en
Feedback
የ ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ዲጅታል ቤተ-መጽሐፍ

የ ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ዲጅታል ቤተ-መጽሐፍ

Open in Telegram

ይህ የተለያዩ መንፈሳዊ መጻሕፍት የሚጋሩበት የ ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ዲጅታል ቤተ-መጽሐፍ ነው። ለ መወያየት : ለ ገንቢ ሀሳባት እና ለ መጻሕፍት ጥቆማ @timbri7 እንዲሁም @YNSel

Show more
927
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+930 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
June '25
June '25
+8
in 1 channels
May '25
+21
in 1 channels
Get PRO
April '25
+11
in 1 channels
Get PRO
March '25
+31
in 1 channels
Get PRO
February '25
+31
in 1 channels
Get PRO
January '25
+23
in 2 channels
Get PRO
December '24
+54
in 1 channels
Get PRO
November '24
+57
in 1 channels
Get PRO
October '24
+25
in 0 channels
Get PRO
September '24
+20
in 0 channels
Get PRO
August '24
+50
in 2 channels
Get PRO
July '24
+20
in 0 channels
Get PRO
June '24
+28
in 0 channels
Get PRO
May '24
+49
in 1 channels
Get PRO
April '24
+43
in 1 channels
Get PRO
March '24
+87
in 1 channels
Get PRO
February '24
+49
in 1 channels
Get PRO
January '24
+72
in 1 channels
Get PRO
December '23
+70
in 0 channels
Get PRO
November '23
+66
in 0 channels
Get PRO
October '23
+331
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
19 June0
18 June0
17 June0
16 June0
15 June+1
14 June0
13 June+2
12 June+1
11 June+1
10 June+1
09 June0
08 June0
07 June0
06 June0
05 June0
04 June0
03 June+1
02 June+1
01 June0
Channel Posts
📖 መጽሐፉ ሰማዕትነት አያምልጣችሁ እና ሌሎች ይሰኛል ✍🏽 ተርጓሚው መምህር ገብረእግዚአብሔር ኪደ ናቸው። መጽሐፉ የተወደደውን አባት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በተለያዩ ጊዜያት ያስተማራቸው ትምህርቶች እና የሰበካቸው ስብከቶች ተሰባስበው የተዘጋጀ መድብል ነው። መጽሐፉ በብዛት የእያንዳንዳችንን ሕይወት የሚነኩ ስብከቶች ያሉበት ሲሆን በስብከቶቹ መካከልና መጨረሻ ላይ የምናገኛቸው ጥያቄዎች ደግሞ ወደ ውስጣችን እንድንመለከት የሚያደርጉ ናቸው። ለአብነት ያህል መጽሐፉ የተሰየመበት 'ሰማዕትነት አያምልጣችሁ' የሚለው ግሩም ስብከት የዘመናችን ሰማዕትነት ምን አይነት እንደሆነ የሚያብራራ ሲሆን (ሰማዕትነትን ልዩ በሆነ መነጽር ያየዋል) ከእሱም ጋር በመዋጋት ከሰማዕታት በረከት እንድንሳተፍ የሚመክር ነው። በአጠቃላይ መጽሐፉ አጫጭር በአጫጭር ስብከቶችን የያዘ መሆኑና ሳቢ መሆናቸው ለንባብ ጀማሪዎችን ወደ ንባብ የሚያቀርብ ያደርገዋል። የንባብ ልምድ ያለውም ቢሆን የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስብከቶች ጣዕም ከተመስጦው ይወጣ ዘንድ አይፈቅዱለትም። የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ረድኤትና በረከት በሁላችን ላይ ይደርብን!🙏🏽

2
#ግንቦትና_ልደት #መርገምና_በረከት #ግንቦት ወር #በመጀመሪያ👇 • አዳምና ሔዋን ዕፀ በለስን የበሉበት • አዳምና ሔዋን ከገነት የወጡበት • ኢዮብ የተወለደበት #ግንቦት ወር #በሁለተኛ👇 • እመቤታችን የተወለደችበት • ጌታ ወደ ሰማይ ያረገበት • መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ የወረደበት ወር ነው፡፡ ግንቦት በጥንት ዘመን የሚፈራ ወር ነበር፤ በብዛትም በዚህ ወር ሠርግ አይደረግበትም ነበር፤ ዋናው ምክንያት ደግሞ ኢዮብ የተወለደበት ወር በመሆኑ ነው፡፡ ከልደተ ኢዮብ ጋር ምን አገናኘው? ቢሉ ኢዮብ የተወለደበትን ቀን እንዲህ ብሎ ረግሞታል፦ ✿ ከዚያም በኋላ ኢዮብ አፉን ከፍቶ የተወለደበትን ቀን ረገመ። ያ የተወለድሁበት ቀን ይጥፋ፥ ያም ወንድ ልጅ ተፀነሰ የተባለበት ሌሊት። ያ ቀን ጨለማ ይሁን፤ እግዚአብሔር ከላይ አይመልከተው፥ ብርሃንም አይብራበት። ቀኖች መካከል ደስ አይበለው፤ በዓመቱ በወሮች ውስጥ ገብቶ አይቈጠር። እነሆ፥ ያ ሌሊት መካን ይሁን፤ እልልታ አይግባበት።✿ ኢዮ 3፡1-7፡፡ በማለት ረግሞት ነበር፡፡ ይህ ወር ሰይጣን ጻድቃንን የከሰሰበት፤ ኢዮብን የፈተነበት ወር ነበር፤ (ኢዮ 2፡1-10)፤ በአንፃሩ የሰይጣን ወዳጆች ራሱን ሰይጣንን የሚጠሩበት፤ ለሰይጣን መሥዋዕት የሚያቀርቡበት ወር ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት የጥንት ሰዎች ሩቅ መንገድ መጓዝ፤ ጋብቻ መፈጸም የመሳሰሉ ትልልቅ ጉዳዮችን አያከናውኑም ነበር፤ ወሩ ሰይጣን የሚሰለጥንበት ነው ተብሎ ስለሚታሰብ፡፡ ይህ ልማድ በብሉይ ኪዳን ነበር፡፡ እግዚአብሔር ቸር ነውና የዚህን ወር ርግማን ወደ በረከት ይቀይረው ዘንድ በዚህ ወር ሦስት ታላላቅ ነገሮችን አከናወነበት፡፡ 1. ልደተ ማርያም፦ እመቤታችን የተፀነሰችው ነሐሴ ሰባት ቀን ሲሆን የተወለደችው ግንቦት አንድ ቀን ነው፡፡ የእመቤታችን ልደት የመዳናችን ዋና መሠረት ነው፤ እርሷ ካልተወለደች ክርስቶስ በሥጋ አይወለድም፤ እርሱ በሥጋ ካልተወለደ ቤዛ የሚሆነን ዘመድ አይኖረንም ነበር፤ ቅዱስ ያሬድ " ከመ ትቤዙ ነቢያተ ወጻድቃነ.." (ለነቢያትና ለጻድቃን ቤዛ ትሆን ዘንድ (ክርስቶስን በመውለድ)) ብሎ ተናግሯል፤ የዕለቱ ምልጣን፡፡፡፡ ☞የእመቤታችን ልደት የእውነተኛው ፀሐይ ክርስቶስ ልደት እስኪገለጥ ድረስ ሌሊቱን እንደ ጨረቃ እያበራ ያቆየን ተስፋችን ነበር፡፡ እመቤታችን በራእየቴክታ በጨረቃ የተመሰለችውም ይህንን ምሥጢር ያሳያል፡፡ • ኢዮብ የተወለደበት ይህ ወር እንዲጎድል ተረግሞ ነበር እመቤታችን ግን ሙሉ ጨረቃ ሆና እያበራች ወሩን ሙሉ (30) አደረገችው፡፡ • የኢዮብ ጨረቃ 29 ቀን ብቻ የምታበራ 1 ቀን ያጨለመች ናት (ኢዮብ ማለት ጨረቃ አበባ ማለት ነው) እመቤታችን ግን ሶልያና ተብላ 30ውን ሌሊት ሙሉ ያበራች ሙሉ ጨረቃ ናት (ሶልያና ማለት ሙሉ ጨረቃ ማለት ነው፤ የጨለመብንን ሌሊት ታብራልን!) • ኢዮብ የተወለደበትን ቀን ጨለማ እንዲሆን ብርሃን እንዳይኖርበት የረገመውን ቀን ድንግል "የብርሃን እናት" ሆና ተወለደችበት፤ ቅዱስ ያሬድ "ዮም ተወልደት እመ ብርሃን"ማለቱም ለዚህ ነው፡፡ • ኢዮብ የተወለደበትን ቀን "ዕልልታ አይደረግበት" ብሎ ረግሞት ነበር እመቤታችን ስትወለድ ግን እርግማኑ ተሻረ፤ ፍጥረት ሁሉ "እልል.." አለ፤ • የሊባኖስ ተራሮች ብሥራተ ልደቷን ተናገሩ፤ እናት አባቷ እልል አሉ፤ እኛም ከቅዱስ ያሬድ ጋር አሁንም " ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም" እያልን እልል...... እንላለን፡፡ • ኢዮብ የተወለደበትን ከቀኖች ተለይቶ ቀን መካን ይሁን ብሎ ቢረግመውም "ድንግል እልፍ ሆና" ተወለደችበት፤ "መልአት ምድረ ወሰማያተ ወሊዳ ዋሕደ ወተወሊዳ አሐተ ፤ መልአት ምድረ ወሰማያተ" እንዳለ ባለቅኔ (አንድ ሆና ተወልዳ፣ አንድ ብቻ ወልዳ ሰማዩንም ምድሩንም ሞላችው)፡፡፡ • ክርስቶስ አዳምን የረገመበትን ዕለተ ዓርብ ተሰቅሎበት መርገምን ሺሮ ዓርብን ቅዱስ ቀን እንዳደረገው ሁሉ እመቤታችንም ኢዮብ ተወልዶ የረገመውን ወር ተወልዳበት ባረከችልን!!! • ድንግል ሆይ ልደትሽ በረከታችን ነው!!! • ድንግል ሆይ የልደትሽ ቀን ሙላታችን ነው!!! 2. ዕርገተ ክርስቶስ፦ ጥንተ ዕርገት ግንቦት 8 ቀን ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ሰይጣን እስከ ሶስተኛው ሰማይ ድረስ ሄዶ ሰዎችን የመክሰስ ሥልጣን ነበረው፤ አሁን ግን አይችልም! ከምድር እስከ ሰማይ ድረስ በደመ ክርስቶስ ማኅተም ተዘጋ፤ ወደላይ የሚወጡት ክርስቶስና መላእክት፤ ክርስቶሳውያን ብቻ ናቸው፡፡ ከሳሽነት ቀረ፤ አዳም ነጻ ወጣ፤ መንገዱ ሁሉ ተባረከ!!! ጌታችን ሲያርግ እጆቹን አመሳቅሎ እየባረከን ነበር!!! እየባረከን እንደባረከን የሰይጣንን ክስ አስቀርቶ በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ!!! እንጠራለን እንጂ አንከሰስም! ☞በዚህ ወር እስከ ሶስተኛው ሰማይ የወጣው ሰይጣን በዚህ ወር ተባረረ!!! 3. ልደተ ቤተ ክርስቲያን (ርደተ ጰራቅሊጦስ)፦ መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረደላቸው በዚህ ወር (ግንቦት 18) ነበር፡፡ ይህም ልደተ ቤተ ክርስቲያን እርግጥ የሆነበት ከ 3000 ሕዝብ በላይ የተጠመቀበት ዕለት ነበር፡፡ ☞ኢዮብ መካን (መኻን) እንዲሆን የረገመውን ቀን መንፈስ ቅዱስ ባርኮት እልፍ አእላፍ ሆነን ተወለድንበት!!!! 👉አዳምና ሔዋን የበለሱን ፍሬ በልተው ከገነት ቢወጡም በእግዚአብሔር ቸርነት በ ጸጋ በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ወደ ሰማይ የምንሄድበት ሥልጣን ተሰጠን!!! ይህን ያደረገ አምላካችን የተመሰገነ ይሁን!!! የአመቤታችን የልደቷ በረከት ይደርብን! ምልጃዋ ሀገራችንን ይጠብቅልን ሕሙማንን ይፈውስልን!!! የተወለድንበትን ቀን ከምንረግምበት ፈተና ሁሉ እግዚአብሔር ይሠውረን!!!! (በድጋሚ የተለጠፈ) ወሩን ቸር የምንሰማበት ያድርግልን!!! አሜን!! መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው
715
3
የሰሞኑ 'ቤዛ ለፍጡራን (በተለይ ከእመቤታችን ጋር በተያያዘ) ይቀጸላል ወይስ አይቀጸልም?' የሚለው ጥያቄ ግራ አጋብቶኛል፤ አንድ ጥሩ መጽሐፍ አንብቤ ከመወዛገብ መገላገል እፈልጋለሁ ካላችሁ እነሆ! መፍትሔው - ይሄ መጽሐፍ ለእናንተ ነው።😉 📖 መጽሐፉ እምነገረ ማርያም ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ይሰኛል ✍🏻 ጸሐፊው መምህር ሙሴ ኃይሉ ናቸው። መጽሐፉ ነገረ ማርያም ላይ ያተኮረ እንደመሆኑ ስለ ነገረ ማርያም ትምህርት መነሻና እድገት ታሪክ ማብራርያ በመስጠት ይጀምርና ነገረ ማርያም ከነገረ ድኅነት ጋር ያለውን ግንኙነት ያስረዳል። በዚህ ምዕራፍ ነገረ ማርያም ዛሬ የተጀመረ እንዳልሆነና ቀደምት የቤተክርስቲያን አባቶችም (early church fathers) ጭምር ያስተማሩት እንደሆነ መረዳት ይቻላል በቀጣዩ ምዕራፍ ደግሞ 'መድኃኒት' የሚለውን ቃል በመበየን (define በማድረግ) ይጀምርና 'ይህ ቃል ለፍጡራን መሰጠት ይችላል ወይ?' የሚለውን በአግባቡ ይመልሳል በተመሳሳይ መልኩ 'ቤዛ' የሚለውንም ቃል ከተረጎመ በኋላ ለፍጡራን ስለመሰጠቱ ያሳይና ነገሩን ከእመቤታችን 'ቤዛዊተ ዓለም' መባል ጋር ያገናኘዋል። በመጨረሻም ክብረ ድንግል ማርያም እንዲሁም ከዛ ጋር የሚገናኙ ጉዳዮችን አንስቶ መጽሐፉን ያጠናቅቃል። መጽሐፉ የሊቃውንትን ምስክርነት በአግባቡ የሚያቀርብ መሆኑ ብዥታን በደንብ የሚቀርፍ ነው። እመቤታችን ጣዕመ ፍቅሯን በልቡናችን ጣዕመ ስሟን በአንደበታችን ታውልብን፤ ታሳድርብን! 🙏🏼 መልካም ንባብ! 🤗
842
4
ከትንሣኤ በኋላ ያሉ ዕለታት ቅዳሜ ቅዱሳት አንስት ይባላል በወንጌል ተጽፎ እንደምናነበው ፍቅሩን በማሰብ ጨለማውን ሳይፈሩ ወደ መቃብር ስለመጡት መግደላዊት ማርያም እና ማርያም ባውፍልያ በስፋት ቤተክርስቲያን እንድናስብ ስለምታስተምረን ቅዱሳት አንስት ተብሏል። ወንጌሉ ስለዚህ ዕለት እንዲህ ብሎ ይገልጻል :- "ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን መግደላዊት ማርያም ገና ጨለማ ሳለ ማለዳ ወደ መቃብር መጣች ድንጋዩም ከመቃብሩ ተፈንቅሎ አየች። እየሮጠችም ወደ ስምዖን ጴጥሮስና ኢየሱስ ይወደው ወደ ነበረው ወደ ሌላው ደቀ መዝሙር መጥታ፦ ጌታን ከመቃብር ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አናውቅም አለቻቸው። ስለዚህ ጴጥሮስና ሌላው ደቀ መዝሙር ወጥተው ወደ መቃብሩ ሄዱ። ሁለቱም አብረው ሮጡ፤ ሌላው ደቀ መዝሙርም ከጴጥሮስ ይልቅ ፈጥኖ ወደ ፊት ሮጠና አስቀድሞ ከመቃብሩ ደረሰ፤ ዝቅም ብሎ ቢመለከት የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥ ነገር ግን አልገባም። ስምዖን ጴጥሮስም ተከትሎት መጣ ወደ መቃብሩም ገባ፤ የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥ ደግሞም በራሱ የነበረውን ጨርቅ ለብቻው በአንድ ስፍራ ተጠምጥሞ እንደ ነበረ እንጂ ከተልባ እግሩ ልብስ ጋር ተቀምጦ እንዳልነበረ አየ። በዚያን ጊዜ አስቀድሞ ወደ መቃብር የመጣውም ሌላው ደቀ መዝሙር ደግሞ ገባ፥ አየም፥ አመነም፤ ከሙታን ይነሣ ዘንድ እንዲገባው የሚለውን የመጽሐፉን ቃል ገና አላወቁም ነበርና። ደቀ መዛሙርቱም ወደ ቤታቸው ደግሞ ሄዱ። ማርያም ግን እያለቀሰች ከመቃብሩ በስተ ውጭ ቆማ ነበር። ስታለቅስም ወደ መቃብር ዝቅ ብላ ተመለከተች፤ሁለት መላእክትም ነጭ ልብስ ለብሰው የኢየሱስ ሥጋ ተኝቶበት በነበረው አንዱ በራስጌ ሌላውም በእግርጌ ተቀምጠው አየች። እነርሱም፦ አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? አሉአት። እርስዋም፦ ጌታዬን ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አላውቅም አለቻቸው። ይህንም ብላ ወደ ኋላ ዘወር ስትል ኢየሱስን ቆሞ አየችው፤ ኢየሱስም እንደ ሆነ አላወቀችም። ኢየሱስም፦ አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? ማንንስ ትፈልጊያለሽ? አላት። እርስዋም የአትክልት ጠባቂ መስሎአት፦ ጌታ ሆይ፥ አንተ ወስደኸው እንደ ሆንህ ወዴት እንዳኖርኸው ንገረኝ እኔም እወስደዋለሁ አለችው። ኢየሱስም፦ ማርያም አላት። እርስዋ ዘወር ብላ በዕብራይስጥ፦ ረቡኒ አለችው፤ ትርጓሜውም፦ መምህር ሆይ ማለት ነው። ኢየሱስም፦ ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ፦ እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው አላት። መግደላዊት ማርያም መጥታ ጌታን እንዳየች ይህንም እንዳላት ለደቀ መዛሙርቱ ነገረች። (ዮሐ፳:፩-፲፰)
710
5
ከትንሣኤ በኋላ ያሉ ዕለታት አርብ ቅድስት ቤተክርስቲያን/ነፍሳት/ ይባላል በዚህ ዕለት ቅድስት ቤተክርስቲያን ተብሎ የተሰየመበት ምክንያት በጥቂቱ በቤተክርስቲያን ዙሪያ ሰባት ነገሮችን እንድናስብ ነው፡፡ እነዚህም፡- ፩. ቅድስት ቤተክርስቲያን በሞቱ እና በትንሣኤው መመስረቷን እናስባለን፡፡ ፪. አምላካችን ራሱን አሳልፎ እንደሰጣት እናስባለን፡፡ ፫. እርሱ ራሷ እርሷ ደግሞ አካሉ እንደሆነች እናስባለን፡፡ ፬. ቅድስት ቤተክርስቲያን መሰረቷ የነብያት እና የሐዋርያት ቃል መሆኑን እናስባለን፡፡ ፭. በደሙ ስለመታጠቧ እናስባለን። ፮. ከነገድ ከቋንቋ ሁሉ ስለመመረጧ እናስባለን፡፡ ፯. ለዘላለም እንዳትናወጽ በእርሱ ላይ ስለመታነጽዋ እናስባለን፡፡ (ሥርዓተ አምልኮ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ገጽ፻፰፯) ነፍሳት ከሲዖል የወጡበት ጌታችን በዕለተ ዓርብ በመልዕልተ መስቀል ቅዱስ ሥጋውን ቆርሶ ክቡር ደሙን አፍስሶ በአካለ ነፍስ ወደ ሲዖል ወርዶ በሲዖል ያላችሁ ውጡ በጨለማ ያላችሁ ተገለጡ ብሎ ግእዛነ ነፍስን ( የነፍስን ነፃነት ) ሰበከላቸው ሰይጣንን አሰረው ሲዖልን መዘበረው ነፍሳትን ነፃ አወጣቸው ልምላሜ ገነትን አወረሳቸው ይህ ዕለት በቀጣዩ በትንሣኤ ሳምንት ዓርብ እንዲታሰብ ነፍሳት የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል ፡፡
553
6
ከትንሣኤ በኋላ ያሉ ዕለታት ሐሙስ አዳም ይባላል ይህ ዕለት አዳም ሐሙስ (አዳም) የተባለበት ምክንያት አምላካችን እግዚአብሔር ለአዳም "ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" ብሎ ቃል የገባበት ዕለት በመሆኑ ይህንን ስያሜ አግኝቷል፡፡(ዘፍ፫፡ ፲፭) ፤ (መጽሐፈ ቀለሜንጦስ አንቀጽ ፰ እና መጽሐፈ አክሲማሮስ ዘዓርብ ቁ. ፲፫) ቤተክርስቲያን በዋናነት ለአዳም የተሰጠውን የተስፋ ቃል አምላካችን መፈጸሙንና የሰው ልጆች ሁሉ በትንሣኤው ከሞት ነጻ እንደወጡ በዚህ ዕለት ታስተምራለች፡፡ በዚህ ዕለት በአባታችን በአዳም በእናታችን በሔዋን አንጻር:- ፩. ከውድቀታችን ይልቅ መነሳታችንን ፪. ከባርነታችን ይልቅ ነጻነታችንን ፫. ከለቅሶአችን ይልቅ መጽናናታችንን ፬. ከሀዘናችን ይልቅ ደስታችንን ፭. ከመሰበራችን ይልቅ መጠገናችንን ፮. ከመታመማችን ይልቅ መፈወሳችንን ፯. ከድካማችን ይልቅ ኃይላችንን ፰. ከመረሳታችን ይልቅ መታወሳችንን ፱. ከጨለማችን ይልቅ ብርሃናነችንን ፲. ከፍርሃታችን ይልቅ ድፍረታችንን ፲፩. ከክህደታችን ይልቅ እምነታችንን ፲፪. ከጥላቻችን ይልቅ ፍቅራችንን ፲፫. ከመታወካችን ይልቅ ሠላማችንን ፲፬. ከሞታችን ይልቅ ሕይወታችንን ፲፭. ከመቃብራችን ይልቅ ትንሣኤአችንን የምናስብበት ዕለት ነው፡፡
607
7
ከትንሳኤ በኋላ ያሉ ዕለታት ማክሰኞ ቶማስ ይባላል እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ሲፈጥረው የሚያንቀላፋና የሚነቃ አድርጎ ፈጥሮታል፡፡ ማንቀላፋቱ የሞት ፤ መንቃቱ ደግሞ የትንሣኤ ምሳሌ መሆኑን ስናስብ ሁሌም ይደንቃል፡፡ አባቶቻችን የትንሣኤውን ምሥጢር በአበው እና በስነፍጥረትም ይመስሉታል፤ አቤል ከሞተ በኋላ በደሙ መናገሩ እና የሔኖክ ሳይሞት በእግዚአብሔር መሰወሩ የትንሣኤ ምሣሌ ናቸው፡፡ በተፈጥሮ ፀሐይ መውጣቷ የመወለዱ ፤ መጥለቋ የሞቱ እና ዳግመኛ መውጣቷ የትንሣኤው ምሣሌ ነው፡፡ አምላካችን ክብር ይግባውና በእርሱ ያመንን ሁላችን እንደምንነሳ የእርሱ ከሙታን መካከል በሥልጣኑ መነሳት ለሁላችን መነሳት በኩር መሆንና ማረጋገጫም እንደሆነ በቃሉም በተግባሩም ያስተማረን የትንሣኤ ጌታ ነው፡፡ በቃሉ "በመቃብር ያሉት ሁሉ ድምጹን የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል ፤ መልካም ያደረጉ ለሕይወት ትንሣኤ ፤ ክፉም ያደረጉ ለፍርድ ትንሣኤ ይወጣሉና በዚህ አታድንቁ " (ዮሐ፭፡፳፱) እንዲሁም በተግባር የአራት ቀን ሬሳ አልዓዛርን አስነስቷል፡፡(ዮሐ፲፩፡፵፫) የትንሣኤው ምሥጢር ሁላችን አምላክ የሆንበት ፤ በሁሉ ላይ ሥልጣን ያገኘንበት ፤ነጻ ወጥተን ነጻ አውጪ የሆንበት ፤ ከማይጠፋ ዘር እንደተወለድን ያረጋገጥንበት ፤ ሞትን የተዘባበትንበት ፤ ጨለማን የረታንበት ከዓለም እና ከዲያብሎስ እስራት ነጻ የወጣንበት ልዩ ክብር ኃይል እና ጸጋን ያገኘንበት ምሥጢር ነው፡፡ ይህቺ ዕለትም ይህንኑ ምሥጢር ነው የምትገልጥልን ሐዋርያው #ቶማስ ተብሎ ለምን ተሰየመ የሚለውን ከማየታችን በፊት ማነው የሚለውን ማየት ነገርን ከስሩ እንድንረዳው ይረዳናልና እውነት ሐዋርያው ቶማስ ማነው? ሐዋርያው ቶማስ ሐዋርያው ቶማስ የስሙ ትርጓሜ ፀሐይ ማለት ሲሆን የቀድሞ ስሙ ዲዲሞስ ይባላል ትርጉሙም ጨለማ ማለት ነው፡፡ ቁጥሩ ከ፲፪ ሐዋርያት ነው፡፡ (ማቴ፲፡፫) (መዝገበ ታሪክ ክፍል ሁለት ገጽ፹፱) ፤ ሐዋርያ ማለት ደጅ አዝማች ፤ ቀላጤ ፤ ምጥው ፤ ፍንው ፤ ሂያጅ ማለት ነው፡፡(ወንጌል ቅዱስ ገጽ፻፶፱) ሐዋርያው ቶማስ አልዓዛር በሞተ ጊዜ ጌታችን ወደ ኢየሩሳሌም አቅራቢያ ወደነበረው መቃብሩ ለመሄድ በተነሳ ጊዜ አይሁድ ሊገሉት ስለሚፈልጉ ሌሎቹ ሐዋርያት ክርስቶስ እንዳይሄድ ቢፈልጉም ቶማሰ ሌሎቹን ሐዋርያት በድፍረት እኛም ከእርሱ ጋር እንሞት ዘንድ አብረን እንሂድ ያለ የእምነት ሐዋርያ ነው፡፡ (ዮሐ፲፩፲፮) ሐዋርያው ቶማስ ጌታችንን በእውነት እስከ ሞት ድረስ ያመነው ከሙታን ተለይቶ ከተነሳ በኋላ በ8ኛው ቀን እሁድ ሲሆን ሐዋርያት የነገሩትን ካላየው አላምንም ብሎ የተወጋ ጎኑን ከዳሰሰ በኋላ ነው፡፡ የእምነት ምስክርነቱም ጌታዬ አምላኬም ብሎ የገለጠው፡፡(ዮሐ፳፡፳፬) ሐዋርያው ቶማስ መንፈስ ቅዱስን ከሐዋርያት ጋር ከተቀበለ በኋላ በ፵፮ ዓ.ም ገደማ በፋርስና በሕንድ እንዳስተማረ የተለያዩ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ይገልጣሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ ፤ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ፤ ቅዱስ አምብሮስ ተጠቃሾች ናቸው፡፡በመጨረሻም ብዙ ተአምራት እና ድንቅን አድርጓል፡፡ የሐዋርያው ቶማስ ተአምር እና አገልግሎት ብዙ ተአምራትን ቢያደርግም ለአሁኑ አንዱን ብቻ እናያለን፡፡ የኸውም የሉክዮስ አገልጋይ ሆኖ በሕንጻ ማነጽ እና በሐውልት መስራት ተቀጥሮ በሚሰራበት ወቅት የሉክዮስን ሚስት ከእነ ልጆቿ እና አገልጋዮቿ አሳምኖ ያጠመቀ ሐዋርያ ነው፡፡ ሐዋርያው ቶማስ ለሕንጻ እና ለሐውልት ማሰሪያ ከሉክዮስ የተቀበለውን ገንዘብና ወርቅ ሁሉ ለነዳያን በመመጽወቱ ንጉሡ እጅና እግሩን አሥሮ ቆዳውን አስገፍፎ ስልቻ አሰፍቶ በአሸዋ ሞልቶ አሸክሞት ገበያ ለገበያ ሲያዞረው የሉክዮስ ሚስቱ አርሶንዋ ተመልክታ በድንጋጤ ሞታለች፡፡ ንጉሡም ለሚስቴ መሞት ምክንያት አንተ ነህ ካዳንካት እኔም በአምላክህ አምናለው ሲለው ጌታችን ቁስሉን እንደ ውኃ አቀዝቅዞለት ካለችበት ሄዶ ስልቻውን ቢያስነካት ተነስታለች በዚህም ሉክያኖስ አምኖ ተጠምቋል፡፡ ሐዋርያው ቶማስ በራሱ ቆዳ በተሰራ ስልቻ እየተዘዋወረ ሙት አስነስቷል ፤ ድውያንን ፈውሷል አሕዛብን አሳምኖ አጥምቋል ፤ በቀንጦፍያ አንድ ሽማግሌ ሰባት ልጆቹን ገድለውበት ሰባቱንም ከሞት አስነስቷል ፤ በኢናስም በቃሉ ትምህርት እና በእጁ ተአምራቱ ብዙዎችን አሳምኖ አጥምቋል፡፡ የሐዋርያው ቶማስ ሰማእትነት በሕንድ የነበሩት የብራሕማን እምነት ተከታዮች የቶማስ ትምህርት የእነርሱን እምነት የሚጻረር እና የሚያጠፋ መሆኑን ተገንዝበው ተነሱበትና በብዙ ስቃይ አሠቃይተው በ፸፪ዓ.ም በሰማዕትነት አርፏል፡፡ በሶርያ ትውፊት መሠረት የሐዋርያው የቶማስ አጽም በአንድ የሶርያ ነጋዴ ተወስዶ በኤዴሳ በክብር አርፏል፡፡ (የእግዚአብሔር መንግሥት ታሪክ በምድር ላይ አንደኛ መጽሐፍ ገጽ ፺፪) ሐዋርያው ቶማስ ለምን ሰምቶ አላመነም? እንደ ወንጌል ትርጓሜ ሐዋርያው ቶማስ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዝግ ቤት ገብቶ ሰላም ለእናንተ ይሁን ባለ ጊዜ አልነበረም ፤ በነገሩት ጊዜም አላመነም ያለማመኑ ምክንያት ሰዱቃዊ ስለነበር እና ሐዋርያቱ አይተው እርሱ ሰማው ብሎ ከሚያስተምር ማየት ወዶ ነው፡፡ "ጌታዬ አምላኬም" (ዮሐ፳:፳፰)
637
8
ከትንሣኤ በኋላ ያሉ ዕለታት ሰኞ ሰኑይ ማእዶት ይባላል እንደ ቤተክርስቲያን ይትባሕል ከትንሣኤ እስከ ዳግማዊ ትንሣኤ ያለውን ሳምንት እንደ አንድ እሁድ እናከብራለን። ለዚህም ነው ዕለታቱን እንደ ሰንበት እናከብራቸው ዘንድ በፍትሐ ነገሥት ላይ አባቶቻችን ትእዛዝ የቀረጹልን። ማእዶት ማለት መሻገር ማለት ነው። አደወ ማለት ተሻገረ ማለት ሲሆን ማእዶት መሸጋገሪያ ማለት ሊሆን ነው። ማእዶት የትንሣኤ እሑድ ማግስት ጌታ ክርስቶስ በትንሣኤው ምዕመናንን ከሞት ወደ ሕይወት ያሻገረበት ቀን የትንሣኤው ማሳሰቢያ ነው። (ከሣቴ ብርሃን ተሰማ የአማርኛ መዝገበ ቃላት ገጽ ፻፶) መሻገር በዕብራይስጥ ፓሳሕ ከሚባለው ቃል ይመሳሰላል ትርጉሙም ፋሲካ መሻገር ማለፍ የሚል ትርጉም ይሰጣል። ሁላችን እንደምናውቀው እስራኤላውያን ከሚያክብሯቸው አበይት በዓላት አንዱም ፋሲካ ነው። ምክንያታቸው ደግሞ እግዚአብሔር ከሞተ በኩር ያሳለፋቸውን ዕለት ያስቡበታል። ቤተክርስቲያናችንም ይህንን በዓለ ትንሣኤን የፋሲካ በዓል የማክበሯ ምሥጢር ወይም የትንሣኤው ምሥጢር ነፍሳት በአምላካችን ትንሣኤ ከሞት ወደ ሕይወት ፣ ከአሳር ወደ ክብር ፣ ከሲዖል ወደ ገነት መሻገራቸውን በማሰብ አማናዊው ፋሲካ ወይም አሸጋጋሪው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ብላ ታምናለች። እናምናለን። ቅዱስ ጳውሎስ በብሉይ ኪዳን በታረደው የፋሲካ በግ (ዘዳ፲፮:፮) ምትክ አማናዊው ክርስቶስ እንደታረደልን እና ሞት ላያገኘን በሕይወት ለሕይወት እንዳሸጋገረን ሲገልጥ እንዲህ ብሏል:-"" እንግዲህ ያለ እርሾ እንዳላችሁ አዲሱን ሊጥ ትሆኑ ዘንድ አሮጌውን እርሾ አስወግዱ። ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና፤" (፩ ቆሮ ፭:፯) ቅዱስ ጳውሎስ ስለ እርሾም ሆነ ስለ አዲሱ ሊጥ በምሳሌ የሚነግረን እስራኤላውያን የእግዚአብሔርን ፋሲካ ሲያከብሩ ያደርጉት የነበረ ስርዓትን ነው። ይኸውም ፋሲካን ያከበሩት ገና ከነጻነት በፊት ነው። ምክንያቱ ደግሞ ከላይ እንዳየነው ከሞተ በኩር መቅሰፍት ለመዳን እና ከእግዚአብሔር ፍርድ ለመዳን ነበር። በአዲስ ኪዳንም ያለን ክርስቲያኖች በተለይ ይህንን ዕለት ወይም ማእዶትን ስናስብ አምላካችን ከሞት ወደ ሕይወት እንዳሻገረን ፣ ከአሳር ወደ ክብር እንዳሳለፈን ፣ ከድካም ወደ ኃይል እንዳሻገረን ፣ ሁላችን ወደ መንግሥተ ሰማያት ፋሲካችን በሆነው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተሸጋገርን በማመን ሊሆን ይገባል። የፋሲካው ጌታ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሞት ላይ እንድንዘባበትበት ሞትን ፣ ፍርሃትን ፣ ጭንቀትን ፣ ተስፋ መቁረጥን ፣ ሐዘንን ፣ ለቅሶን ፣ ትካዜን ፣ ድካምን ፣ ሥጋትን እና መቃብርን ሁሉ አጥፍቶ አሻግሮናል። ክብር ማዕዶታችን ለሆነ ለእርሱ ይሁን። አሜን ክብር ይግባውና አምላካችን የሰው ልጅ ሞትን እንዲሻገር ሁለት ነገሮች(እምነት እና ምግባር ) እንደሚያስፈልጉት በመዋለ ስብከቱ እንዲህ ሲል አስተምሮናል:- "እውነት እውነት እላችኋለሁ ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሙታን የእግዚአብሔርን ልጅ ድምፅ የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል እርሱም አሁን ነው፤ የሚሰሙትም በሕይወት ይኖራሉ።" (ዮሐ፭:፳፬-፳፭) ሊቁ ቅዱስ ያሬድም ዕለቷ ፋሲካ እንደሆነችና እንደሰትባት ዘንድ የተገባች እንደሆነች እንዲህ ሲል በመዝሙሩ አዚሞታል:- " ፋሲካ ዛቲ ዕለት ቅድስት ይእቲ (ይህቺ የፋሲካ ዕለት ልዩ ናት) ፣ ዛቲ ዕለት ንትፈሳሕ በቲ (በዚህ ዕለት ሐሴት እናድርግባት).
478
9
ከትንሣኤ በኋላ ያሉ ዕለታት ሰኞ ሰኑይ ማእዶት ይባላል እንደ ቤተክርስቲያን ይትባሕል ከትንሣኤ እስከ ዳግማዊ ትንሣኤ ያለውን ሳምንት እንደ አንድ እሁድ እናከብራለን። ለዚህም ነው ዕለታቱን እንደ ሰንበት እናከብራቸው ዘንድ በፍትሐ ነገሥት ላይ አባቶቻችን ትእዛዝ የቀረጹልን። ማእዶት ማለት መሻገር ማለት ነው። አደወ ማለት ተሻገረ ማለት ሲሆን ማእዶት መሸጋገሪያ ማለት ሊሆን ነው። ማእዶት የትንሣኤ እሑድ ማግስት ጌታ ክርስቶስ በትንሣኤው ምዕመናንን ከሞት ወደ ሕይወት ያሻገረበት ቀን የትንሣኤው ማሳሰቢያ ነው። (ከሣቴ ብርሃን ተሰማ የአማርኛ መዝገበ ቃላት ገጽ ፻፶) መሻገር በዕብራይስጥ ፓሳሕ ከሚባለው ቃል ይመሳሰላል ትርጉሙም ፋሲካ መሻገር ማለፍ የሚል ትርጉም ይሰጣል። ሁላችን እንደምናውቀው እስራኤላውያን ከሚያክብሯቸው አበይት በዓላት አንዱም ፋሲካ ነው። ምክንያታቸው ደግሞ እግዚአብሔር ከሞተ በኩር ያሳለፋቸውን ዕለት ያስቡበታል። ቤተክርስቲያናችንም ይህንን በዓለ ትንሣኤን የፋሲካ በዓል የማክበሯ ምሥጢር ወይም የትንሣኤው ምሥጢር ነፍሳት በአምላካችን ትንሣኤ ከሞት ወደ ሕይወት ፣ ከአሳር ወደ ክብር ፣ ከሲዖል ወደ ገነት መሻገራቸውን በማሰብ አማናዊው ፋሲካ ወይም አሸጋጋሪው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ብላ ታምናለች። እናምናለን። ቅዱስ ጳውሎስ በብሉይ ኪዳን በታረደው የፋሲካ በግ (ዘዳ፲፮:፮) ምትክ አማናዊው ክርስቶስ እንደታረደልን እና ሞት ላያገኘን በሕይወት ለሕይወት እንዳሸጋገረን ሲገልጥ እንዲህ ብሏል:-"" እንግዲህ ያለ እርሾ እንዳላችሁ አዲሱን ሊጥ ትሆኑ ዘንድ አሮጌውን እርሾ አስወግዱ። ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና፤" (፩ ቆሮ ፭:፯) ቅዱስ ጳውሎስ ስለ እርሾም ሆነ ስለ አዲሱ ሊጥ በምሳሌ የሚነግረን እስራኤላውያን የእግዚአብሔርን ፋሲካ ሲያከብሩ ያደርጉት የነበረ ስርዓትን ነው። ይኸውም ፋሲካን ያከበሩት ገና ከነጻነት በፊት ነው። ምክንያቱ ደግሞ ከላይ እንዳየነው ከሞተ በኩር መቅሰፍት ለመዳን እና ከእግዚአብሔር ፍርድ ለመዳን ነበር። በአዲስ ኪዳንም ያለን ክርስቲያኖች በተለይ ይህንን ዕለት ወይም ማእዶትን ስናስብ አምላካችን ከሞት ወደ ሕይወት እንዳሻገረን ፣ ከአሳር ወደ ክብር እንዳሳለፈን ፣ ከድካም ወደ ኃይል እንዳሻገረን ፣ ሁላችን ወደ መንግሥተ ሰማያት ፋሲካችን በሆነው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተሸጋገርን በማመን ሊሆን ይገባል። የፋሲካው ጌታ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሞት ላይ እንድንዘባበትበት ሞትን ፣ ፍርሃትን ፣ ጭንቀትን ፣ ተስፋ መቁረጥን ፣ ሐዘንን ፣ ለቅሶን ፣ ትካዜን ፣ ድካምን ፣ ሥጋትን እና መቃብርን ሁሉ አጥፍቶ አሻግሮናል። ክብር ማዕዶታችን ለሆነ ለእርሱ ይሁን። አሜን ክብር ይግባውና አምላካችን የሰው ልጅ ሞትን እንዲሻገር ሁለት ነገሮች(እምነት እና ምግባር ) እንደሚያስፈልጉት በመዋለ ስብከቱ እንዲህ ሲል አስተምሮናል:- "እውነት እውነት እላችኋለሁ ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሙታን የእግዚአብሔርን ልጅ ድምፅ የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል እርሱም አሁን ነው፤ የሚሰሙትም በሕይወት ይኖራሉ።" (ዮሐ፭:፳፬-፳፭) ሊቁ ቅዱስ ያሬድም ዕለቷ ፋሲካ እንደሆነችና እንደሰትባት ዘንድ የተገባች እንደሆነች እንዲህ ሲል በመዝሙሩ አዚሞታል:- " ፋሲካ ዛቲ ዕለት ቅድስት ይእቲ (ይህቺ የፋሲካ ዕለት ልዩ ናት) ፣ ዛቲ ዕለት ንትፈሳሕ በቲ (በዚህ ዕለት ሐሴት እናድርግባት)..." @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
1
10
የመጽሐፍ ግብዣ ርዕስ = Thine is the power ጸሐፊ = H.H pope shiouda lll (ቅዱስነታቸው ብጹዕ አቡነ ሽኖዳ ፫ኛ) የገፅ ብዛት = ፷(60) ብቻ😁 ስለ መጽሐፉ ይዘት መጽሐፉ በግብፅ ያለችው እኅት ቤተክርስቲያናችን በሰሙነ ሕማማት ያላትን ስርዓተ አምልኮ የሚያሳይ ሲሆን ነገርግን በጥንቷ ቤተክርስቲያን ያሉ ምእመናን የሰሙነ ሕማማትን እንዴት ያሳልፉ እንደነበርም ያትታል። በግብፅ ባለችው ቤተክርስቲያናችን በሰሙነ ሕማማት ጊዜ የሚባለውን "Thine is the power the glory" በአገራችን ባለችው ቤተክርስቲያናችን ደግሞ "ለከ ይደሉ ኃይል ወስብሐት ወለከ ይደሉ አኮቴት..." የሚባለውን ምስጋና  በስግደታችን ጊዜ የምንለውን በግሩም ሁኔታ የሚያብራራ እንዲሁም የጌታችን መሰቀል የሚያሳየው ደካማነቱን ወይስ ብርቱ ኃይለኛ መሆኑን ነው? የሚለውን ወሳኝ ጥያቄ የሚያብራራ እንዲሁም በሰሙነ ሕማማት በስግደታችን ጊዜ የምንለው ይህ ቃል ከመስቀሉ ጋ አያይዞ የሚተነትን ድንቅ መጽሐፍነው።
700
11
የአልዓዛር ቅዳሜ ጌታ የሚወደው የቢታንያው ወዳጅ አልዓዛር ታመመ፤ እኅቶቹ ማርታና ማርያም ወደ ኢየሱስ "የምትወደው ወዳጅህ ታሟል" ብለው ቢልኩበትም ኢየሱስ ግን የመሰቀያው ጊዜ መድረሱን አውቋልና ኾን ብሎ ዘገየ፤ አልዓዛርም ሞተ። የክርስቶስ መሰቀያ ጊዜ እና የአልዓዛር ሞት ምን አገናኘው? የተገናኘው የካህናት አለቆች ጌታን ይገድሉት ዘንድ የተማከሩት አልዓዛርን በማስነሣቱ ምክንያት ነውና ሊቀ ካህናቱ ቀያፋ "ሕዝቡ ኹሉ ከሚጠፋ ስለ ሕዝቡ አንድ ሰው ቢሞት ይሻለናል" ብሎ የተናገረው አልዓዛርን ካስነሣው በኋላ ሕዝቡ ኹሉ ስለተከተለው ነው። (ዮሐ 11፡50) በነጋታው ሕዝቡ ኹሉ ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እያለ የተከተለውም ትልቁ ምክንያት አልዓዛርን በማስነሣቱ ነው። አልዓዛርን ማስነሣት ለምን እንዲህ ትልቅ ነገር ኾነ? ጌታ ከእርሱ በፊት እኮ 2 ሰዎችን አስነሥቷል፤ ምነው የአልዓዛር ተጋነነ? ከዚህ በፊት ጌታ ያስነሳቸው ሰዎች በሞቱበት ቀን ነው። አይሁድ ደግሞ በአስተምህሮዋቸው አንድ ሰው ሲሞት ነፍሱ ከሥጋው ትለይና ምናልባት የመመለስ እድል ካገኘው ብላ ከሥጋዋ አከባቢ ለ3 ቀናት ታንዣብባለች፤ ለ3 ቀን ካልተመለሰች ተስፋ ትቆርጥና ወደ ማደሪያዋ ትገባለች ስለዚህ በ3ኛው ቀን ሰው ላይነሣ ፈጽሞ ሞተ ይባላል። ጌታም አልዓዛር ሞተ ብለው እኅቶቹ ሲልኩበት የዘገየበት ምክንያት የእግዚአብሔር ክብር ይገለጥ ዘንድ "ትንሣኤ እና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝም ቢሞት እንኳን ይነሣል" በማለቱ የሰው ልጅ ፈጽሞ ከሞተ በኋላ እንኳን የሚያስነሣ እርሱ መኾኑ ለሕዝቡ ኹሉ ይገለጥ ዘንድ ነው። (ዮሐ 11፡25) ስለዚህም ጌታ ወደ ቢታንያ ሲደርስ አልዓዛር ከሞተ 4 ቀን ኾኖት ነበር፤ አይሁድም ፈጽሞ መሞቱን ስላመኑ ከዚህ በኋላ ይነሣል የሚል ተስፋ እንኳን አልነበራቸውም። እንኳን አይሁድ በኢየሱስ ያመኑ እኅቶቹ ማርታ እና ማርያም እንኳን ጌታ መቃብሩን ክፈቱልኝ ባለ ጊዜ "አራት ቀን ኾኖታል ይሸታል" ብለው ታቀወሙ ፤ ትንሣኤ እና ሕይወት ክርስቶስ ግን "አልዓዛር ፣ አልዓዛር ና ውጣ" በሚል ቃል ብቻ ፈጽሞ የሞተውን አልዓዛር ከመቃብር ከነመግነዙ አወጣው ፤ ትንሣኤ እና ሕይወት እርሱ መኾኑ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ሆሳዕና (አዳኝ) እርሱ መኾኑም በዛ ላለ ሕዝብ ኹሉ ተገለጠ። የአልዓዛር ከሙታን መነሣት በቢታንያ እና በኢየሩሳሌም ምድር ኹሉ ተሰማ ሕዝቡ ኹሉም የተነሣውን አልዓዛርን ያዩ ዘንድ ወደ ቢታንያ ተሰበሰቡ ያስነሣውን ሆሳዕና (አዳኝ) ያዩ ዘንድም ናፈቁ፤ ኢየሱስ ግን ወደ ኤፍራታ ከተማ ትቶአቸው ሄዶ ነበር (ዮሐ 11፡54)። ነገር ግን ለረጅም ጊዜ አይደለም ለአንድ ቀን ብቻ ነው እንጂ፤ በነጋታው ይመጣል! ሕዝቡ ኹሉም የናፈቁትን ሆሳዕና (አዳኝ) በዘንባባ ይቀበሉታል!
656
12
✝️የ ዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 21📌🌹 ኢየሱስ፡ስምዖን፡ጴጥሮስን፦የዮና፡ልጅ፡ስምዖን፡ሆይ፥ከነዚህ፡ይልቅ፡ ትወደኛለኽን፧አለው፦አዎን፡ጌታ፡ሆይ፥እንድወድኽ፡አንተ፡ታውቃለኽ፡አለው፦ግልገሎቼን፡አሰማራ፡ አለ+3
✝️የ ዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 21📌🌹 ኢየሱስ፡ስምዖን፡ጴጥሮስን፦የዮና፡ልጅ፡ስምዖን፡ሆይ፥ከነዚህ፡ይልቅ፡ ትወደኛለኽን፧አለው፦አዎን፡ጌታ፡ሆይ፥እንድወድኽ፡አንተ፡ታውቃለኽ፡አለው፦ግልገሎቼን፡አሰማራ፡ አለው። ፤ደግሞ፡ኹለተኛ፦የዮና፡ልጅ፡ስምዖን፡ሆይ፥ትወደኛለኽን፧አለው፦አዎን፡ጌታ፡ሆይ፥እንድወድኽ፡ አንተ፡ታውቃለኽ፡አለው፦ጠቦቶቼን፡ጠብቅ፡አለው
625
13
📌✨🌹የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 20 ፤ኢየሱስም፦ማርያም፡አላት።ርሷ፡ዘወር፡ብላ፡በዕብራይስጥ፦ረቡኒ፡አለችው፤ትርጓሜውም፦መምህር፡ ሆይ፡ማለት፡ነው። ኢየሱስም፦ገና፡ወደ፡አባቴ፡አላረግኹምና፡አትንኪኝ፤ነገር፡+3
📌✨🌹የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 20 ፤ኢየሱስም፦ማርያም፡አላት።ርሷ፡ዘወር፡ብላ፡በዕብራይስጥ፦ረቡኒ፡አለችው፤ትርጓሜውም፦መምህር፡ ሆይ፡ማለት፡ነው። ኢየሱስም፦ገና፡ወደ፡አባቴ፡አላረግኹምና፡አትንኪኝ፤ነገር፡ግን፥ወደ፡ወንድሞቼ፡ኼደሽ፦እኔ፡ወደ፡ አባቴና፡ወደ፡አባታችኹ፡ወደ፡አምላኬና፡ወደ፡አምላካችኹ፡ዐርጋለኹ፡ብለሽ፡ንገሪያቸው፡አላት።
701
14
የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 19📌🌸🌸🌹 🌸ኢየሱስ እንዲሰቀል ተፈረደበት 🌸የኢየሱስ ስቅለት 🌸አንቺ ሴት እነሆ ልጅሽ አላት 🌸የኢየሱስ መሞት 🌸የኢየሱስ መቀበር+3
የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 19📌🌸🌸🌹 🌸ኢየሱስ እንዲሰቀል ተፈረደበት 🌸የኢየሱስ ስቅለት 🌸አንቺ ሴት እነሆ ልጅሽ አላት 🌸የኢየሱስ መሞት 🌸የኢየሱስ መቀበር
473
15
✨📌📌የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 18 🌹📚✝️+3
✨📌📌የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 18 🌹📚✝️
478
16
የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 17 📚🌹💫+2
የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 17 📚🌹💫
439
17
📚📚📌የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 16✨✨ 🌸የመንፈስ ቅዱስ ሥራ 🌸ወደላከኝ አእብ እሄዳለሁ 🌸ለምኑ ትቀበላላችሁም+3
📚📚📌የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 16✨✨ 🌸የመንፈስ ቅዱስ ሥራ 🌸ወደላከኝ አእብ እሄዳለሁ 🌸ለምኑ ትቀበላላችሁም
436
18
6 ገብርኄር.pdf
429
19
የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 15+2
የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 15
412
20
ታላቁ ጎርጎርዮስ እኔ እንደ ወደድኋችሁ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትእዛዜ ይህች ናት።ዮሐንስ 15፡12 ሁሉም የጌታችን የተቀደሱ ንግግሮች በትእዛዛቱ የተሞሉ ሲሆኑ፣ ለምን ፍቅርን በተመለከተ ይህን ልዩ ትዕዛዝ ይሰጣል? ሁሉም ትምህርቶቹ ስለ ፍቅር ስለሆኑ እና ትእዛዛትም ሁሉ በፍቅር ስለሚጠቀለሉ አይደለምን? ፍቅር የትእዛዝ ሁሉ ፍጻሜ ነው። የዛፍ ቅርንጫፎች ሁሉ ከአንድ ሥር እንደሚወጡ ሁሉ በጎነትም ሁሉ ከአንድ ፍቅር ይገኛሉ፤ ቅርንጫፉም ማለትም በጎ ሥራ፣ በፍቅር ሥር ውስጥ ከሌለ በቀር ሕይወት የለውም። ከፍተኛው ፣ ብቸኛው የፍቅር ማረጋገጫ ፣ ጠላታችንን መውደድ ነው ። እውነት እርሱም ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ ለአሳዳጆቹ ያለውን ፍቅር አሳይቷል፡ አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው (ሉቃስ 23፡34)። ስለዚህ ፍቅርም ክርስቶስ እንዲህ ሲል ተናግሯል። " በእውነት ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት የበለጠ ፍቅር ለማንም የለውም"። ጌታችን የመጣው ለጠላቶቹ ሊሞት ነው።ሮሜ 5፤10 ነገር ግን እርሱ ስለ ወዳጆቹ ነፍሱን አሳልፎ እንደሚሰጥ ተናግሯል። በመውደድ ጠላቶቻችንን ማሸነፍ እንደምንችል እና እኛን የሚያሳድዱ ወዳጆቻችን እንደሚሆኑ አሳየን። ነገር ግን በሰላም ጊዜ ጊዜውን ለእግዚአብሔር አሳልፎ የማይሰጥ ሁሉ በመከራ ነፍሱን እንዴት አሳልፎ ይሰጣል? እንግዲህ በመከራ ውስጥ የሚያሸንፍ የፍቅር በጎነት በመልካም ሥራ በሰላም ጊዜ እናዳብር። የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቅ በትክክል ወዳጁ ተብሎ ይጠራል። የምንሰማውን ሰማያዊ ነገር ስንወድ በፍቅር እናውቀዋለን።ምክንያቱም ፍቅር ራሱ እውቀት ነውና። ከምድራዊ ምኞት ስንርቅ በመለኮታዊ ፍቅር እሳት ስንቃጠል ያን ጊዜ ሁሉን ነገር እናውቅ ዘንድ እግዚአብሔር ይገልጥልናል። ነገር ግን የእግዚአብሔር ወዳጅ የመባልን ክብር ያገኘ ማንም ሰው ይህን ከሰው በላይ የሆነ ስጦታ ለራሱ ጥቅም አይለውጠው፡ "እኔ መረጥኩህ እንጂ አንተ አልመረጥከኝም" ዮሐ 15፤16። በፈቃድ እንድትሄዱ በጸጋ ተከልኋችሁ፤ በነጻ ፈቃዳችሁ እንድትሄዱና በመልካም ሥራ ፍሬ እንድታፈሩ ። ምን ዓይነት ፍሬ ማፍራት እንዳለብንም " አብም በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ እንዲሰጣችሁ፥ ልትሄዱና ፍሬ ልታፈሩ ፍሬአችሁም ሊኖር ሾምኋችሁ።" ብሏል።ዮሐ 15፤16 ምድራዊ ሥራ ዘላቂ ፍሬ አያፈራምና፤ ቢያፈራም ሞት በመጨረሻ ይመጣልና ሁሉንም ያሳጣል። ነገር ግን የመንፈሳዊ ድካማችን ፍሬ ከሞት በኋላ እንኳን ይኖራል። እናም የሥጋዊ ድካማችን ውጤት መጥፋት በሚጀምርበት ጊዜ መታየት ይጀምራል። እንግዲያውስ ሞት የማያጠፋቸውን ዘላለማዊ ፍሬዎች እናፍራ።
367