን🔋
❤ኑ ያለምንም ስልጠና በቀላሉ በሞባይል ስልኮ የወር ደሞዝተኛ እናርጋቹ⭐️
❤ተቀላቀሉን @Trading_News_Com ✅ | 169 |
| 3 | የገባሁበት ታክሲ በጣም ከመሙላቱ የተነሳ ረዳቱ እራሱ ወርዶ ከታክሲው ኃላ እነሮጠ ሂሳብ-ወጣ ወጣ አርጉ እያለ ነው ሚከተለን... አውቄ ነው እቤት እኔኮ ሳጋንን አያምጣው ነው...ይሄን ያክል ማጋነን ምን ይሉታል አሁን? በርግጥ ታክሲው ሚጭነው 12ሰው ቢሆንም ታክሲ ውስጥ ያለነው ግን ወደ 2ዐ ገደማ ነን..እንደውም ማጋነን ሲያንሰኝ ነው..ታክሲው ጉዞውን ጀምሯል...የተቀመጥኩት ከሹፌሩ ኋላ ያለው የታክሲው የፊለፊት ወንበር ላይ ነው ለሁለት ሰው እንኳን የማይበቃው የታክሲ ወንበር 3ሰው ሹጥጥ ብሎ ተቀምጦበታል...ከተቀመጥነው ሶስት ሰዎች መሀል ላይ ያለሁት እኔ ነኝ መሀል መቀመጥ ምን ያክል እንደሚጨንቅ የሚያቀው ተቀምጦ ያየው ብቻ ነው...ወዲያወኑ ግን መሀል ላይ የመቀመጥን ጭንቀት የሚያስረሳኝ ነገር ተፈጠረ... ከኔ በግራ በኩል ወይም በመስኮቱ በኩል የተቀመጠችው
ቆንጅዬ ልጅ ስልክ እያወራች መጨቃጨቅ ጀምራለች...እኔም ምስጥ ብዬ ወረዋን ማደመጥ ጀምሬያለው
''እዚጋ ሂሳብ" አለ እረዳቱ
እሷ ምታወራው ወሬ ስለሳበኝ ረዳቱን ቀና ብዬም ሳላየው ከኪሴ ብር አውጥቼ ሰጠሁት...እወነት የኔ ፍቅር አንተ እንዳሰብከው አደለም ትላለች...በጭቅጭቁ መሀል ላይ ወሬወን ለመስማት በጣም ከመጓጓቴ የተነሳ ከስልኩ ሚመጣውን ድምፅ አንዳንዱን እየሰማሁ አንዳንዱን ደሞ እየገመትኩ መስማቴን ቀጠልኩ ምንም እንኳን ጭቅጭቅ ቢሆንም ልጅቷ ስታወራ የሆነ ውበት አለው "እንደሱ አደለም ቆይ ስማኝ" አሁን ተቆጣች...ሲመስለኝ ታክሲ ውስጥ የታጨቀው ሰው ሁሉ ሰምቷታል...እሷም እሱን አውቃ ነው መሰለኝ ጎንበስ ብላ እጇን ከአፏ እና ከስልኩ ፊለፊት አስደግፋ ማውራት ቀጠለች
በጣም ተናደድኩኝ፤ ምክንያቱም እስካሁን ስሰማ የነበረው ወሬ አሁን መስማት አልቻልኩም...እንደዚህ ለመስማት እንደጓጓሁ አልቀርም፤ የሚል አልህ ቢጤ ያዘኝና እኔም በትንሹ ጎንበስ ብዬ የጓጓሁለትን ወሬ መስማት ጀመርኩ...ተፈጥሮዬ ሆኖ ጆሮዬ በቀኝ አንድ ግራ ደግሞ አንድ ቢሆንም ለዛሬ ግን ሁለቱንም በግራ በኩል አድርጌ እየተገለገልኩባቸው ነው...አፏን በእጁ እንደሸፈነች ማውራቷን ቀጥላለች "ማታ አያቴ ጋር ነውያደርኩት ስልህ ለምን አታምነኝም?...ስትል ሰማኋት ኸረረረረረ..ጭራሽ ውጪ አድራ ነው? ከስልኩ የሚመጣውን ድምፅ ለመስማት በደንብ ጠጋ ብልም መስማት ግን አልቻልኩም
ያለኝ አማራጭ የሷን እየሰማሁ የስልኩን ደሞ መገመት ነው ገመትኩ..፤ አያትሽ ጋር የት? ይላል ብዬ አሰብኩ...አው እዛ ነበርኩ ስላልነገርኩህ ይቅርታ" አለች ቲሽ.... የገመትኩት ልክ አልነበረም ድምዷን ከቅድሙ የበለጠ ዝቅ አርጋ "አሁን ወዳንተ እየመጣሁ ነው" ስትል ሰማኋት
ድንገት "እዚ ጋ ወራጅ! ወራጅ ወራጅ!" በሚል ድምፅ ታክሲው ተናወጠ...ደንገጥ ብዬ ስዞር ከኔ በቀኝ በኩል የተቀመጠው ሰው ነው ለመውረድ እንደዚ ሚጮኸው...አቆመለት ሰውየውም እየተቻኮለ ከታክሲው ወረደ
''እኔም እዚጋ ወራጅ ነኝ አሳልፈኝ'' አለችኝ
ተናደድኩ! እንዴት እዚጋ ትወርዳለች ምናለ የጀመረችውን ብትጨርስ? እያልኩ አሳለፍኳት...እሷም ቀልጠፍ ብላ ወረደች አሁን ለሶስት ተጨናንቀን የተቀመጥንበት ወንበር ላይ ብቻዬን ፈልሰስ ብዬ ተቀምጫለሁ ፈልሰስ ብዬ መቀመጤ አንድ ነገር አስታወሰኝ
ስልኬን!
ስልኬስ?
ኸረ ስልኬን ከኪሴ አጣሁት ጎበዝ🙆♂
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 5 041 |
| 4 | ✅በዚ ጊዜ Online Money makers ከባንክ ቤት ሰራተኛ በላይ ገቢ እያገኙ ነው ያሉት🤑
🔋ነቃ እንበል እንጂ 🔋
❤ኑ ያለምንም ስልጠና በቀላሉ በሞባይል ስልኮ የወር ደሞዝተኛ እናርጋቹ⭐️
❤ተቀላቀሉን @Trading_News_Com ✅ | 142 |
| 5 | ስህተት ወይስ ምን?...ክፍል 7
ነቢል ወደ አዲስ አበባ ከሄደ በኋላ ፀባዩ በጣም መቀየር ጀምሯል። ኤማ እየደወለች ልታወራው ብትፈልግም እሱ ግን ሁሌም ስራ ላይ እንደሆነ እና ለማውራት እንደማይመቸው እየነገራት ብዙም ሳያወሩ ስልኩን ይዘጋዋል። ኤማ ግን መደወሏን አላቆመችም...እንደሌላ ግዜው ስራ ላይ ነኝ ብሎ እንዳይዘጋባት ቀኑን ሙሉ ሳትደውልለት ቆየችና ማታ 3 ሰአት ላይ ደወለችለት ኤማ ስልኩን ጆሮዋ ላይ አድርጋ የነቢልን ድምፅ ስትጠብቅ የሌላ ሰው ድምፅ ከስልኩ መሰማት ጀመረ ከስልኩ የወጣው ድምፅ እንደዚ ይላል "የደወሉላቸው ደንበኛ መስመሩን እየተነጋገሩበት ስለሆነ እባኮን ትንሽቆይቸው ይሞክሩ" የነቢል ስልክ ተይዟል ከሌላ ሰው ጋር እያወራ ነው ኤማ ብትናደድም ንዴቷን በውስጧ ያዝ አርጋ ትንሽ ቆይታ በድጋሚ ደወለችለት አሁንም ስልኩ ተይዟል የኤማ ንዴት እየባሰ መጣ ከኔ ጋር 5 ደቂቃ እንኳን ለማውራት ያቃተው አሁን በዚ ማታ ከማን ጋር እያወራ ነው እያለች ደጋግማ መደወሉን ተያያዘችው ኤማ ብዙ ነገሮችን ታግሳ አልፋለች ይሄንን ግን ማለፍ አልቻለችም ከ 3ሰአት ጀምሮ እየደወለች የቆየችው ኤማ ሰአቱን ስታየው 5 ሰአት ሊሆን ጥቂት ደቂቃዎች እንደቀሩት የስልኳ አናት ላይ ባለው ቁጥር አስተዋለች ይሄ ሁሉ ሰአት ከማን ጋር እያወራ ነው የሚለው ጥያቄ እንቅልፍ ነስቷት አደረ፡፡ ገና ከመንጋቱ ስልኳን እስታ ለ ነቢል ደወለችለት ስልኩ ጠራ...
"ሄሎ ኤማ"
ነቢል ከ እንቅልፉ የነቃ አይመስልም
"እንዴት አደርክ ነቢል ቀሰቀስኩህ እንዴን?" አለች
"ደና ነኝ ምነው በጠዋት በሰላም ነው?"
"አይ ማታ ኮ ስደውል ስልክህ ለረጅም ሰአት ተይዟል" አለችና ዝም አለች
እሱም ምንም መልስ አልሰጣትም
በሰላም ነው? አለች ዝምታውን ለመስበር ያክል
ምኑ? ብሎ መለሰ
ግልፅ መሆን እንዳለባት ስላሰበች ሁሉንም ነገር ትነግረው ጀመር ሰሞኑን ተቀይረህብኛል ችግር አለ እንዴ፣ ወይስ ያጠፋሁት ነገር አለ? ከኔ ጋር ለትንሽ ደቂቃ እንኳን ስልክ ማውራት አትፈልግም ማታ
ግን ለረዥም ሰአት ስልክህ ተይዞ ነበር ለኔ ብቻ ነው ጊዜ ያጣኸው?..እሺ ከማን ጋር ነበር ያን ሁሉ ሰአት ስታወራ የነበረው?
ከጓደኛዬ ጋር ሳወራ ነበር" አለና የሷን መለስ መጠበቅ ጀመረ
እኔ ማላውቀው ጓደኛ? ወይስ መናገር አልፈለክም?
አው መናገር አልፈለኩም!"
የባለፈዋ ልጅ ናት አደል? አው እሷ ናት ምትሆነው ሌላ ማንም አይሆንም ይሄ ሁሉ ነገር እየሆነ ያለው በሷ ምክንያት ነው አደል?.. ኤማ እንደለመደችው መበሳጨት ጀመረች ነቢል ጥቂት ዝም ብሎ ከቆየ በኋላ...ማታ ላንቺ ብደውልልሽ ለማውራት አይመችሽም ብዬ ኮ ነው አላት በ ፌዝ መልክ ኤማ ከቅድሙ የበለጠ ተናደደች። ከአይኖቿ ላይ ሊወርዱ ትንሽ ሰበብ ብቻ የሚፈልጉት እንባዎቿ ለመውረድ ተዘጋጅቸዋል። ንዴቷ ከአቅሟ በላይ ሲሆን ጆሮዋ ላይ የያዘችውን ስልክ ፊትለፊቷ ካለው ግድግዳ ጋር በሃይል ወርውራ ድምጥማጡን አጠፋችው...ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ኤማ መሬት ላይ ወድቃ የተሰባበረውን ስልኳን በእጇ እየለቀመች ማልቀስ ጀመረች። ነቢልን ለማግኘት አንድ ያላት መንገድ ስልኳ ነበር... አሁን ግን አጣችው ከዛን ቀን ጀምሮ ከነቢል ጋር ሳትገናኝ 7ቀን ሆናት አንድ ሳምንት ሙሉ ሳታገኘው መቆየት ለሷ ከባድ ነበር ለሱ ምን እንደሆነ ባታውቅም! በስምንተኛው ቀን በቅጡ እንኳን የማታውቃት የኤማ አክስት ከውጪ ሀገር እየመጣች እንደሆነ የምታርፈውም እነሱ ቤት መሆኑን አያቷ ነገረቻት። ከአያቷ ጋር የምትኖረው ኤማ ምንም እንኳን ከውጪ ምትመጣው የማታውቃት አክስቷ ብትሆንም በመምጣቷ ደስ ብሏታል። አመሻሹ ላይ የኤማ አያት እልልልልልል እያሉ በረንዳው ላይ የደስታ እልልታቸውን ማቅለጥ ጀመሩ። አክስትየው መጣች የነኤማ ቤት ሰው በዛበት። ሁሉም የሰፈሩ ሰው እንኳን ደስ አላቹ እያለ ደስታውን መግለፅ ጀመረ። ኤማ በስራ ተጠምዳለች ከውጭ ለመጣችው አክስቷ እና ለጎረቤቶቿ ቡና ስትቆላ እራት ስታቀርብ ቡና ስታፈላ እና ጉድ ጉድ ሰትል ቆየች። በዚ ሁሉ መሀል ግን ስለ ነቢል ሳታስብ አልቀረችም። እነሱ ቤት ከተሰበሰበው ሰው መካከል ስልክ ያለው ብቸኛ ሰው ቢኖር ዛሬ ከውጭ የመጣችው አክስቷ ብቻ ናት። ኤማ አንድ ሀሳብ በአይምሮዋ መመላለስ ጀመረ የአክስቷን ስልክ ሰርቃ ለነቢል መደወል!
ይቀጥላል ....
ፀሐፊ የአብስራ
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 862 |
| 6 | ስህተት ወይስ ምን? ክፍል 6
ከዛን ቀን ጀምሮ ኤማ ነቢልን ብዙ መጠራጠር እና ባገኘችው ቁጥር ብዙ ጥያቄ መጠየቅ ጀምራለች
በዛች ልጅ ምክንያት ቀን በቀን መጨቃጨቃቸው ቀጠለ
ነቢል ግን ለምትጠይቀው ጥያቄ ምንም አይነት ትክክለኛ መልስ ሊሰጣት ፍቃደኛ አደለም ኤማ በዚ ምክንያት ያለ ባህሪዋ ጭናጫ፣አኩራፊ፣ተናዳጅ፣ተቆጪ እና ብስጩ ሆናለች፡፡ አሁን አሁን እንደወም ብስጭቷ ወደ ህመም እየተቀየረ ነው የተናደደች ቀን ወይም የተጨነቀች ቀን መታመም ጀምራለች...ቆይ አትወደኝም እንዴ? እየተናደደች ትጠይቀዋለች ነቢል የኤማን ንዴት ከምንም ሳይቆጥር በዝምታ ለብዙ ደቂቃ ይቆያል "ንገረኝ እንጂ ነባ ድጋሚ ቃል ከአፏ አወጣች...ምን ልንገርሽ?"
ትወደኛለህ ወይስ አትወደኝም?
ምን አይነት ጥያቄ ነው? ይላታል እጁን ወደኪሱ ከቶ ቁርጥራጭ ሲጋራዎችን ወደ መሬት እየጣለ
መመለስ ነው የከበደህ ወይስ አልወድሽም ለማለት ቀላል ቃል እየፈለክ ነው' ኤማ ጥያቄዋ ሙሉ ለሙሱ ወደ ቁጣ ተቀየረ ነቢል ለጥያቄዋ መልስ ከመመለስ ይልቅ በቃ ቻው ልሂድ" አለና ከኪሱ አውጥቶ እየጣለ ከነበረው የሲጋራ
ቁራጭ አንዱን በእጁ ይዞ ፌቱን አዙሮ ሄደ
ኤማ የራሷን ጥያቄ እራሷ መመለስ ጀምራለች። ከቀን ወደ ቀን የሚያሳያት ባህሪ እየተቀየረ ነው..ለዛም ነው ለኔ ያለው ስሜት ተቀይሯል የሚለው ጥያቄዋን እራሷ እየመለሰች ያለችው፡፡
ኤማ 12ተኛ ክፍል ደርሳለች በሚቀጥለው አመት ጥሩ ውጤት አምጥታ ወደ ዩኒቨርስቲ የምትገባበት አመት ነው ምናልባት የነቢል ፀባይ መቀየር ዋነኛ ምክንያት ይሄ ይሆናል ብላ ማሰቧም አልቀረም በፍቅራቸው ውስጥ የገባች አንድ ሴት የነቢልን ፀባይ አትቀይረውም የፀባዩ መቀየር ምክንያት እኔ ነኝ ብላ ራሷን ለማሳመንም ትሞክራለች። ፍቅር ሀያል ነው ሲባል ሀያልነት ውስጥ ብዙ ዝርዝሮች አሉ ለምሳሌ ረቂቅነት፣ድብቅነት፣ጅልነት...ጅልነት በፍቅር ውስጥ ትርጉሙ ሌላ ነው። ኤማን ጅል ያረጋት ባህሪዋ ሳይሆን ፍቅር ነው ፍቅር ጅል ያረገው ሰው ደሞ አንዴ ብቻ ከማሰብ ውጪ ሌላ አማራጭ የለውም ለዛም ነው በቀጣይ አመት ዩኒቨርስቲ መሄዷን ከሱ መቀየር ጋር አገናኝታ ነገሩን ሁሉ ጠምጥማ እራሷ ላይ የጣለችው። ዩኒቨርሲቲ ስትሄጂ ሁሌም እራስሸን ከ ወንዶች ጠብቂ እያለ ሁሌም ይነግራት ነበር ኤማ ግን ከዚ የበለጠ ሀሳብ የሆኑባት ብዙ ነገሮች ነበሩ አንድ ቀን በተፈጠረ ድንገተኛ የስልክ ጥሪ የኤማ እና የነቢል የቀድሞው ግንኙነት እንዲህ መሆኑ እና በዛች ቅፅበት ስልኩን ሀሎ ያለችው ሴት ማናት የሚለው ጥያቄ ለሰከንድ ከኤማ አእምሮ ወቶ አያውቅም እንደውም በሁለቱ መሀል የተፈጠረውን ክፍተት የበለጠ የሚያሰፉ ነገር ተፈጠረ ነቢል ወደ አዲስአበባ ለመሄድ ዝግጅት ጀመረ ኤማ ለምን እንደሚሄድ ብትጠይቀውም "ለስራ ነው ምሄደው" ከማለት ያለፈ ምንም አልነገራትም...ኤማ ደስ አላላትም፤ ለስራ ነው ምሄደው ያላትን ለማመን ብትሞክርም ውስጧ ግን በጣም አዝኗል...ነቢል ወደ አዲስአበባ ሊሄድ አንድ ቀን ቀረው...
ይቀጥላል....
ፀሐፊ የአብስራ
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 733 |
| 7 | ስህተት ወይስ ምን?...ክፍል 5
አይኗ እንደታሰረ በቦታው ደረሱ
ቀስ ብሎ ከመኪናው ካወረዳት በኋላ አይኗ ላይ ያለወን ጨርቅ እንድትፈታ ጠየቃት
እሷም የአይኗ መታሰር ምቾት ነስቷት ስለነበር ወዲያው ጨርቁቱን ከአይኗ ላይ ፈታችው
ዙሪያዋን ስትመለከት ግን ማንም የለም
አጠገቧ ሆኖ ጨርቁን እንድትፈታ የነገራት ነቢልንም ከአጠገቧ ልታገኘው አልቻለችም...ግራ ተጋባች መጮህ አማራት ባለችበት ቦታ እየተዟዟረች የት እንዳለች ማየት ጀመረች ቦታው ብዙ ዛፎች ያሉበትና ፀጥ ያለ ነው ፀጥታውን በትንሹ ሰብሮ ለመግባት የሚሞክር ለስላሳ ሙዚቃ ከሩቅ ይሰማል የኤማ ትኩረት ሙዚቃው ላይ ሆነ...በትንሹ የተከፈተወን ሙዚቃ መስማት ብትችልም ድምፁ ከየት እንደሚመጣ እና ምን አይነት ሙዚቃ እንደሆነ ማወቅ አልቻለችም ኤማ ግራ ተጋብታ በቆመችበት ቆየች..ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ "ኤማ" የሚል ድም ሰምታ ድምፁን ወደሰማችበት አቅጣቻ ስትዞል ነቢል በእጁ አበባ ይዞ ራቅ ብሎ ቆሟል...ነቢል ምንድነው? ኤማ ግራ ተጋባች
ነቢል ፈገግ እያለ በዝምታ ቆየ
'ምንድነው ነቢል ንገረኝ እንጂ፤ ኤማ ከድንጋጤዋ ብዛት መቆጣት ጀመረች ነቢል አሁንም ፈገግ እያለ "መልካም ልደት ኤማ" በስሱ ይሰማ የነበረው ሙዚቃ አሁን ድምፁ ከፍ ብሏል ሙዚቃው ከሁሉም ሰው የ ደስታ ቀን ጀርባ የማይጠፋው "ልዩ ቀን ነው ልዩ.... የሚለው የ ሄኖክ አበበ ሙዚቃ ነው...
ኤማ የሚሰማት ስሜት ተደበላለቀባት ደስታ ይሁን ሀዘን ይሁን ድንጋጤ መለየት አቅቷታል
ኤማ ዛሬ የተወለደችበት ቀን ነው የዛሬ 2ዐ አመት የካቲት 17 ቀን ነበር የተወለደችው..እስከዛሬ ድረስ አንድም ቀን ልደቷን አክብራ አታውም ዛሬ ግን ነቢል በእጁ አበባ እና ኬክ ይዞ ለመጀመሪያ ግዜ ኤማን መልካም ልደት አላት...
ኤማ ስሜቷን መቋቋም አቃታት ነቢልን ትኩር ብላ እያየች እንባዋ መውረድ ጀመረ...
የዛን ቀን አሪፍ የሚባል የፍቅር ጊዜ አሳለፉ...
ከዛን ከን ቀኋላ ኤማ ስለ ነቢል የሚሰማት ስሜት መቀየር ጀመረ...ያቺ ሰው አላምንም ሰው አልወድም ሰው አልጠጋም የምትለው ኤማ አሁን ሙሉ ለሙሉ ራሷን ፍቅር ውስጥ ገብታ
አገኘችው...አበደችለት ሳታየው መዋል እስከሚያቅታት ድረስ ለሱ ያላት ስሜት ተቀየረ ያኔ በሳምንት አንዴ ምታገኘውን ነቢል አሁን ቀኑን ሙሉ ፍላጎቷ እሱ ብቻ ሆኖ ቀረ በሱ እቅፍ ውስጥ መዋል የሷ አለም ሆነ የሱን ድምፅ መስማት ሁሌም የምትናፍቀው ሱስ ሆኖባት ቀረ ቀስ በቀስ ብላ የማታውቀውን የፍቅር አለም መልመድ ጀመረች ለመጀመሪያ ግዜ የኤማን ከንፈር በከንፈሩ የነካው ነቢል ነበር የዛን ቀን ለሷ የመጀመሪያው አስፈሪም አስደሳችም ቀን ነበር። ያኔ ሲስማት
ያፈረችው ኤም አሁን ያለምንም ፍርሀት ግጥም አርጋ ትስመዋለች። ያኔ ሲያወራት ለመልሷ ምትቆጠበው ኤማ አሁን ከሱ ጋር እንደልቧ ማውራት ጀምራለች። ከሱ ተለይቶ ለትንሽ ሰአታት መቆየት ማለት ለሷ ትልቅ ህመም እየሆነባት መጣ ሳታውቀው ያለሱ መኖር ማትችልበት ደረጃ ላይ ደረሰች
ከሱ ጋር ብዙ ነገር ማድረግ ፍቅር እንጂ ብልግና መሆኑ አልታይ ብሏታል። እናቷ ፊት ልብሷን እንኳን መቀየር ምትፈራዋ ልጅ አሱ ፊት ምንም ማፈር አቁማለች።
ቀናቶች እያለፉ በመጡ ቁጥር ለሱ ያላት ፍቅርም እየባሰ መጣ ትምህርቷን አቁማ ሁሌ ከሱ ጋር ብትውል ደስታዋ ነበር። ከትምህርት ቤት ስትመለስ ነቢል ቤት ደረስ ይሸኛታል አንዳንዴም ወደቤት ይገባል።
አንድላይ ሆነው በጣም ብዙ ነገር ማድረግ ጀምረዋል መሆን ሚገባትን ሁሉ ሆናለታለች አለኝ የምትለውን የሂወቷን ውድ ነገር ሰታዋለች። ምንም እንኳን ደፍረው ወሲብ ባይፈፅሙም ከሱ ማይተናነስ ነገር ነበር አብረው ሚያደርጉት። ሁለቱም የሚያደርጉት ነገር ልክ እንዳልሆነ ያውቃሉ ላለማድረግ ቢሞክሩም ሁሌ ስሜታቸው እንደ አዲስ ይፈካል..በዚህም ምክንያት ብዙ ጊዜ ይጨቃጨቃሉ ብዙ ጊዜም ይኮራረፋሉ...
አንድ ቀን በዚሁ ምክንያት እንደተኮራረፉ ኤማ ትታመማለች ነቢልም እቤት ድረስ መቶ ይጠይቃትና መድሐኒት ሊገዛላት ተጣድፎ ይወጣል። በችኮላ ሲወጣ ስልኩን እዛው ረስቶ ነበር የወጣው.. ኤማ በተኛችበት ቦታ ላይ ስልክ ሲጠራ ትሰማና ተነስታ ስልኩን ታየዋለች የጠራው ስልክ የነቢል ነበር... ኤማ ስልኩን አንስታ ነቢል እንደሌለ እና ሲመለስ እንደሚደውል ተናግራ ስልኩን ትዘጋዋለች። ነቢል መድሀኒቱን ገዝቶ ሲመለስ "ነባ ቅድም ስልክህን ረስተህ ወተህ ሲጠራ ነበር" አለችው እዛው በተኛችበት
ነቢል በድንጋጤ ስልኩን አንስቶ አየና "አንስተሽ አውርተሻል እንዴ? አለ በቁጣ ድምፅ
አዎ.. አሁን የለም ሲመለስ ይደውላል ብዬ ዘጋሁት
ለምን? ነቢል ከቅድሙ የባሰ ተቆጣ ነቢል የመቆጣቱ ምክንያት ባይገባትም ቀስ ብላ ልታስረዳው ሞከረች
ምናልባት የስራ ስልክ የሆናል ብዬ ስላሰብኩ አንስቼ ስትመለስ እንደምትደውል ተናግሬ ዘጋሁት ምነው ችግር አለው?
አ.አ.አይይይ ችግር የለውም ግን ማን እንደሆነ ነግሮሻል?
ስላመመኝ ነው መሰለኝ ምንም ነገር አልሰማሁም ብቻ ግን ሲመጣ ይደውላል ብዬ ነው የዘጋሁት
ነቢል ሳይታወቀው ኡፍፍፍፍ ብሎ በረጅሙ ተነፈሰ ይሄን የሰማችው ኤማ መጠራጠር ጀመረች...ወዲያው ከተኛችበት ተነስታ በጥያቄ አፋጠጠችው
ማነው የደወለው?
ማንም የስራ ስልክ ነው መሰለኝ
ታዲያ ለምን ተቆጣህ?
አ.አ።.አይይይይይ
ሴት ናት?
ይቀጥላል...
ፀሀፊ የአብስራ
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 603 |
| 8 | ስህተት ወይስ ምን? ክፍል 4
ነቢል ከ አንድ ሳምንት በፊት እንደሚወዳት ነግሯት ሁለቱም
ተጨቃጭቀው ነበር የተለያዩት
ነቢል ሳምንቱን ሙሉ ጭንቀት እና ፍርሀት እየተፈራረቁ ሲቀጡት ቆዩ
ያ ሲጋራ የሚያጨስበት ከንፈሩ ከሌላ ጊዜው በተለየ መልኩ ጠቁሯል
እነዛ በመጠጥ ብዛት የቀሉት አይኖቹ ዛሬ ደማቅ ቀይ ሆነዋል
የለበሰው ነጣ ያለ ልብስ እላዩ ላይ ያረጀ እስኪመስል ድረስ ጠቁሯል
እነዛ ሲጋራ ቆልፎ ይዞ የሚያጨስባቸው ጣቶቹ መንቀጥቀጥ
ጀምረዋል
ዛሬ ኤማን የሚያገኝበት ቀን ነው
ሁሌ የሚገናኙበት ቦታ ሄዶ እሷን ቁጭ ብሎ መጠበቅ ከጀመረ ሰአታት ተቆጠሩ ኤማ አልመጣችም። ነገር ግን እየጠበቃት ነው
ነቢል የእጁን መንቀጥቀት ሲያስተውል ፈጠን ብሎ እጁን ወደ ጃኬት ኪሱ ውስጥ ወሸቀው
እጁን የከተተበት አንደኛው የጃኬት ኪሱ ውስጥ የተቆረጠ ሰጋራ አገኘ ከኪሱ አውጥቶ ትንሽ ካየው በኋላ ከኋላ ኪሱ ክብሪት አውጥቶ ቁራጯን ሲጋራ በትንሹ አቃጠላት
ለማጨስ የለኮሰውን ሲጋራ ወደ አፉ ሲያስጠጋው የኤማን መምጣት ከሩቅ አየ..በድንጋጤ ክብሪቱንም ሲጋራውንም ወደ ኋላ ጥሎ አፉን እና ሙሉ ፊቱን መጠራረግ ጀመረ
ኤማ አጠገቡ ስትደርስ እንደሌላው ጊዜ ሰላም አላለቸውም ቀሚሷን እንደነገሩ ሰብሰብ አርጋ አጠገቡ ቁጢጥ አለች "ደና ነሽ ኤማ? ጠየቃት
ምንም መልስ አልሰጠችውም ይልቅ አንገቷን ደፍታ መሬት ላይ ያሉትን ሳሮች በእጇ እየዳሰሰች በሀሳብ ጭልጥ ብላለች
ነቢል ጥያቄውን ደገመው "ኤማ ደና ነሽ?"
ቀና ብላ አየችውና 'ይሄ ሱስ ኮ እየጎዳህ ነው ታውቃለህ አደል? አሁንም አይኗ እሱ ላይ ነው
እሱ ግን ቀና ብሎ ማየት አልቻለም በዝምታ አንገቱን ደፍቶ የምትለውን ይሰማታል
'በተለያዩ መንገዶች ልነግርህ ሞክሪያለሁ አንተ ግን ምንም ልትረዳኝ አልቻልክም ነቢል፤ አንተኮ አሁን ከ ሱስህ ጋር ሳይሆን ከ ኑሮህ ጋር ነው መታገል ያለብህ ከዛሬ ነገ ትተዋለህ ብዬ ጠበኩህ ግን ይኸው እንደውም አሁን ላይ ጭራሽ ራስህን ትተህ ለሱስህ መኖር እየጀመርክ ነው
ነቢል አንገቱን ከደፋበት ቀና አላለም...ያላሰበው ነገር በመሆኑ ቢገረምም ባለፈው አፍቅሬሻለሁ ብዬ የነገርኳትን ስሜቴን ረስታው ነው ወይስ? የሚል ጥያቄ በውስጡ ሲመላለስ ነበር ኤማ የዛን ቀን ምንም እንዳልተፈጠረ ሆና ነበር ያናገረችው በዚ የተገረመው ነቢል ስሜቱን በመናገሩ ውስጡን አንዳች ስሜት ቢሰማውም የኤማ እሺ ወይም እምቢ የሚለውን የፍቅሩን ጥያቄ ምላሽ ሳያውቅ ቆየ... የሁለቱ ግንኙነት ምን እንደሆነ እንኳን ሳይታወቅ እንዲው ግራ በተጋባ ስሜት ውስጥ ሆነው ብዙ ቀናት አለፉ ነቢል ያለበትን ሱስ ሙሉ ለሙሉ ባይተው እንኳን እንደሚቀንስ ሁሌ ለኤማ ቃል ይገባላታል ሁሌም ቢሆን ባገኛት ቁጥር "ትላንትኮ አንድ ብቻ ነው ያጨስኩት ትላንት ግማሽ ብቻ ነው የጠጣሁት" "ጫትኮ አቆምኩ ዛሬ አንዱን ሲጋራ ቆርጩ ግማሹን ነው ያጨስኩት" እያለ ሁሌም ይነግራታል የኤም እና የነቢል ግንኙነት ግልፅም ድብቅም በማይባል መልኩ ቀጠለ
አንድ ቀን ጠዋት ነቢል ኤማ ጋር ደውሎ ከ እንቅልፏ ይቀሰቅሳታል
ኤማ ስልኩን አነሳችው
በር ላይ እየጠበኩሽ ነው የምወስድሽ ቦታ አለ ይላትና ስልኩን ወዲያው ይዘጋዋል
ግራ የተጋባችው ኤማ መልሳ መደወል ጀመረች ነቢል ግን ስልኩን አላነሳም..ምንም አማራጭ ስላልነበራት ከተኛችበት ተነስታ ፊቷን እንደነገሩ ታጥባ ልብሷን እንደነገሩ ቀይራ ወጣች ነቢል በር ላይ ፈገግ ብሎ ተቀበላት..እጁ ላይ የያዘወን ሻርፕ እያሳያት አይንሽን በዚ እሰሪ የሆነ ቦታ ልወስድሽ ነው ብሎ እራሷ አይኗ ላይ
እንድታስረው በእጇ ሰጣት ኤማ ከድንጋጤዋ ውጪ ምንም የጠረጠረችው ነገር የለም...ሻርፑን
አይኗ ላይ አሰረችው አይኗ ላይ እንዳሰረችው ወዲያው አንድ መኪና ከአጠገቧ ቆመ ነቢል እጇን ይዞ
"ወደ መኪና ውስጥ ጊቢ" አላት
አሷም በእጇ እየዳበሰች መኪና ውስጥ ገብታ ተቀመጠች ነቢል ከ አጠገቧ ተቀምጧል...መኪናው መሄዱን ቀጠለ....ወዴት?
ይቀጥላል....
ፀሀፊ የአብስራ
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 529 |
| 9 | ስህተት ወይስ ምን? ክፍል 3
ደንግጣ ስትዞር ነቢል ነው ነቢል በ አንድ እጁ ጥላ በአንድ እጁ ደሞ የሷን እጅ አጥብቆ ይዟል
ኤማ ደነገጠች...የሚዘንበውን ዝናብ ለመከላከል እጇን ግንባሯ ላይ አድርጋ "ምነው ነቢል በሰላም ነው? አለች ነቢል እያለከለከ ነው ሱሰኝነቱ አደለም ለመሮጥ በፍጥነት ለመራመድ እንኳን እስከሚያቅተው ድረስ ጎድቶታል
በዚ ዝናብ ብዙ ርቀት እንደሮጠ ያስታውቃል
ትንፋሹ እየተቆራረጠ "እንኪ.።.. ዝ..ዝናብ እንዳይመታሽ" አለ በአንድ እጁ የያዘውን ጥላ እንድትቀበለው እጁን እየዘረጋ ኤማ ጥላውን መቀበል ትታ ነቢልን እያየች ፈገግ ማለት ጀመረች ትንሽ ከቆየች በኋላ አመሰግናለሁ ነቢሎ" አለችና ጥላውን ዘርግታ ወደ ትምህርት ቤት በፍጥነት መራመድ ጀመረች ከዛን ቀን ጀምሮ ነበር ኤማ የነቢል ጉዳይ ያሳስባት የጀመረው እንደውም የሆነ ቀን ከትምህርት ቤታቸው ፊት ለፊት ያለው ባለሱቅ ከሩቅ ሆኖ ኤማ ከትምርት ቤት ስጥወጣ ይጠራትና ሙሉ ካርቶን እስክርቢቶ ይሰጣታል
ኤማ ደንግጣ ምንድነው ብላ ባለሱቁን ጠየቀችው
ባለሱቁም "የሆነ ሰው ላንቺ እንድሰጥ አዞኝ ነው" አላት ነቢል ነበር ይሄን የሚያደርገው ነቢል ከትንሽ እስከ ትልቅ ብዙ ስጦታዎችን ይሰጣት ነበር
ኤማ ግን ከትንሽ ጊዜ በኋላ የነቢል ነገር አልተዋጠላትም
ለሷ ብሎ በሚያደርጋቸው ነገሮች መጠራጠር ከጀመረች ሰንበትበት ብላለች
"ምናልባት ወዶኝ ይሆን? አይ አይሆንም? ታዲያ ለምንድነው ለኔ ይሄን ሁሉ ነገር ሚያደርገው? ኤማ መጨነቅ ጀመረች ጭንቀቱ ሲበዛባት ነቢልን እንደበፊቱ መቅረብ አቆመች... ከሱ መሸሽ ጀመረች ከዚ ቀደም በቀን በቀን ታገኘው የነበረችው ኤማ አሁን ግን በሳምንት አንዴ ወይም ሁለቴ ነው ምታገኘው የምትሰጠው ምክንያት ደሞ አክስቴ ጋር ስራ ስለሚበዛብኝ እንደበፊቱ ላገኝህ አልችልም የሚል ነበር ነቢል ኤማ በጣም እየራቀችው እንደሆነ ሲሰማው እንደሚያፈቅራት ሊነግራት ወሰነ እንዴት እንደሚነግራት ግን አያውቅም ነቢል በሳምንት አንዴ ኤማን ሚያገኝበትን ቀን መጠባበቅ ጀመረ
ቀኑ ደረሰ...
እሷ እስከምትመጣ አንዲት ሲጋራ በ ሁለት ጣቶቹ መሀል ይዞ ወደ ከንፈሮቹ እያመላለሰ እያጨሰ እየጠበቃት ነው መምጣቷን ከሩቅ ሲያይ ያልጨረሰውን ሲጋራ መሬት ላይ ወርውሮ ረገጠው አጠገቡ ስትደርስ ከሰላምታ አስቀድሞ እንደሚያፈቅራት ነገራት ኤማ የፈራችው ነገር እውን ሆነ ነቢል ደገመው "ኤማ አፍቅሬሻለሁ"
ኤማ መለፍለፍ ጀመረች "'እኔ መውደድ አልችልም እኔ ማፍቀር አልችልም እኔን ልታፈቅረኝ አይገባም እኔ ለፍቅር ምሆን ሰው አደለሁም" እያለች ብዙ ነገር ትነግረው ጀመር እሱ ግን ሊሰማት ፍቃደኛ አልነበረም በተደጋጋሚ እንደሚያፈቅራት እና ሰሞኑን የሷ መራቅ እያስጨነቀው እንደሆነ እየደጋገመ ይነግራታል...የዛን ቀን ተነጋግረው ሳይግባቡ ሁለቱም እንደተጨነቁ ወደ ቤታቸው ሄዱ ነቢል ኤማን ከሳምንት በኋላ እንደሚያገኛት ሲያስብ የበለጠ መጨነቅ ጨመረ ጭንቀቴን ያጠፋልኛል ብሎ ሚያስበው ሱሱን ስለነበር ከበፊቱ በተለየ
መልኩ ማጨስ መቃም እና መጠጣት ጀመረ
መናገር አልነበረብኝ እያለ እራሱን መውቀስ ከጀመረ ሳምንት ሆነው እሷን ድጋሚ ሚያገኝበት ቀን ደረሰ...
ይቀጥላል...
ፀሀፊ የአብስራ
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 553 |
| 10 | ስህተት ወይስ ምን?
ኤማ ከነቢል ጋር መጣም መግባባት ጀመረች
ብዙ ጊዜ ማውራት እና መገናኘት ጀመሩ
አንድ ቀን ሁለቱም አንድ ሰርግ ተጠርተው እንግዳ ሆነው ይሄዳሉ
ሁለቱም ዘንጠው አንድላይ ሰርግ ቤት ተገኙ
ሰርግ ቤቱ በቆንጆዎች ጢም ብሎ ሞልቷል
በዚ መሀል ነቢል ጨዋታውን ጀመረ
"ኤሚ!"
"ወይ" ኤማ ማንንም አቤት ብላ አታውቅም ስሟ ሲጠራ ወይ ማለትልምዷ ነው
"እስኪ ከዚ ሁሉ ቆንጆ አንድ ሚስት ለኔ መምረጪልኝ" አለ አይኗን በስስት እያየ
"እዛ ጥግ ላይ ቀይ ቀሚስ ያረገችው አታምርም በናትህ?እያት እስኪ ወይ ደሞ እዛ ጋ ያለችው ፀጉሯ እረጅሟ" እያለች ታስመርጠው ጀመር በዛን ሰአት እሷ ስለሱ ምንም አይነት ሀሳብ አልነበራትም
ኤማ መወደድ እንጂ መውደድን በጭራሽ አስባው አታውቅም
በወንዶች ስትወደድ ደስ ይላታል ወንዶችን ለመውደድ ግን ምንም ፍላጎት አልነበራትም
ልቧን ለማንም ለመክፈት ፍቃደኛ አደለችም
ነቢል የዛን ቀን በመለሰችለት መልስ ተገረመ
እሱ አስቦ የነበረው እሷ ትቀናለች ወይም ትናደዳለች ብሎ አስቦ ነበርእሷ ግን በተቃራኒው ረጅሟ፣አጭሯ፣ቀይ ቀሚስ ያረገችው እያለች መመለሷ አስገርሞታል
ነቢል እንዲው እንደተገረመ ቀናቶች አለፋ
አንድ ቀን ነቢል ልብሱን እያጠበ ኤማ ከፊቱ ተቀምጣ ታዋራዋለች 'ስማኝማ ነቢሎ፤ ባለፈው ሂሳብ አስተማሪያችን...ነቢል እየሰማት አልነበረም ከአይኑ ትይዩ በቲሸርቷ አንገት በኩል የሚታዩት ጡቶቿ ላይ አይኑ
አርፏል ኤማ ማውራቷን እንደቀጠለች ነው
እሱ ግን አሁንም አይኑን ካሳረፈበት መንቀል አልቻለም ድንገት ተቆጣ "ተነሺ'' ብሎ ጮኸ
ኤማ ደነገጠች "እህህህ ምነው? አለች
ከፊለፊቴ ተነሽ አለ አሁንም እየተቆጣ እህህ ለምን? ኤማ ግራ ገባት!
የማይሽ አስተያየት ትክክል ስላልሆነ አለና ውሃ ውስጥ ያለውን ልብስ እያወራጨ ማጠብ ጀመረ ኤማ ደረቅ እና እልኸኛ ስለነበረች "አልነሳም" ብላ ባለችበት ተቀመጠችቨ ነገሮች እንዲህ ባለ ሁኔታ ቀጠሉ እሷ ለሱ ምንም ስሜት ሳይኖራት እሱ ግን ለሷ መሸነፍ ጀመረ ነገር ግን ምንም ነገር ሳይነግራት በተግባር ለማሳየት መሞከር ጀመረ
ከለታት ባንዱ ቀን ኤማ ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ ሀይለኛ ዝናብ መዝነብ ጀመረ እሷም መሮጥ ጀመረች ድንገት ግን አንድ ሰው ከኋላዋ እጇን ይዞ አስቆማት ደንግጣ ስትዞር ነቢል ነው...
ይቀጥላል...
ፀሀፊ የአብስራ
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 623 |
| 11 | ስህተት ወይስ ምን?
ተዋወቋት ኤማ ትባላለች...
ኤማ ተወልዳ ያደገችው ቢሾፍቱ በምትባል አነስ ባለች ከተማ ውስጥ ነው፡፡ በወቅቱ ቢሾፍቱ ከተማ ለመባል ባትበቃም ከገጠርነት ወደ ከተማነት ለመለወጥ ብዙም ስላልፈጀባት።ቢሾፍቱ ከተማ ተባለች፡፡ ኤማ የምትኖረው ከ አያቷ ጋር ነው ከአያቱ ጋር ያደገ ልጅ ቀበጥ ነው ይባላል ኤማ ግን በተቃራኒው ነች። መቅበጥ ሚባልል ነገር ፈፅሞ
አልፈጠረባትም ብዙወን ግዜ ዝምታን ምትመርጥ ልጅ ናት፡፡ ደስ የሚለው ቅጥነቷ ከርዝመቷ እና ከቅላቷ ጋር ተዳምሮ ቆንጅናን አልብሷታል ትምህርቷን የተማረችው እዛው ለሰፈሯ ቅርብ የነበረው አንድ የመንግስት ት/ቤት ነው ኤማ ዝምተኛ እና ጨዋ ስለነበረች አስተማሪዎችም ሆነ ተማሪዎችም የሚወዷት ተማሪ ነበረች እስከ ሰባተኛ ክፍል እዛው ስትማር ቆየች ልክ ስምንተኛ ክፍል ስትገባ አድጋለች ብላ ስላሰበች አክስቷ ከራሷ ስራ ታሰራት ጀመር... የኤማ አክስት ቡና እና ሻይ እያፈላች ነበር የምትተዳደረው በዚህም ምክንያት ኤማ ከአክስቷ ጋር ስራ እያገዘች መቆየት ግድ ሆነባት...ኤማ ቡና ትቀዳለች ሻይ ትቀዳለች እቃ ታጥባለች አልፎ አልፎ ደሞ እቃ ትሰብራለች ኤማ ትምህርቷን እየተማረች ስራ መስራቷን ወዳዋለች ምክንያቱም አያቷ ተቆጪ እና ኮስታራ ስለነበሩ ለጨዋታም ሆነ ለምንም ነገር ከቤት መውጣት ለኤዎ ከባድ ነበር አሁን ግን ከ አክስቷ ጋር ስራ መስራቷ ከቤት የመውጫ አንድ ሰበብ ነበረና ኡማ በጣም ደስተኛ ነበረች ኤማ አንድ ጓደኛ አለቻት..አንድ ብቻ..ስሟ ሪሀና ይባላል ልክ እንደ እህቷ ምታያት አብሮ አደግ ጓደኛዋ ነች ሁሌ ወደ ት/ቤት ስትሄድም ሆነ ስትመጣ ከሷ ጋር ነው የትም ስትሄድ ከሷ ተለይታ አታውቅም ኤማ እና ሪሀና ሁሌ ሚያጨቃጭቃቸው አንድ ጉዳይ ነበር እሱም...የኤማ ፍቅር ከማንም አይዘኝም የሚለው ግትርነቷ ነው በዚህ ምክንያት ነበር ኤማ እስካሁን ድረስ የተዋወቀቻቸውን ወንዶች በቁም ነገር ለማየት ያቃታት ስምንተኛ ክፍል ስትማር ብዙ ወንዶች አበድኩልሽ ሞትኩልሽ ቢሏትም እሷ ግን አንዳቸውንም ዞር ብላም ለማየት ፍቃደኛ አልነበረችም ኤማ ዘጠነኛ ክፍል ገብታ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን መማር ጀመረች ኤማ እየተማረች እና እየሰራች መኖሯን ቀጥላለች ከትንሽ ግዜ በኋላ የሪሀና አያት ያርፋሉ... ሪሀና በአያቷ ሞት ቀላል ማይባል ሀዘን ውስጥ ገባች በዚህም ምክንያት ኤማም የሪሀና አያት ቤት ሪሀናን ለማፅናናት መቆየት ጀመረች...ከመቆየትም አልፋ ማደር ጀመረች ስራውንም ቢሆን ለትንሽ ጊዜ ማቆም እንዳለባት አስባ ከጓደኛዋ ጋር መቆየትን መረጠች ኤማ ለቅሶ ቤት ባደረች በሁለተኛው ቀን ነቢልን ለመጀመሪያ ግዜ ሲያለቅስ አየችው ነቢል የሪሀና የአክስት ልጅ ነው ነቢል ፀባዩ ኮስታራ እና ሱሰኛ ስለነበረ ከማንም ሰው ጋር መቀራረብ አይፈልግም በዚህም ምክንያት ኤማ ከነቢል ጋር ያላት ትውውቅ የአይን ብቻ እንጂ ቀርባ ለማውራት ድፍረቱ አልነበራትም ዛሬ ግን ሲያለቅስ ስታየው አሳዘናት ምንም እንኳን ቀርባ ባታውቀውም እያለቀሰ ስታየው ግን "ምናለ አቅፌ ባባበልኩት" ብላ ተመኘች ነቢል በጣም እያለቀሰ ነበር ኤማ እንዳሰበችው እንደተመኘችው እቅፍ አርጋ ለማባበል እና ለማፅናናት አልቻለችም ያቀን አለፈና በቀጣዩ ቀን ነቢልን ልታዋራው ፈለገች ነቢል ብዙውን ጊዜ ብቻውን ስለሚቀመጥ ኤማም ይሄን አጋጣሚ ተጠቅማ ልታዋራው ትሞክር ነበር ኤማ በተደጋጋቢ ከነቢል ጋር ማውራቷን ቀጠለች ከማንም ጋር ለመግባባት የማይፈልገው ነቢል ከ ኤማ ጋር መግባባት ጀመረ የኤማ እና የነቢል ትውውቅ እዚ ጋር ጀመረ
ይቀጥላል...
ፀሀፊ የአብስራ
jᵒⁱⁿ⇝ @Lyrics_profile | 718 |
| 12 | አትጠይቂኝ
"ያቡ መቼ ነው ምትነግረኝ" የ ሁል ጊዜ ጥያቄዋ
ምኑን? የ ሁል ጊዜ መልሴ
ፍቅር ላንተ የሚሰጠወውን ትርጉም
ስለተጣላን ለመታረቅ በተገናኘንበት አጋጣሚ ነው እንደዚ ያለቺኝ ገና ተመቻችታ እንኳን ሳትቀመጥ
በርግጥ በጣም ናፍቃኝ ነበር ግን ምን ያደርጋል አሁንም ይሄን ጥያቄዋን አላቆመችም ፍቅር ስለሚባል ነገር አትጠይቂኝ ብዬ ሺ ግዜ ነግሬያታለሁ እሷ ግን ከ ቀን ወደ ቀን እየባሰባት መጣች ጭራሽ ብላ ብላ የ ሁልጊዜ አጀንዳዋ አድርጋዋለች "እ ንገረኛ! አሁንም ዝም ልትለኝ ነው?" 'ምን አልሺኝ?" አልኩኝ ጥያቄውን እንዳልሰማ ሆቼ 'የፍቅር ትርጉሙ ላንተ ምንድነው? እየተቆጣች ደገመችው ኤጭ
"ፍቅርኮ በህንደኛ የተሰራ ረዘም ያለ ዘፈን እና ጭፈራ የበዛበት ታሪክ አደለም...ወይስ ትርጉም በ ስለሺ እያልኩ እንድተረጉምልሽ ነው ምትፈልጊው" አልኳት ኮስተር ብዬ በ ሞልቃቃ አፏ "'አትቀልድ በናትህ" አለችና ቆንጆ በሆነው ከንፈሯ አኮረፈችበት
ኸረ አኮረፍሽ፤ በደንብ አኩርፊ ስላኮረፍሽ ምንም ሚፈጠር ነገር የለም የፍቅርን ትርጉም አላውቀውም ስንቴ ነው የነገርኩሽ ስለ ፍቅር
"አ፡ትጠ.ይ.ቂ.ኝ"
መልሶችህ ሁሌ ይገርሙኛል.አሁን የመለስክልኝን ጨምሮ" ብላ ያኮረፈችበትን ከንፈር በትንሹ ፈገግ አለችበት "ገረመሽም አልገረመሽም ጉዳዬ አደለም ቆይ ለምንድነው ሁል ጊዜ ስለ ፍቅር ብቻ ምትጠይቂኝ? ከሱ ሌላ ምትጠይቁቂኝ ነገር የለም? ተቆጣኋት
"አለ አለ፤" አለች ለመጠየቅ እየጓጓች
"እሺ ምንድነው ጠይቂኝ!' አልኳት
"እእ....በናትህ ስለ በፊቷ ፍቅረኛህ ንገረኝ?
ጭራሽ..! እኔ ነኝ በገዛ እጄ ፊት እየሰጠኋት እንደዚ የቀበጠችው!
"አንቺ ወይ ጨዋታ ቀይሪ ወይ ደሞ ቻው በቃ ልሄድ ነው'" አልኩኝ ጠረጴዛ ላይ ያስቀመጥኩትን ስልኬን ወደ ኪሴ እየከተትኩ "እሺ እሺ በቃ አልጠይቅህም አትሂድ ነገር ግን ያቡ።..." አለች አይኗን ቁልጭ ቁልጭ እያረገች "ነገር ግን ምን?" አልኩኝ ሚቁለጨለጩት አይኖቿ ላይ አፍጥጩ
"ስላንተ ማወቅ እፈልጋለሁ"
"ውይ ለሱ ነው እንዴ፤ የአብስራ እባላለሁ እንተዋወቅ" አልኳት ቀኝ እጄን ለ ሰላምታ ዘርግቼላት "ቆይ አንተ አይገባህም? አለች በጣም ተቆጥታ ካፌ ውስጥ የነበሩት ሰዎች በሙሉ እኛን ማየት ጀመሩ እኔ ግን የገረመኝ፤ ለመጀመሪያ ግዜ እንደዚ ስትቆጣ ማየቴ ነው አቤ...ት ሴትነቷ፤ አሁን ደስ አለቺኝ እንደዚ እንደምትቆጣ አላውቅም ነበር ይሄን ያክል ስለኔ ማወቅ ለምን ፈለገች? ለምንድነው ስለ ፍቅር ያለኝን አመለካከት በዚ ልክ ለማወቅ ምትፈልገው? "እሺ መጀመሪያ ተረጋጊ" አልኳት እስካሁን ድረስ ካፌ ውስጥ ያሉ ሰዎች እኛን ማየት አላቆሙም እጄን ወደላይ ከፍ አድርጌ እያውለበለብኩ "ሰላም ነው አታስቡ" የሚል ምልክት ለሁሉም ማሳየት ጀመርኩ
"ለምንድነው ምረጋጋው!፤ ቆይ አላበዛኸውም እንዴ፤!" ቁጣዋ ከቅድሙ ባሰ
ምንም መልስ መስጠት ስላልፈለኩ ዝም ብዬ ቆየሁ
"ያቡ! ለመጨረሻ ጊዜ አንድ ጥያቄ ብቻ ልጠይቅህ!"
ኡፍፍፍ ተገላገልኩ፤ ለመጨረሻ ጊዜ ያለቺኝ የምሯን ከሆነ ለኔ ግልግል ነው!
ደስ እያለኝ "እሺ ለመጨረሻ ጊዜ ምን?" አልኳት
"እኔ ላንተ ምንህ ነኝ? ይሄን ብቻ መልስልኝ!
ማለት?
"አኔ ምንህ ነኝን ጥያቄውን ብቻ መልስልኝ ቦግ አለች
ደነገጥኩ!
ለዚ ጥያቄ አንድ መልስ ብቻ ነው ያለኝ
እኮ ምን ንገረኝ
መረጋጋት አልቻለችም 'ንገረኝ''
ን.ገ.ረ.ኝ......!
አ.ትጠ.ይ.ቂ.ኝ! የመጨረሻ መልሴ
ፀሀፊ የአብስራ
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 829 |
| 13 | አትጠይቂኝ! Part 5
"መታረቅ አለባቹ ያቡ" አለኝ ደና ሀሳብ ያመጣ ይመስል
"ደሞ አንተ ምን አገባህ ለዚ ነው ካፌ እንገናኝ ብለህ
የቀጠርከኝ" አልኩት ተናድጄ
"እንዴት አያገባኝም?" ሁለታቹም ጓደኞቼ ናቹ ኮ እንደዚ
ስትሆኑ ማየት ደሞ አልፈልግም"
"ታዲያ እንዴት ስንሆን ነው ማየት ምትፈልገው" አልኩት
ፈገግ እያልኩ
ፈገግታዬ አበሳጭቶት ነው መሰለኝ "ያቡ አትቀልድ እኔ
የምሬን ነው" አለኝ እየተቆጣ
"እኮ እሺ ንገረኛ እንዴት ስንሆን ነው ማየት ምትፈልገው?
እኔ እሷን አፍቅሬ ከሷ ጋር አብሬ ስሆን ነው ማየት
ምትፈልገው?" ጮህኩበት
"ቆይ እሷን ካንተ በላይ የሚያውቃት ሰው አለ? አንተንስ
ቢሆን ከሷ በላይ ስላንተ ሚያውቅ ሰው አለ?"
አሪፍ ጥያቄ ጠየቀኝ
በሁለት ሰዎች መካከል ያለ ከፍተኛ ትውውቅ ወደ ፍቅር
ሊቀየር ሚችልበት ምክንያት አለ ብዬ አላስብም
ምን ብዬ ልመልስለት?
ዝም ልበለው" ወይስ የራሴን ሀሳብ ልንገረው?
እንደውም መልሼ እኔም ጥያቄ ልጠይቀው"በእኔና በሷ መሀል ያለው ትውውቅ ለመፋቀር ብቁ ነው
ብለህ ታስባለህ?" ብዬ የሱን መልስ መጠበቅ ጀመርኩ
ትንሽ ቆየና "አው" የሚል አጠር ያለ መልስ ሰጠኝ
ከት ብዬ መሳቅ ጀመረኩ "ሀሀሀሀ....."
"ምን ያስቅሀል"
"እንዴት አያስቀኝምፇ በሁት ሰዎች መካከል ያለ ከፍተኛ
ትውውቅ መግባባትን እንጂ መፋቀርን ሊያመጣ
አይችልም! ፍቅር ሚመጣው ከመግባባት ሳይሆን ከ
ስሜት ነው። ፍቅር ሚመጣው ከመግባባት ቢሆንማ
እስካሁን እኔና አንተ እንፋቀር ነበር..."
ደነገጠ "ማለት..፤ ምን ማለት ፈልገህ ነው?!"
"ለማለት የፈለኩትማ እኔና አንተ እስከዛሬ በጓደኝነት
የቆየነው በመግባባት እንጂ በፍቅር አደለም ፍቅር ስሜት
ያስፈልገዋል አውቃለሁ በተመሳሳይ ፆታ ስሜት ሊኖር
እንደማይችል ነገር ግን አንተ ለኔ ጓደኛዬ ነህ እሷም ልክ
እንዳንተ ጓደኛዬ ናት ከዛ ያለፈ ነገር ከሷ ጋር እንዲኖረኝ
አልፈልግም.።..አየህ ፍቅር ያለ ስሜት ባዶ ነው መግባባት
ብቻውን ለመፋቀር ብቁ አደለም!"
"እሺ አሁን ገባኝ። ግን እንደ ትልቅ ሰው ቁጭ ብላቹ ይሄን
ጉዳይ መፍታት አለባቹ" አለኝ"በጣም ብዙ ጊዜ ልነግራት ሞክሪያለሁ እሷ ግን ለጥያቄዋ መልስ እንጂ ለመነጋገር ዝግጁ አደለችም ሁሌ ምትጠይቀኝ ጥያቄ "ፍቅር ላንተ ምንድነው"ብላ ትጠይቀኝና ስመልስላት ትበሳጫለች ወይም ደሞ ታኮርፋለች" በዚ መሀል ስልኩ ጠራ
ስልኩን ካነሳ በኋላ "አው እየጠበቅንሽ ነው ነይ ጊቢ
ወደውስጥ" ብሎ ስልኩን ዘጋው
“ማነው?!" አልኩት ደንግጩ
"እሷ ናት እየመጣች ነው ታወራላቹ" አለና እስካሁን በወሬ
ቀዝቅዞ የቆየውን ማኪያቶ ፉት አረገው
"ለማውራት ዝግጁ ከሆነች እኔ ፍቃደኛ ነኝ ግን እንደ
ሌላ ጊዜው ፍቅር ላንተ ምንድነው የሚል ዝባዝንኬዋን
ከጀመረች ይቅርታ አርግልኝ ተነስቼ እወጣለሁ" ብዬ
ነገርኩት
በእጁ የያዘውን የቀዘቀዘ ማኪያቶ እያስቀመጠ "ቆይ
ፍቅር ላንተ ምንድነው ብላ ከጠየቀችህ በኋላ ምን ብለህ
መልሰህላት ነው የምታኮርፍህ እና የምትናደድብህ"
"አ.ት.ጠ.ይ.ቂ.ኝ" ብቻ ነው ያልኳት
ፀሀፊ <"የአብስራ">
ከወደዳቹት❤
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 759 |
| 14 | አትጠይቂኝ ክፍል 4
እየናፈቀቺኝ ባልሆነ!! አአአይይይይ ሊሆን አይችልም
አንድ ወር ሙሉ ሳንገናኝ አሁን ትዝ ምትለኝ ለምንድነው?
ጓደኛዋ ጋር ልደውል? ወይስ ራሷ ጋ ደውዬ ላውራት፣
አላረገውም! አ.ላ.ረ.ገ.ው.ም.!
አላስቻለኝም ብዙም ሳልቆይ ደወልኩላት
ስልኩን ካነሳችው በኋላ ሄሎ በማለት ፋንታ እንደማታውቀኝ
ሆና
"አቤት" አለቺኝ
"አቤት...71 እኔን ነው አቤት ያልሺኝ!?" ተናደድኩ ለነገሩ
እኔ ነኝ ጥፋተኛ መደወል አልነበረብኝም...ስልኩን ዘጋሁት
ስልክ አንስታ አቤት ትለኛለች እንዴን ሰው አቤት ሚለው
ስሙ ሲጠራ ነው። ታዲያ እንዴት አቤት ትለኛለች?
ቆይ ምን እንድትለኝ ጠብቄ ነበር?..እኔንጃ;
ብቻ ግን አቤት ማለት አልነበረባትም
ስልኬ ጠራ...እሷ ናት የደወለችው
አነሳሁትና "አቤት!" አልኩኝ
ውይ እኔም ደገምኩት
"ማለቴ፤.ሄሎ ለማለት ፈልጌ ነው" አልኳት
ደስ በሚል እና በናፈቀኝ ድምዷ
"ደውለህ ነበር!" አለቺኝ
"ማ? እኔ?!"
"አው አንተ! ምነው አልደወልኩም ለማለት ነው?"
"እሺ አዎ ደውዬ ነበር እና ምን ይጠበስ?"
"እሺ ለምን ደወልክ?"
'ስላስቀየምኩሽ ይቅርታ ልጠይቅሽ እና ስለናፈቅሺኝ ነው
የደወልኩት"
ምንም ሳትመልስለኝ ዝም ብላ ቆየች
እኔ ማውራቴን ቀጠልኩ "የዛን ቀን ለምን ያንን ጥያቄ
እንደጠየቅሺኝ ስለማውቅ እና ያን ጥያቄ ከመለስኩ
በኋላ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ስለገባኝ ነው
የተበሳጨሁት,.ምናልባት ከ ጥያቄው በኋላ ለኔ ያለሽን
ስሜት ልትነግሪኝ ይሆናል ወይ ደሞ እኔ ላንቺ ያለኝን
ስሜት እንድነግርሽ ልትጠይቂኝ ይሆናል..ያ ደሞ ልክ
አይመጣም.።.ለኔ ፍቅር ማለት ምን ማለት እንደሆነ ነግሬሽ
ነበር አደል..በቃ ያልኩሽን እመፒኝ
አሁን የደወልኩት ይቅርታ ልጠይቅሽ ነበር ለምን ሌላ ነገር
እንዳወራ ታደርጊኛለሽ" ብዬ እስከዛሬ ሳሰላስል የነበረውን
ጭንቀቴን ከተነፈስኩላት በኋላ ስልኩን ዘጋሁት
ከዘጋሁት በኋላ ግን ውስጤ መጨነቅ ጀመረ
ምናልባት ዝም ብል ይሻል ነበር. ወይስ ያረኩት ነገር ልክ
ነው?
መደወሌ ስህተት ነው?" ለምን ደወልኩ?
እኔ ምን አውቄ!
ስልኬ ድጋሚ ጠራ
እራሷ ነች...
ላንሳው?.. አይ ባላነሳው ይሻላል!
ላንሳውና ድምዷን ልስማው..
አነሳሁት
"ሄሎ"
"ቆይ ግን ያቡ ልብ የለህም?" እንደተናደደች ድምዷ
ያስታውቃል
"የጀግና ልብ አለኝ፤ አንቺ ደሞ ምትፈልጊው የ አፍቃሪ
ልቤን ነው...አደል?" የአፍቃሪ ልብ ደሞ ሊኖረኝ አይችልም
እንዲኖረኝም አልፈልግም"
እኔ ልብን ማውቀው ካርታ ላይ ነው
አልማዝ፣ጦር፣አበባ እና ልብ፤
ምናልባት ፍላጎትሽ አልማዝ ከሆነ እንዴትም ብዬ አምጥቼ
ልሰጥሽ እችላለሁ።
ምናልባት ደሞ ፍላጎትሽ አበባ ከሆነ የፈለግሽውን አይነት
የፈለግሽውን ያክል አበባ ልሰጥሽ እችላለሁ።
እንደው ምናልባት ያንቺ ፍላጎት ጦር ከሆነም ያሻሽን ጦር
ከነ ጋሻው ልሰጥሽ እችላለሁ።
ነገር ግን ልቤን ልሰጥሽ አልችልም "አትጠይቂኝ"
"አ.ት.ጠ.ይ.ቂ.ኝ" | 675 |
| 15 | አትጠይቂኝ ክፍል 3
ከዛን ቀን ጀምሮ ለ ሶስት ሳምንት ያክል ሳንገናኝ ቆየን
እንደሌላ ጊዜው አልደወለችም ቴክስት አላረገችም ቤትም አልመጣችም ጭራሽ ምንም ሳላያት ሶስት ሳምንት አለፈኝ በትንሹም ቢሆን ስትናፍቀኝ ይታወቀኛል
ይሄን ያክል አስከፍቻታለሁ ማለት ነው?
ቆይ፤ ስለ ፍቅር አትጠይቂኝ ማለቴ ነው ያጣላን?"ብቻዬን መቀባጠር ጀመርኩ እንዴ ቆይ፤ ስለ ፍቅር ማላውቅ ከሆነስ! ማወቅ ማልፈልግ ከሆነስ! ስለ ፍቅር ማውራት ካልፈለኩስ፤ በግድ! ይሄን ያክል እኔን ስለ ፍቅር መጠየቋ ሳያንስ በዚው ምክንያት መጣላታችን እየገረመኝ መጣ
ፍቅር ላንተ ምንድነው ብላ ጠየቀቺኝ!
እኔ ደሞ ፍቅር እቃቃ እንደሆነ... የሁለት ሰዎች ነፃ
ጨዋታ እንደሆነ... ፍቅር ማለት ቁማር እንደሆነ እና በስተመጨረሻም "አላቅም ስለ ፍቅር አትጠይቂኝ" ብዬ
ተቆጣኋት እንጂ ምን አረኩ፤ቆይ ምን ብዬ እንድመልስላት ነው የጠየቀቺኝ?
"ፍቅር ማለት በሁለት ሰዎች መሀል ሊፈጠር የሚችል ትልቅ የመተሳሰብ የመፈላለግ እና የመዋደድ ስሜት ነው"
እንድላት ነው የፈለገችው?፡ወይስ "ፍቅር ሀያል ነው ፍቅር
አይሳሳትም ፍቅር ትልቅ ነው ፍቅር የልብ ቋንቋ ነው ፍቅር
እንደዚ ነው ፍቅር እንደዛ ነው" እያልኩ ብዙሀኑ በጋራ የተስማሙበትን የፍቅርን ምንነት እንድነግራት ፈልጋ ነው?
ማሰብ ማቆም አልቻልኩም..የምርም ናፍቃኛለች መሰለኝ፤
አይ አይ አልናፈቀቺኝም!
ናፍቆት!..ምንድነው ናፍቆት? ስለ አንድ ሰው ማሰብ ነው ናፍቆት? ወይስ የማናገኘውን ሰው በልባችን ይዘን መቆየት ነው ናፍቆት?
ናፍቆት ስቃይ ነው?.ወይስ ስለ አንድ ሰው ያለማቋረጥ
የማሰብ ጭንቀት?
"ያቡ ምነው ዛሬ ስራ የለም እንዴ" አለቺኝ..እማዬ ናት
እናቴ...የኔ እናት፤ሶፋ ላይ በጀርባዬ ተጋድሜ ኮርኒሱ ላይ አፍጥጩ በሀሳብ ከሄድኩት በጥያቄዋ አነቃቺኝ ተጣምሜ ከተጋደምኩበት ጠባብ ሶፋ ላይ እየተነሳሁ "እማ ፍቅር ምንድነው?7" የሚል ቃል ከአፌ ወጣ...ደንግጩ እማዬን አየኋት ይሄ ቃል ማውጣቴ አስደነገጠኝ...ሳላስበው ነበር እንደዚ ያልኩት እማዬ ሰምታ ይሆን ወይስ ይሄ ቃል ከአፌ አልወጣም?
እማዬ፦ "ዛሬ ደሞ ምን አይነት ጥያቄ አመጣህ" አለቺኝ ከኔ ፊትለፊት ያለው ሶፋ ላይ እየተቀመጠች እውነትም ይሄ ቃል ከአፌ ወቷል
"አይ ዝም ብዬ ነው" አልኩኝ ድንጋጤው እንዲለቀኝ
ሶፋውን ጭምድድ እያረኩ
"ምነው ፍቅር ያዘህ እንዴ" አለቺኝ ፈገግ እያለች
አይ እማ፤ ፍቅር ያዘህ ወይ አልሽኝ?" ማን አባቱ ስለሆነ
ነው እኔን ሚይዘኝ
"አይ ልጠይቅሽ ብዬ ነው" ብዬ ዝም አልኩኝ
እማዬም ልክ እንደኔው ስለ ፍቅር ማውራት አትወድም
ብዬ ነበር ማስበው...ግን እንደማስበው አደለም እማዬ ለጠየኳት ጥያቄ መልስ መወርወር ጀመረች
"ፍቅር ማለት....
አይ እማ.. ፍቅር ማለት እሷ እንደሆነች ሳታውቅ ስለ ፍቅር
እየነገረቺኝ ነው። ሁሉንም ባልሰማትም መጨረሻ ላይ
ያለችውን ግን በደንብ ነው የሰማኋት
"ፍቅር ከመዋደድ ያለፈ ስሜት ነው ፍቅርን ለማስረዳት ቃል ብቻ በቂ አደለም ፍቅር ይሄ ነው ተብሎ ሊገለፅ የማይችል ትልቅ ስሜት ነው" አለቺኝ
እማ ስለ ነገሮች የምታስብበት መንገድ ሁሌም ልዩ ነው ሁሌም ትገርመኛለች,.በርግጥ ራሴ ነኝ ማውራት ስለማልፈልገው ነገር የጠየኳት ነገር ግን መልሷ ልዩ
ሆነብኝ ምንም እንኳን በመልሷ ብደሰትም ከዚ በላይ ግን ስለ ፍቅር እንድታብራራልኝ አልፈቀድኩላትም
"በቃ ልወጣ ነው ምሄድበት ቦታ አለ" አልኩኝ
ከተቀመጥኩበት ብድግ እያልኩ
"ጥያቄ ጠይቆ መሸሽ ደሞ ከየት ያመጣኸው ባህሪ ነው" አለቺኝ በቁጣ ድምፅ
ምናልባት ጥያቄው ስለ ፍቅር ከሆነ መሸሽ ብቻ ሳይሆን ምሽግ መፈለግም ወሳኝ ነገር ነው" አልኩት ለራሴ 'ስለምቸኩል ነው እማ...ቡሀላ በጊዜ መጣለሁ" አለኩና ከቤት ወጣሁ
ይቀጥላል...
ፀሀፊ <"የአብስራ">
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 651 |
| 16 | አትጠይቂኝ ክፍል 3
ከዛን ቀን ጀምሮ ለ ሶስት ሳምንት ያክል ሳንገናኝ ቆየን
እንደሌላ ጊዜው አልደወለችም ቴክስት አላረገችም ቤትም አልመጣችም ጭራሽ ምንም ሳላያት ሶስት ሳምንት አለፈኝ በትንሹም ቢሆን ስትናፍቀኝ ይታወቀኛል
ይሄን ያክል አስከፍቻታለሁ ማለት ነው?
ቆይ፤ ስለ ፍቅር አትጠይቂኝ ማለቴ ነው ያጣላን?"ብቻዬን መቀባጠር ጀመርኩ እንዴ ቆይ፤ ስለ ፍቅር ማላውቅ ከሆነስ! ማወቅ ማልፈልግ ከሆነስ! ስለ ፍቅር ማውራት ካልፈለኩስ፤ በግድ! ይሄን ያክል እኔን ስለ ፍቅር መጠየቋ ሳያንስ በዚው ምክንያት መጣላታችን እየገረመኝ መጣ
ፍቅር ላንተ ምንድነው ብላ ጠየቀቺኝ!
እኔ ደሞ ፍቅር እቃቃ እንደሆነ... የሁለት ሰዎች ነፃ
ጨዋታ እንደሆነ... ፍቅር ማለት ቁማር እንደሆነ እና በስተመጨረሻም "አላቅም ስለ ፍቅር አትጠይቂኝ" ብዬ
ተቆጣኋት እንጂ ምን አረኩ፤ቆይ ምን ብዬ እንድመልስላት ነው የጠየቀቺኝ?
"ፍቅር ማለት በሁለት ሰዎች መሀል ሊፈጠር የሚችል ትልቅ የመተሳሰብ የመፈላለግ እና የመዋደድ ስሜት ነው"
እንድላት ነው የፈለገችው?፡ወይስ "ፍቅር ሀያል ነው ፍቅር
አይሳሳትም ፍቅር ትልቅ ነው ፍቅር የልብ ቋንቋ ነው ፍቅር
እንደዚ ነው ፍቅር እንደዛ ነው" እያልኩ ብዙሀኑ በጋራ የተስማሙበትን የፍቅርን ምንነት እንድነግራት ፈልጋ ነው?
ማሰብ ማቆም አልቻልኩም..የምርም ናፍቃኛለች መሰለኝ፤
አይ አይ አልናፈቀቺኝም!
ናፍቆት!..ምንድነው ናፍቆት? ስለ አንድ ሰው ማሰብ ነው ናፍቆት? ወይስ የማናገኘውን ሰው በልባችን ይዘን መቆየት ነው ናፍቆት?
ናፍቆት ስቃይ ነው?.ወይስ ስለ አንድ ሰው ያለማቋረጥ
የማሰብ ጭንቀት?
"ያቡ ምነው ዛሬ ስራ የለም እንዴ" አለቺኝ..እማዬ ናት
እናቴ...የኔ እናት፤ሶፋ ላይ በጀርባዬ ተጋድሜ ኮርኒሱ ላይ አፍጥጩ በሀሳብ ከሄድኩት በጥያቄዋ አነቃቺኝ ተጣምሜ ከተጋደምኩበት ጠባብ ሶፋ ላይ እየተነሳሁ "እማ ፍቅር ምንድነው?7" የሚል ቃል ከአፌ ወጣ...ደንግጩ እማዬን አየኋት ይሄ ቃል ማውጣቴ አስደነገጠኝ...ሳላስበው ነበር እንደዚ ያልኩት እማዬ ሰምታ ይሆን ወይስ ይሄ ቃል ከአፌ አልወጣም?
እማዬ፦ "ዛሬ ደሞ ምን አይነት ጥያቄ አመጣህ" አለቺኝ ከኔ ፊትለፊት ያለው ሶፋ ላይ እየተቀመጠች እውነትም ይሄ ቃል ከአፌ ወቷል
"አይ ዝም ብዬ ነው" አልኩኝ ድንጋጤው እንዲለቀኝ
ሶፋውን ጭምድድ እያረኩ
"ምነው ፍቅር ያዘህ እንዴ" አለቺኝ ፈገግ እያለች
አይ እማ፤ ፍቅር ያዘህ ወይ አልሽኝ?" ማን አባቱ ስለሆነ
ነው እኔን ሚይዘኝ
"አይ ልጠይቅሽ ብዬ ነው" ብዬ ዝም አልኩኝ
እማዬም ልክ እንደኔው ስለ ፍቅር ማውራት አትወድም
ብዬ ነበር ማስበው...ግን እንደማስበው አደለም እማዬ ለጠየኳት ጥያቄ መልስ መወርወር ጀመረች
"ፍቅር ማለት....
አይ እማ.. ፍቅር ማለት እሷ እንደሆነች ሳታውቅ ስለ ፍቅር
እየነገረቺኝ ነው። ሁሉንም ባልሰማትም መጨረሻ ላይ
ያለችውን ግን በደንብ ነው የሰማኋት
"ፍቅር ከመዋደድ ያለፈ ስሜት ነው ፍቅርን ለማስረዳት ቃል ብቻ በቂ አደለም ፍቅር ይሄ ነው ተብሎ ሊገለፅ የማይችል ትልቅ ስሜት ነው" አለቺኝ
እማ ስለ ነገሮች የምታስብበት መንገድ ሁሌም ልዩ ነው ሁሌም ትገርመኛለች,.በርግጥ ራሴ ነኝ ማውራት ስለማልፈልገው ነገር የጠየኳት ነገር ግን መልሷ ልዩ
ሆነብኝ ምንም እንኳን በመልሷ ብደሰትም ከዚ በላይ ግን ስለ ፍቅር እንድታብራራልኝ አልፈቀድኩላትም
"በቃ ልወጣ ነው ምሄድበት ቦታ አለ" አልኩኝ
ከተቀመጥኩበት ብድግ እያልኩ
"ጥያቄ ጠይቆ መሸሽ ደሞ ከየት ያመጣኸው ባህሪ ነው" አለቺኝ በቁጣ ድምፅ
ምናልባት ጥያቄው ስለ ፍቅር ከሆነ መሸሽ ብቻ ሳይሆን ምሽግ መፈለግም ወሳኝ ነገር ነው" አልኩት ለራሴ 'ስለምቸኩል ነው እማ...ቡሀላ በጊዜ መጣለሁ" አለኩና ከቤት ወጣሁ
ይቀጥላል...
ፀሀፊ <"የአብስራ">
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 1 |
| 17 | ገና በጠዋቱ የቤታችን በር ተንኳኳ
እኔም "ማነው?" እያልኩ እየጮህኩ ለመክፈት ወደ በሩ ሄድኩ...ያው እኛ ሀገር በር ከተንኳኳ “ማነው" ማለታችን ማይቀር ነገር ነው። የሚያንኳኳው ሰው ደሞ "እኔ ነኝ" ይላል። ማን እንደሆነ እንኳን ሳናውቅ "እኔ ነኝ" ስላለ ብቻ ሄደን እንከፍተዋለን...
አሁን ግን “ማነው ብዬ ስጮህ"
“እኔ ነኝ" የሚል ድምፅ አልተመለሰልኝም
የበለጠ ድምፄን ጨምሬ "ማነው?'" አልኩ
እኔ ነኝ በማለት ፋንታ በሩን የበለጠ መንኳኳት ጀመረ አማራጭ ስላልነበረኝ በሩን ከፈትኩት
ገና ከመክፈቴ
አንተ፤ ትላንት ምን ሆነህ ነው እንደዛ ተበሳጭተህ ተቆጥተኸኝ ጥለኸኝ የሄድከው" ብላ መጮህ ጀመረች
ኤጭ! ብላ ብላ ደሞ ቤት ድረስ መምጣት ጀመረች
"አንቺ ያምሻል እንዴ በዚ ጠዋት ለመጨቃጨቅ ነው ቤት ድረስ የመጣሽው?" ብዬ ለመቆጣት ሞከርኩ
እሷ ግን ጭራሽ ባሰባት "ጥያቄዬን መልስልኝ ትላንት ለምን ትተኸኝ ወጣህ?"
"ማይሆን ጥያቄ ስለጠየቅሺኝ!"
"ምኑ ነው ማይሆን ጥያቄ?፣ ፍቅር ላንተ ምንድነው ብዬ መጠየቄ ነው ማይሆን ጥያቄን?!"
ኤጭ ጀመራት ደሞ!...አሁንም ነገሩን እንደ አዲስ ልትጀምረው ነው
"እሺ አሁን ለዚ ነው የመጣሽው?!!" ብዬ ወሬውን ለማስቀየር ሞከርኩ
እሷ ግን የበለጠ እየተናደደች መጣች
ፊቷን አኮሳትራ "ቆይ አንተ ለምንድነው ሁሌ ስለ ፍቅር ስጠይቅህ ምትቆጣኝ ለምንድነው ስለ ፍቅር ሲነሳ ሌላ ሰው ምትሆንብኝ"
ጥያቄዋ አልገረመኝም ምክንያቱም ልክ ናት ስለ ፍቅር ማውራት አልወድም...ማንም ሰው ስለ ፍቅር ቢጠይቀኝ መልሴ "አላውቅም" ነው...
አላውቅማ፤ አዎ አላውቅም!
አውቀው የተፋቀሩ መስሏቸው ሳያቁ ሚለያዩ በበዙበት አለም ስለ ፍቅር አውቃለው ብዬ ለመናገር ከምሞክር
አላውቅም ብዬ ዝም ብል ይሻለኛል.አው አላውቅም!
መታወቅ ከሌለባቸው ነገሮች ውስጥ "ፍቅር" አንዱ ነው...አለማወቅ እንዴት ደስ ይላል። ፍቅርም ለሚያውቀው ሳይሆን ለሚያታልለው ነው ሚያደላው
"ከዚ በኋላ ፍቅር ላንተ ምንድነው። ፍቅር ላንተ ምን እንደሆነ ንገረኝ። የፍቅር ትርጉሙ ምንድነው! ፍቅር
ፍቅር ፍቅር እያልሽ አትጠይቂኝ በቃ! ፍቅር ምን እንደሆነ አላውቅም ማወቅም አልፈልግም ስለ ፍቅር ማወቅ ከፈለግሽ ብዙ መፅሐፍ አሉ እነሱ ላይ ደስ ያለሽን ውሸት መርጠሽ ማንበብ ትችያለሽ!"
ይሄ የመጨረሻ መልሴ ነው ብዬ ስላሰብኩ ዝም ብዬ አይኗን ማየት ጀመርኩ
አይኗ ላይ እንባ ይታየኛል ገና ያልወረደ እንባ ገና ተጠራቅሞ ያልሞላ እንባ ገና ከሩቅ የሚመጣ የሚመስል እንባ አይኗ ላይ አየሁ
"ምን ሆንሽ" አልኳት ደንግጩ
እንባ ያነቀው ድምዷን እየታገለች "ያቡ ቆይ ምን ሆነሀል? ይሄን ያክል ስለ ፍቅር ያለህ አመለካከት ለምን እንደተቀየረ አልገባኝም..የሆንከው ነገር አለ7" ብላ ሌላ ጥያቄ ጨመረችብኝ
እኔም እንባዋን ካየሁ በኋላ አሳዘነቺኝ "እሺ በቃ አትጠይቂኛ...፤ መመለስ ማልፈልገውን ነገር ለምን
ትጠይቂኛለሽ.." ብዬ በድጋሚ ዝም አልኩ
እስካሁን አይኗ ላይ ተጠራቅሞ ለመውረድ ሲታገል የነበረው እንባዋ ወረደ
ፀሀፊ <"የአብስራ">
ከወደዳቹት❤ | 647 |
| 18 | ገና ከመንጋቱ ስልኬ እየጮኸ ከእንቅፌ ቀሰቀሰኝ ስልክን ካለበት አንስቼ አየሁት የማላውቀው ቁጥር ነው። ማነው እያልኩ ግራ እየተጋባው አንስቼ ጆሮዬ ላይ አደረኩት ሄሎ የሚል ቁጣ ያለበት የትልቅ ሰው ድምፅ ሰማው፦ሄሎ አቤት አልኩ ከተኛሁበት ለመነሳት እየሞከርኩ ፦ትሰማለህ ከዛሬ በኋላ ልጄ አጠገብ እንዳትደርስ አይ ምትል ከሆነ ...ማን ልበል ስልክ ተሳስተዋል መሰለኝ አባቴ ተሳስተዋል ብዬ ስልኩን ለመዝጋት ስንደረደር ፦አባቴ አትበለኝ፤ እራስህ ነህ በጭራሽ አልተሳሳትኩም ነገርኩህ ከልጄ ጋር እንድትሆን አልፈቅድልህም ምንድነው እናንተ ገና ልጆች አይደላችሁም እንዴ እያሉ በጣም ብ...ዙ ፃ ነገር ካወሩ በኋላ አርፈህ ተቀመጥ ኋላ ችግር ውስጥ እንዳንገባ ብለው ዛቱብኝ ወዲያው ስልኩን ዘግቼ ማሰብ ጀመርኩ የቃልኪዳን አባት ናቸው ወይስ የ ፅዮን ለካ ፅዮን አባቷ ከሞቱ 2 ዓመት ሆናቸው ምፅ ምስኪን በቃ ወይ የሂክማ ወይም ደሞ የትርሲት ነው ሚሆኑት ከሂክማ ጋር ደግሞ ለዚ ሚያደርስ ቅርበት የለንም እና ቆይ የማን አባት ናቸው? የበፀሎት አባት ድምፅፃቸው እንደዚ ነው እንዴ፣ ወይ ማህሌት ጋር ደውዬ የአባትሽን ስለክ ቁጥር ንገሪኝ ልበላት? ወይኔ ዛሬ.. ድጋሚ ሰውየው ጋር ለመደወል ተዘጋጀው አንዴ በረጅሙ ከተነፈስኩ በኋላ ስልኬን አንስቼ ደወልኩ አሁንም ያ የቁጣ ድምፅ አልሰከነም "ሀሎ" አሉ ጠንከር ብለው ፦ሄሎ ጋሼ አሁን አውርተወኝ ነበር..አልኩኝ ረጋ በዬ እየተቆጡ፦ሰምተኸኛል አደል የተግባባን መሰለኝ.. ፦አው አው ተግባብተናል ጋሼ ግን ኮ....ብዬ ዝም አልኩ ፦ግን ምን. አሁን ድምፃቸው ጣራ ነካ ፦እኔም ደፈር አልኩና...ግን እኮ እርሶ ያሉኝ ከልጄ እራቅ ነው እንጂ ከየትኛዋ ልጆት እንደሆነ አልነገሩኝም..ስልኩን ጆሮዬ ላይ ባለ በሌለ ሀይላቸው ጥርቅም አረጉት...ከዛን ቀን ቡሀላ ነበር ሴት ልጅ ስተዋወቅ ቀድሜ የአባታቸውን ቁጥር መቀበል የጀመርኩት
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 804 |
| 19 | አትጠይቂኝ!
"ስማኝማ ያቡ?" ብላ ጠራቺኝ ገና የተቀጣጠርንበት ካፌ ገብተን እፎይይ... ብዬ ከመቀመጤ
"አቤት..." አልኳት እፎይይይ የሚለውን ቃል ወደ አቤት ቀይሬ
"አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ" አለች ቀልጠፍ ብላ
ደሞ የምን ጥያቄ አመጣች ለራሴ ረሀብ ሊደፋኝ ነው...ምሳ ልንበላ ነው የመጣነው...በዚ ሰአት ምን እንብላ ምን እንዘዝ ይባላል እንጂ "ጥያቄ ልጠይቅህ"
ይባላል?..አይባልም!
ምናልባት "ምን እንዘዝ" ብላ ልትጠይቀኝ ነው ብዬ አሰብኩና "እ ምን ይሁን ጥብስ ነገር?" አልኳት ለመብላት የተዘጋጀውን እጄን ወደዚ ወደዛ እያደረኩ
"እህህህህ እኔ መች ምግቡን አልኩ"
"ታድያ ምንድነው እሺ?
"ተወው በቃ" አለቺኝና የሚያምረውን ለምቦጯን ዘርግታ ማኩረፏን አሳየቺኝ
"እሺ ምንድነው ጠይቂኝ አልኩሽ አደል!" አሁን ቆጣ አልኩኝ..እውነትም እርቦኛል. ለራሴም ገረመኝ
"እሺ ፍቅር ላንተ ምንድነው" አለችና አይኔን ትኩር ብላማየት ጀመረች
ውይይይ እንደዚ ያኮረፈችው እቺን ጥያቄ ለመጠየቅ ነው እንዴ!
ፍቅር ማለት ሁለት ሰዎች በልባቸው የሚጫወቱት እቃቃ
እንደሆነ ሳታውቅ ቀርታ ነው?
ወይስ ከኔ አንደበት መስማት ፈልጋ?
ፍቅር ማለት የሁለት ጅሎች ነፃ ጨዋታ እንደሆነ አውቃለሁ...አዎ ጅሎች...እነዚ ጅል!
አንዱ አንዱን አምኖ በነፃ ሊጫወት የሚችለው ጨዋታ
ቢኖር ፍቅር ነው...
ፍቅር ማለት ቁማር ነው..ቁማርተኛው እበላለው ይደርሰኛል ብሎ ተስፋ እንደሚያደርገው አፍቃሪም ልክ እንደዛው የኔ ይሆናል እፈልገዋለሁ (አገባዋለሁ) ብሎ
ተስፋ ያደርጋል
ቁማርተኛው እንደዚው ተስፋ ያደርጋል እንጂ ሊደርሰውም ላይደርሰውም እንደሚችል ያውቃል አፍቃሪውም ፍቅሩን ሊያጣም ሊያገኝም እንደሚችለው ሁሉ ማለት ነው።
"ያቡ መልስልኝ እጂ" ብላ ከገባሁበት ሀሳብ ልታወጣኝ እየሞከረች ነበር
እኔግን አሁንም ብቻዬን ማሰላሰልን መርጫለሁ
ካልጠፋ ጥያቄ እንዴት "ፍቅር ላንተ ምንድነው" ተብሎ
ይጠየቃል ተናገርኩ ኮ በቃ! ፍቅር ማለት አኩኩሉ ነውውው
አንደኛው አይኑን ጨፍኖ በፍቅር "አኩኩሉ" እያለ "ነጋ" የሚለውን የሌላኛውን ድምፅ በጉጉት ይጠብቃል ሌላኛው ደሞ "አልነጋም" እያለ የማይነጋ ጨለማ ውስጥ እስከሚነጋ እየጠበቀ ለዘላለም እዛው ጨለማ ውስጥ ይቀራል...
አታፍርም እንዴ ደሞ "ፍቅር ላንተ ምንድነው" ብላ ደረቷን ነፍታ ስትጠይቅ
ፍቅር ጨካኝ ነው። ፍቅር ክፉ ነው። ፍቅር ርህራሄ የለውም።ፍቅር....
'ያቡ ምን ሆንክ አትመልስልኝም እንዴ" አሁን ድምዷን ከፍ አርጋ እየተቆጣች ከሀሳቤ አወጣቺኝ
ምን እንደነካኝ አላውቅም እኔም ከገባሁበት ሀሳብ ስወጣ
በጣም ተናደድኩ
"ተይኝ በቃ አትጠይቂኝ!!" ብዬ እየጮህኩ ከካፌው ትቻት ወጣሁ
ይቀጥላል...
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 749 |
| 20 | አትጠይቂኝ!
"ስማኝማ ያቡ?" ብላ ጠራቺኝ ገና የተቀጣጠርንበት ካፌ ገብተን እፎይይ... ብዬ ከመቀመጤ
"አቤት..." አልኳት እፎይይይ የሚለውን ቃል ወደ አቤት ቀይሬ
"አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ" አለች ቀልጠፍ ብላ
ደሞ የምን ጥያቄ አመጣች ለራሴ ረሀብ ሊደፋኝ ነው...ምሳ ልንበላ ነው የመጣነው...በዚ ሰአት ምን እንብላ ምን እንዘዝ ይባላል እንጂ "ጥያቄ ልጠይቅህ"
ይባላል?..አይባልም!
ምናልባት "ምን እንዘዝ" ብላ ልትጠይቀኝ ነው ብዬ አሰብኩና "እ ምን ይሁን ጥብስ ነገር?" አልኳት ለመብላት የተዘጋጀውን እጄን ወደዚ ወደዛ እያደረኩ
"እህህህህ እኔ መች ምግቡን አልኩ"
"ታድያ ምንድነው እሺ?
"ተወው በቃ" አለቺኝና የሚያምረውን ለምቦጯን ዘርግታ ማኩረፏን አሳየቺኝ
"እሺ ምንድነው ጠይቂኝ አልኩሽ አደል!" አሁን ቆጣ አልኩኝ..እውነትም እርቦኛል. ለራሴም ገረመኝ
"እሺ ፍቅር ላንተ ምንድነው" አለችና አይኔን ትኩር ብላማየት ጀመረች
ውይይይ እንደዚ ያኮረፈችው እቺን ጥያቄ ለመጠየቅ ነው እንዴ!
ፍቅር ማለት ሁለት ሰዎች በልባቸው የሚጫወቱት እቃቃ
እንደሆነ ሳታውቅ ቀርታ ነው?
ወይስ ከኔ አንደበት መስማት ፈልጋ?
ፍቅር ማለት የሁለት ጅሎች ነፃ ጨዋታ እንደሆነ አውቃለሁ...አዎ ጅሎች...እነዚ ጅል!
አንዱ አንዱን አምኖ በነፃ ሊጫወት የሚችለው ጨዋታ
ቢኖር ፍቅር ነው...
ፍቅር ማለት ቁማር ነው..ቁማርተኛው እበላለው ይደርሰኛል ብሎ ተስፋ እንደሚያደርገው አፍቃሪም ልክ እንደዛው የኔ ይሆናል እፈልገዋለሁ (አገባዋለሁ) ብሎ
ተስፋ ያደርጋል
ቁማርተኛው እንደዚው ተስፋ ያደርጋል እንጂ ሊደርሰውም ላይደርሰውም እንደሚችል ያውቃል አፍቃሪውም ፍቅሩን ሊያጣም ሊያገኝም እንደሚችለው ሁሉ ማለት ነው።
"ያቡ መልስልኝ እጂ" ብላ ከገባሁበት ሀሳብ ልታወጣኝ እየሞከረች ነበር
እኔግን አሁንም ብቻዬን ማሰላሰልን መርጫለሁ
ካልጠፋ ጥያቄ እንዴት "ፍቅር ላንተ ምንድነው" ተብሎ
ይጠየቃል ተናገርኩ ኮ በቃ! ፍቅር ማለት አኩኩሉ ነውውው
አንደኛው አይኑን ጨፍኖ በፍቅር "አኩኩሉ" እያለ "ነጋ" የሚለውን የሌላኛውን ድምፅ በጉጉት ይጠብቃል ሌላኛው ደሞ "አልነጋም" እያለ የማይነጋ ጨለማ ውስጥ እስከሚነጋ እየጠበቀ ለዘላለም እዛው ጨለማ ውስጥ ይቀራል...
አታፍርም እንዴ ደሞ "ፍቅር ላንተ ምንድነው" ብላ ደረቷን ነፍታ ስትጠይቅ
ፍቅር ጨካኝ ነው። ፍቅር ክፉ ነው። ፍቅር ርህራሄ የለውም።ፍቅር....
'ያቡ ምን ሆንክ አትመልስልኝም እንዴ" አሁን ድምዷን ከፍ አርጋ እየተቆጣች ከሀሳቤ አወጣቺኝ
ምን እንደነካኝ አላውቅም እኔም ከገባሁበት ሀሳብ ስወጣ
በጣም ተናደድኩ
"ተይኝ በቃ አትጠይቂኝ!!" ብዬ እየጮህኩ ከካፌው ትቻት ወጣሁ
ይቀጥላል...
jᵒⁱⁿ⇝ @Habesha_Edit | 2 |
