cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የዝዋይ ሐመረ ኖህ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም ሰንበት ት/ት ቤት

የዝዋይ ሐመረ ኖህ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም ሰንበት ት/ት ቤት ቻናል ተከታታዮች ይህ ቻናል ለተለያዩ ትምህርቶች የተዘጋጀ ሲሆን 1. ስለ ዕምነታችን 2. የቤተ ክርስቲያን ስነ-ምግባሮችን የምናውቅበት 3. ስለ ህይወታችን በምን መንገድ ማሳለፍ እንዳለብን በቅዱሳን አባቶቻችን ትምህርት በምክር መልክ እንማማራለን 4. የተለያዩ መዝሙራት ከዚህ ቻናል ማግኘት ይችላሉ። ጓደኞትን በማስገባት ይተባበሩን

Show more
Advertising posts
292
Subscribers
-124 hours
-17 days
+1130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ስለ ግብረሰዶማዊነት እና ተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ ቋሚ ሲኖዶስ ምን አሉ ? ዛሬ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻና ግብረ ሰዶማዊነትን አስመልከቶ እየተደረጉ ነው ስላላቸው ሁለገብ ተጽእኖዎችንና መመሪያ የማስለወጥ ማግባባቶችን በተመለከተ መግለጫ ሰጥቷል። ቋሚ ሲኖዶስ ምን አለ? - ግብረ ሰዶማዊነት በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተገለጸው ለአንድ ሀገርና ሕዝብ ከነጎረቤቶቹ መጥፋት ምክንያት የሆነ ተግባር ነው። የሰዶምና ገሞራ በመቅሰፍተ እሳት መቃጠል ከእነርሱ መቀጣትም  አልፎ ላለውና ለመጪው ትውልድ አስተማሪ የሆነ ምልክት እንዲሆን ነው። - ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ግብረ ሰዶማዊነትን የምትቃወመው ተፈጥሮዋዊ ስላልሆነ ብቻ ሳይሆን በብሉይ  ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን ትምህርት በእግዚአብሔር ዘንድ የረከሰ፣ ተቀባይነት የሌለው፣ ኃጢአት በመሆኑ ነው፡፡ - ቅድስት ቤተክርስቲያን ጾታዊ ግንኙነት ወይም የተቀደሰ ጋብቻ በተቃራኒ ጾታዎች ብቻ የሚፈጾም እንዲሆን ታስተምራለች። - ግብረ ሰዶማዊነት የሰውን ልጅ ተፈጥሯዊ ማንነት የሚንድ፣ መሠረተ እምነትንና ቀኖናን የሚሽር፣ ማኅበራዊ ዕሴት የሚያጠፋ፣ ከሥነ ምግባር መገለጫዎች በአሉታዊ ገጽ የቆመ፣ ሕሊናን የሚያውክ ለትውልድ ጥፋት፣ ለሀገር መውደም ምክንያት የሆነ አጸያፊ ተግባር ነው፡፡ - ቅድስት ቤተክርስቲያን ይህን ተግባር የሚፈጽሙ ሰዎች ወደ ንሥሓና ድኅነት እንዲመጡ፣ ከሥጋና ከመንፈስ ስብራት እንዲፈወሱ ዘወትር ጥሪ ታደርጋለች እንጅ ማንም ሰው የኃጢአቱ ወይም የርኩሰቱ ተባባሪ እንዲሆን አትፈቅድም። - በሀገራችን የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ በሕግ የተከለከለ ነው። - ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይህን ተግባር (የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ) በግልጥ በሕገ መንግሥታቸውና በልዩ ልዩ ማኅበራዊ ድንጋጌዎቻቸው እንደ ጥሩ ነገር እንደ ፍትሐዊነትና አካታችነት በመቁጠር በይፋ የደነገጉ የምዕራቡ ዓለም ሀገራት መኖራቸው ግልጽ ነው። እነዚሁ ሀገራት ያላቸውን የፖለቲካና የኢኮኖሚ አቅም መከታ በማድረግ በእምነታቸው፣ በባሕላቸው በማኀበራዊ መገለጫቸው ይህን አጸያፊ ድርጊት ፈጽመው በማይቀበሉ የአፍሪካና የምሥራቁ ዓለም ሀገራት ላይ ቢቻል በማግባባት፣ ካልሆነም የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጫና በማሳደር እንዲቀበሉ የጥፋት ልማዳቸውን እንዲጋሩ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉትን ድብቅና ግልጽ እንቅስቃሴዎችን እንቃወማለን። - ይህ ግብረ ርኩሰት በዘመናችን ተቀባይነት እንዲኖረው፣ የሚደረጉ ሁለገብ ማግባባቶች ፣ተጽዕኖዎችና ተያያዥነት ያላቸው ስምምነቶች በሀገራችን መንግሥት ተቀባይነት አግኝተው እንዳይፈጸሙ በጥብቅ እናሳስባለን። - ከመገናኛ ብዙኃንና ከሌሎችም የመረጃ ምንጮች ለማወቅ እንደተቻለው ግብረ ሰዶማዊነትንና ተያያዥነት ያላቸውን ተግባራት የንግድ፣ የፖለቲካ ፣ የኢኮኖሚ ፣የፍትሕና የሰብዓዊነት ግንኙነቶች አካል በማድረግ በቃላትና በዓረፍተ ነገሮች ውስጥ አስርጎ በማስገባት አሣሪ ስምምነቶች እንዲፈጸሙ ለማድረግ ያለው ሃደት በአፋጣኝ እንዲፈተሽ። የሀገራችን መንግሥት ብሎም የአፍሪካ መንግሥታት የአህጉራችንን ሃይማኖታዊ ማኅበራዊና ሥነ ልቦናዊ ዕሴቶች አስጠብቀው እንዲቀጥሉ ቋሚ ጥብቅ ጥሪ እናቀርባለን። (ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል) @tikvahethiopia
Show all...
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ አገር እንዳይገቡ ተከለከሉ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት ጨርሰው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ እንዳይገቡ መከልከላቸው ተሰምቷል። ብፁዕነታቸው ከሳምንታት በፊት በቋሚ ሲኖዶስ እውቅና ወደ ሀገረ ስብከታቸው በመሄድ የአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ዓመታዊ በዓል፣ የከተራና የጥምቀት በዓላትን ከመንፈስ ልጆቻቸው ጋር ያከበሩ ሲሆን ለአዳጊ ሕጻናትም ማዕረገ ዲቁና መስጠታቸው ይታወቃል። ብፁዕነታቸው በአሁኑ ሰዓት ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያው እንደሚገኙ ታውቋል።
Show all...
👍 1
መርቆሬዎስ ======== መርቆሬዎስ /2/ የችግሬ ደራሽ ና በፈረስ እንባዬን ልታብስ ፈጥነህ ድረስ ባስልዮስ ጎርጎሪወቀስ ሰምሯል ልመናቸው ስዕሉ ዘለለ ታምራት አያችሁ እናንተን የረዳ መጥቶ በፈረስ ዛሬም ለኛ ይድረስ ይምጣ መርቆሬዎስ ዑልያኖስ ተገድሏል ሃይማኖት ይስፋፋል ብሎ መሰከረ መርቆርዮስ ሃያል ገፀ ከላባቱ ባህርይ ቀየሩ እርሱን ለማገልገል ከእግሩ ስር አደሩ ትካዜ ሀዘኔ ይርቃል ጭንቀቴ መርቆርዮስ ሲመጣ ሲገባ ከቤቴ በፀሊም ፈረሱ እየገሰገሰ መርቆሬዎስ ወዳጄ ስጠራው ደረሰ ስቃዩን ሊያረዝም ዳኪዎስ ወደደ ከጨለማ እስር ቤት ታስሮ ተወሰደ በጋለ ሹል ብረት መርቆሬዎስ ተወጋ ስሙ ተሰየመ ከሰማዕት ጋ አልፈራም መከራ አልፈራም ችግር መፍቅሬ አብ ካለ ያኘሎፓዴር ቂሳርያ እስር ቤት መርቆሬዎስ ታሰረ ወህኒ ቤቱ በራ እግዚአብሔር ከበረ @EthiopianOrthodoxTewahdoMezmurs
Show all...
​​#ጥር\_23 #ሐዋርያው\_ቅዱስ\_ጢሞቴዎስ አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሃያ ሦስት በዚች ዕለት አሕዛብን ለሚያስተምር ለከበረ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ የሆነ የከበረ ሐዋርያ ጢሞቴዎስ በሰማዕትነት ሞተ። የዚህም ቅዱስ ልደቱና እድገቱ ልስጥራን ከሚባል አገር ነው አባቱም ከዋክብትን የሚያመልክ ዮናናዊ ነው እናቱ ግን በኦሪት ሕግ ጥላ ሥር ያለች ናት። የከበረ ሐዋርያ ጳውሎስም በልስጥራን ሀገር በሰበከ ጊዜ ይህ ጢሞቴዎስ ስብከቱንና ትምህርቱን ሰማ እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያደርጋቸውን ድንቆች ተአምራቶችን አይቶ እሊህም ተአምራቶች አስተዋዮችና ጥበበኞች የሚደነግጡባቸው ናቸው ስለዚህም ወደ ሐዋርያ ጳውሎስ ሒዶ በእርሱ ትምህርት በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠምቆ የሐዋርያ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ ሆነ ወደ ብዙ አገሮችም ተከትሎት በመሔድ ከእርሱ ጋር ደከመ ታላቅ መከራና ብዙ ኀዘንም ደርሶበታል ሐዋርያው ጳውሎስም በኤፌሶን ውስጥ በአንዲት አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾመው። በዚያንም ጊዜ ወደርሷ ገብቶ ለሰዎቿ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰበከ ብዙዎችንም ወደ ቀናች ሃይማኖት መልሶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው ከዚህም በኋላ በዙሪያዋ ወዳሉ ብዙዎች አገሮች በርቀትም ለሚገኙ አገሮችም የከበረ ወንጌልን ሰበከላቸው። የከበረ ሐዋርያ ጳውሎስም ሁለት መጻሕፍቶችን ጽፎ ወደርሱ ልኳል እርሳቸውም ሕዝቡን የሚያስተምርባቸው ራሱም ከቢጽ ሐሳውያን የሚጠበቅባቸው ቅስና ወይም ዲቁና ሊሾም የሚገባውንና የማይገባውን የሚለይበት ክህነት በማይገባው እጁን እንዳይጭን የሚያስጠነቅቁ ናቸው ጢሞቴዎስን ደግሞ ለርሱ ተወዳጅ ልጁ አድርጎ ይጠራዋል መልእክቶቹንም በእርሱ እጅ ወደ አገሮች ልኳል። በላያቸው የተሾመባቸውን የክርስቶስን መንጋዎች ፈጽሞ በጠበቀ ጊዜ በትምህርቶቹ በተግሣጾቹና በድርሰቶቹ ልቡናቸውን ብሩህ አደረገ አይሁድንና ዮናናውያንን ይገሥጻቸውና ይዘልፋቸው ነበር እነርሱም ቀንተውበት ሁሉም በጠላትነት ተነሡበት ተሰብስበውም ገደሉት ምእመናንም ሥጋውን አንሥተው ቀበሩት ጻድቅ ቈስጠንጢኖስም እስከ ነገሠ በዚያው ኖረ እርሱም ስለ ሥጋው አስቦ ወደ ቊስጥንጥንያ ከተማ በጥር ወር በሃያ ሰባት ቀን አፈለሰው በዚያችም ቀን በዓል አደረገለት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሱ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። (#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
Show all...

👍 3
እንኳን ለቅዱስ ዑራኤል አመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳቹ አደረሰን! መልዐኩ ቅዱስ ዑራኤልና አገልግሎቱ በጥቂቱ ✍ ዑራኤል የሚለው ስም "ዑር"እና ኤል ከሚለው ሁለት ቃላት የተመሰረተ ነው ። ትርጉሙም ብርሃነ ጌታ አምላክ  ብርሃን ነው። ማለት ነው። ✍ ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ መብረቅና ነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው።በመሆኑም መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበቁ ነጓድጓድ ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። (መጽሐፈ ሄኖክ ፮፥፪) ✍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከእየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግብጽ ስትሰደድ መንገድ እየመራ፤ ከእስራኤል ወደ ግብጽ ከዚያም ከእመቤታችን ጋር በሀገራችን ኢትዮጵያ እየመራ ያመጣት መልአክ ነው። ✍ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሆኖ በተሰቀለበት ጊዜ፥ክቡር ደሙ በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃን ነሳንስ የረጨው እሱ ነው። ✍ ለነብዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ልቦና ያጠጣው፥ጥበብን ማስተዋልን የሰጠው የጠፉ መጽሓፍት በቃሉ አስታውሶ እንደገና ያጻፈው የረዳው መልአክ ነው።(ዕዝ፲፫፥፴፱) ✍ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ትዕዛዝ ብዙ ድርሰት የደረሱት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ጽዋ ህይወት ስላጠጣቸው ነው። ✍ በዓላቱም በዓመት 3ናቸው። ፩...ጥር። 22 በዓለ ሲመቱ፤ ፪....መጋቢት 27 የጌታችንን ደም በዓለም የረጨበት፤ ፫...ሐምሌ 21 እና 22 ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ። ✍ በጸሎቱ የተማጸነ ከእግዚአብሔር አምላክ በረከትን ፣ምህረትን የሚያሰጥ አዛኝ ጠባቂ ና የዋህ መልአክ ነው።በተለይም ህጻናትን የሚጠብቅ የሚለምኑትን ሁሉ የሚሰማ ፥ኃጢአተኞች ካሉበት ቦታ እኔን ላከኝ እያለ አምላኩን የሚማጸን አዛኝ የዋህ መልአክ ነው። ✍ ይህ አለም በአማላጅነቱ አምኖ በእምነት ጸበሉን ቢጠጣ ፥ዝክሩንም ቢዘክር ከክፉ በሽታው እንደሚድን፤ እንደሚፈውሰው ቃል ኪዳን ተሰጥቶታል ። ✍ ቅዱሳን መላዕክት እግዚአብሔርን በሚፈሩ ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራሉ ከመከራም ያድኑዋቸዋል።(መዝ ፴፫÷፯) የአባታችን የጠባቂያችን የአማላጃችን የመልአኩ የቅዱስ ዑራኤል ቃል ኪዳን አይለየን።    ወስብሐት ለእግዚአብሔር
Show all...
🌷✞ ገብርኤል በሰማይ ✞🌷 ገብርኤል በሰማይ ኤልሳቤጥ በምድር/፪/ ይመሰክራሉ ድንግል ያንቺን ክብር/፪/ ትፀንሺ ሲልክ በከበረ ዜና ይሁንልኝ አልሽው ትውልድ እንዲፅናና ከገብርኤል ሰምተው መላዕክቱ ሁሉ ለበጉ ማደሪያ ክብርን ይሰጣሉ ብፅሂት እንላለን እኛም አደግድገን የራማውን ልዑል አብነት አድርገን     ስርሽ በምድር ነው ሀረግሽ በሰማይ ንፁህ መሶበ ወርቅ የተመላሽ ሲሳይ የማህፀንሽ ፍሬ በላነው ጠጣነው በኤፍራታ ሰምተን በዱር አገኘነው የተሰወረውን መና በልተነዋል ከተመረጡት ጋር ብፅሂት ብለናል     ከተፈጥሮ በላይ ፅንስን ያዘለለ የእሳት ምሰሶ ባንቺ ተተከለ የእግዚአብሔር ሀገሩ የእንጀራ ቤታችን ምንኛ ድንቅ ነው ክብርሽ እናታችን ብፅይት እንላለን እኛም አደግድገን ቅድስት ኤልሳቤጥን አብነት አድርገን     ተወልዶ በግርግም ተኝቶ ስላዪት ሰዉና መላዕክት አብረው አከበሩት የጥሉ ግርግዳ በልጅሽ ፈረሰ በዳግማዊት ሄዋን የአዳም ዘር ተካሰ እጅ እንነሳለን ሁነን በትህትና ክብርሽን መመስከር ክብራችን ነው እና 💚@yemezmurgetemoche 💛@yemezmurgetemoche ❤️@yemezmurgetemoche
Show all...
🌷✞ ገብርኤል በሰማይ ✞🌷 ገብርኤል በሰማይ ኤልሳቤጥ በምድር/፪/ ይመሰክራሉ ድንግል ያንቺን ክብር/፪/ ትፀንሺ ሲልክ በከበረ ዜና ይሁንልኝ አልሽው ትውልድ እንዲፅናና ከገብርኤል ሰምተው መላዕክቱ ሁሉ ለበጉ ማደሪያ ክብርን ይሰጣሉ ብፅሂት እንላለን እኛም አደግድገን የራማውን ልዑል አብነት አድርገን     ስርሽ በምድር ነው ሀረግሽ በሰማይ ንፁህ መሶበ ወርቅ የተመላሽ ሲሳይ የማህፀንሽ ፍሬ በላነው ጠጣነው በኤፍራታ ሰምተን በዱር አገኘነው የተሰወረውን መና በልተነዋል ከተመረጡት ጋር ብፅሂት ብለናል     ከተፈጥሮ በላይ ፅንስን ያዘለለ የእሳት ምሰሶ ባንቺ ተተከለ የእግዚአብሔር ሀገሩ የእንጀራ ቤታችን ምንኛ ድንቅ ነው ክብርሽ እናታችን ብፅይት እንላለን እኛም አደግድገን ቅድስት ኤልሳቤጥን አብነት አድርገን     ተወልዶ በግርግም ተኝቶ ስላዪት ሰዉና መላዕክት አብረው አከበሩት የጥሉ ግርግዳ በልጅሽ ፈረሰ በዳግማዊት ሄዋን የአዳም ዘር ተካሰ እጅ እንነሳለን ሁነን በትህትና ክብርሽን መመስከር ክብራችን ነው እና 💚@yemezmurgetemoche 💛@yemezmurgetemoche ❤️@yemezmurgetemoche
Show all...
🌷✞ ገብርኤል በሰማይ ✞🌷 ገብርኤል በሰማይ ኤልሳቤጥ በምድር/፪/ ይመሰክራሉ ድንግል ያንቺን ክብር/፪/ ትፀንሺ ሲልክ በከበረ ዜና ይሁንልኝ አልሽው ትውልድ እንዲፅናና ከገብርኤል ሰምተው መላዕክቱ ሁሉ ለበጉ ማደሪያ ክብርን ይሰጣሉ ብፅሂት እንላለን እኛም አደግድገን የራማውን ልዑል አብነት አድርገን     ስርሽ በምድር ነው ሀረግሽ በሰማይ ንፁህ መሶበ ወርቅ የተመላሽ ሲሳይ የማህፀንሽ ፍሬ በላነው ጠጣነው በኤፍራታ ሰምተን በዱር አገኘነው የተሰወረውን መና በልተነዋል ከተመረጡት ጋር ብፅሂት ብለናል     ከተፈጥሮ በላይ ፅንስን ያዘለለ የእሳት ምሰሶ ባንቺ ተተከለ የእግዚአብሔር ሀገሩ የእንጀራ ቤታችን ምንኛ ድንቅ ነው ክብርሽ እናታችን ብፅይት እንላለን እኛም አደግድገን ቅድስት ኤልሳቤጥን አብነት አድርገን     ተወልዶ በግርግም ተኝቶ ስላዪት ሰዉና መላዕክት አብረው አከበሩት የጥሉ ግርግዳ በልጅሽ ፈረሰ በዳግማዊት ሄዋን የአዳም ዘር ተካሰ እጅ እንነሳለን ሁነን በትህትና ክብርሽን መመስከር ክብራችን ነው እና 💚@yemezmurgetemoche 💛@yemezmurgetemoche ❤️@yemezmurgetemoche
Show all...