en
Feedback
ቃለ ዐዋዲ አዳማ አጥቢያ

ቃለ ዐዋዲ አዳማ አጥቢያ

Open in Telegram

“ጌታ ቅርብ ነው። ይህ የውሉደ ብርሃን አዳማ አጥቢያ የሚድያ አገልግሎት ነው። አገልግሎቱን መደገፍ ለምትፈልጉ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000652067097 በብርሃን ባንክ 1600080066739 (W.B.Y) Wulude Birhan Yekirstos Betekrstian Adama Atbiya

Show more
411
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-330 days
Posts Archive
መሀል መሆን ሲያምርብህ ከፍ ከፍ ላርግህ ስምህ መልካም መአዛ እርሱ ብቻ የማይሞት እውነት ያለህ ከአለቅነት በላይ ካህኔ ሊቀ ካህኔ ዘላለም የምትኖር አልፋ ነህ በሰማይ ያለህ

አልፋ ነህ አልፋ ነህ መጀመርያዬ ኦሜጋ ነህ መጨረሻዬ የአዲስ ኪዳን መካከለኛ ኢየሱስ ነህ የኔ መዳኛ ሜዳ አርገኸው የለም ሸለቆ ኮርቷል ልቤ ስምህን ታጥቆ የጠጣሁህ የአለቱ ውሃ ማረፊያዬ የአይኔ ፍስሃ      በመስቀል ላይ የሞትክልኝ      እየቆሰልክ የፈወስከኝ      መስኪን ሳለሁ ገና ደካማ      ውደኸኛል መህረትህ ቀድማ አንድ ብሎ አይቆጠርም እስከ ብሎ አይገደብም ዘመን እድም የማይለካ ታርደህልኝ ሆኗል ፋሲካ        በድንግዝግዝ እያሰብኩህ        በግልጥ ነው ዛሬ ያየሁህ        ማዳንህን እሰብከዋለሁ        ለዘላለም አመልክሃለሁ ፍቅር ደምቆ ታውጇል በአለም ተጽፎበት በደመህ ቀለም ተምረናል ማድረግ ይቅርታ ተሸንፈህ ሁሉን ስትረታ        ይኸው ቅኔ አዲስ ዝማሬ        ንግስናዬ አንተ ነህ ክብሬ        እወድሃለሁ ታውቃለህ ጌታ        ስለዳንኩኝ በአንተ ውለታ አይታወቅ የአንተ መነሻ አይደረስ ያንተ መድረሻ የጅማሬ ፈጻሚ ዋልታ   የፍጻሜ ጀማሪ ጌታ           ከዘላለም ድንበር በኋላ           የዘመንህ ቁጥር አይሞላ           ይቀጥላል መንግሰት ጸንቶ           በምስጋና በክብር ሞልቶ

ከአለቅነት በላይ ከአለቅነት በላይ ከጌትነት በላይ ከሚጠራው ከስም ሁሉ በላይ ይበልጣል ስልጣኑ ያለፈው በሰማይ ኢየሱስ ያለፈው በሰማይ ዙፋኑት ቢሆኑም ወይም ጌትነት አለቅነትና ሀይላት ስልጣናት በላይ በሰማያት በየብስ ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋል በከበረ ቃሉ ኢየሱስ /2/ ክርስቶስ ከፍ ይበል የማእዘኑ ራስ ከፍጥረታት በፊት ቀድሞ የነበረው ስጋ የሆነው ቃል እርሱ እግዚአብሔር ነው ሁሉ በእርሱ ከእርሱ ለእርሱ ተፈጥረዋል ግኡዛን በድምጹ ሔያዋን ሆነዋል ኢየሱስ /2/ ክርስቶስ   ከፍ ይበል የማእዘኑ ራስ ከስም ሁሉ በላይ ስም የተሰጠው ሞትን በሞት ገድሎ በአብ ቀኝ ያለው ጠላቶችን ሁሉ ከእግሩ ስር ያስገዛ የፍጥረቱ ናፍቆት የትውሉዱ ቤዛ ኢየሱስ /2/ ክርስቶስ   ከፍ ይበል የማእዘኑ ራስ አለቅነትና ስልጣናትን ገፎ የመውጊያውን ብረት ሞትን አሸንፎ የብርታቱ ጉልበት ይታያል በግርማ በላይ በሰማያት በጽዮን ከተማ ኢየሱስ /2/ ክርስቶስ   ከፍ ይበል የማእዘኑ ራስ

ስምህ መልካም መዓዛ ደምህ የሚምር ቤዛ ኢየሱስ አሜን ተቀደስ ኢየሱስ ዘላለም ንገስ ከጥላቴ ወረዳ ጭንቅ ሆኗል ከርሱ ዘንዳ በኢየሱስ ስም ብዬበት ተቃጥሏል እሳት ወርዶበት ደናግል የወደዱህ በፍቅር የለመዱህ ማር ነህ የማር ወለላ ስምህ ጣፋጭ ነው ሚበላ በእረፍት ላይ ነኝ ዛሬ ስምህ ቃኝቶኝ ዝማሬ በለምለሙ ነው መስኬ በአንተ ታድሶ ታሪኬ ነፍሴ ለባለቤቷ ተሰቷል ሰገነቷ ማንንም አላነግስም ታትሟል በኢየሱስ ስም

ከፍ ከፍ ላድርግህ      ከፍ ከፍ ላድርግህ ከፍ ከፍ በል      ሕይወት ሰጥተኸኛል ሞተህ በመስቀል      እንዴት ዝም እላለሁ እያየሁ ፍቅርህን      ለዓለም አውጃለሁ ዛሬም ውለታህን ጀርባህን አየሁት ጅራፍ አቁስሎታል እጅና እግርህን ችንካር ወጥሮታል ከጎንህ ይፈሳል ደምና ውኃው ልቤን አስለቀሰው ፍቅርህ ኃያል ነው      የሾህ አክሊል ከራስህ ላይ ያለው      የእውነተኛ ፍቅር ምስክር ነው     ተስሎብኝ  ደም ያጠበው ገጽህ       አይጠፋኝም ያቃሰትከው ድምፅህ መስቀል ተሸክመህ ስትወጣ ዳገት ሲጨክኑ እያየህ የእጆችህ ፍጥረት የትዕግስትህ መጠን ጥልቀቱን  ፈልጌ እፁብ እፁብ አልኩኝ ድምፄን ከፍ አርጌ       ማን ይከፍላል የፍቅርህን ዕዳ       ስለ ነፍሱ ላየህለት ፍዳ       ትንግርት ነው ከኅሊና በላይ       ንገስልኝ በምድር በሰማይ ያ የብርሃን ፊትህ ጸዳል የሞላበት በጥፊ ተመታ ምራቅ ተተፋበት መላእክት በፍርሃት ፊትህ የሚቆሙልህ ጲላጦስ ፊት ስትቆም እንዴት ቻለው ልብህ      ከዚህ በፊት ታሪክ  አልሰማንም      ወደፊትም ዐይናችን አያይም      የክርስቶስ የማዳኑ ሥራ      ለዘላለም አያልቅም ቢወራ እረኞች የሚያደንቁህ እረኛ ነህ አንተ በደምህ ማኅተም ሰማይ ተከፈተ ከጠቢባን ጥበብ ማስተዋል በላይ ነህ ዕርቃንህን ሆነህ ጌታዬ ታምራለህ      ማን ይከፍላል የፍቅርህን ዕዳ      ስለነፍሱ ላየህለት ፍዳ      ትንግርት ነው ከኅሊና በላይ       ንገስልኝ በምድር በሰማይ

ያ ሰንበር ለኔ ነበር (2) እኔና ጅራፉ መሀል ባትግባ ጀርባህ በግርፋት ደምን ባያነባ ያ ሰንበር ለኔ ነበር (2) እንደ አሮን ያይደለ ሞት የማያሰጋው ማይለወጥ ክህነት ከፍርድ የሚያስመልጥ ለፍርደኛ ሚሆን መካከለኝነት አንተስ ያምርብሃል ደግሞም ተችሎሃል ቤዛነት ለነፍሴ በሚሻል ተስፋ ቃል ለተሻለው ኪዳን የተሻልከው ዋሴ መሀል መሆን ተችሎሃል መሀል መሆን ተገብቶሃል (2) ከሩቅ አልቀረሁም ከተራራው ግርጌ አልተከለከልኩም በደምህ ቀርቤ ማስታወስ ተስኖት አይደለም አባትህ መርሳቱ ጥፋቴን አንተ መሀል ገብተህ ባንተ ታይቼ ነው የተወው ስህተቴን መሀል መሆን ሲያምርብህ (4) ሙሴ መሀል ሆኖ ድንቅ ተከናውኗል መናንም መግቧል የሚበላ መና መሆን ግን አይችልም መናውም ያስርባል አንተኮ እንጀራ ነህ በልተው ሚድኑብህ የህይወት እንጀራ በልቼህ ተተከልኩ ተተክዬ ጸደኩ ጸድቄ ላፈራ መሀል መሆን ተችሎሃል መሀል መሆን ተገብቶሃል (2) ተጋድሞ አነበብኩት ሰንበርህ ያወራል ሃተታው ፍቅር ነው ሞትና እኔ መሀል ደምቆ የተሰመረ መለያ ድንበር ነው እኔ ላይ በነበር ጀራፉ ያረፈው ያ ሁሉ መከራ ህመም የሚያስታውስ ጠባሳ ነው እንጂ ምህረት አያወራ መሀል መሆን ተችሎሃል መሀል መሆን ተገብቶሃል (2) በኔና በሞቴ መካከል ገብተህ ነው ሞት ላይ የፎከርኩት ስላለሁ አይደለም ስላለህልኝ ነው በህይወት ነኝ ያልኩት ሰማይ የቀረበኝ ዝቅ ብሎ አይደለም ዝቅታህ ነው እንጂ ገባሁ በእምነት ያልኩት መካከለኛዬ ቀድመህ ነው ወዳጄ መሀል መሆን ሲያምርብህ (4) ከሩቅ አልቀረሁም ከተራራው ግርጌ አልተከለከልኩም በደምህ ቀርቤ መታዘዝ ለጣለኝ ታዘህ ባታስጥለኝ መብላት ላስባረረኝ በልቼህ ባይምረኝ ባትቤዠኝ ኖሮ ባትገባ ምትኬ የሞት ዜና ነበር የዛሬው ታሪኬ መሀል መሆን ተችሎሃል መሀል መሆን ተገብቶሃል (2)

በሰማይ አለኝ እኔ የሚወደድ የኔ የምለው ወዳጅ ዘመድ የአዲስኪዳን በግ አስታራቂዬ ኢየሱስ ውዴ ቀድሟል ቤዛዬ ሰላመፃዬ እየማማለደ በክፉዎች ፍርድ የተወገደ በሸላቾች ፊት ዝምታን መርጦ በግርማው አለ ሞትን ገልብጦ በፈሰሰው ደም በመጋረጃው መግባት ሆነልኝ ቀንቶኝ ኚሔጃው በደምህ ጉልበት  ሆኖልኝ ደህና መታረቂያዬ ህያው ነህና ስለኔ እራሱን የሰጠው ጌታ ኢየሱስ ነው (2) ህይወቱን ሰጠ መስቀል ላይ ሞትን እንዳላይ (2) እንደመርገም ጨርቅ ፅድቄ ተቆጥሮ ሳለ ጌታዬ ዘንድ ማን ያድነኛልይታደገኛል እያልኩ ስፈልግ ዘመድ አንድ እንኳን ጠፍቶ ፃድቅ በምድር ሁሉ ተዘፍቆ በሀጢያት ቀንበር ዘመኑ ሲደርስ የእግዚአብሔር ክንድ ከሴት ተወልዶ ሆነኝ ዘመድ መሠማሪያዬ አንደኛ በሬ ፅኑ መሸሻአለቴ ቅጥሬ ያላንት ቤዛነት አትድንም አለም ደም ካልፈሰሰ ስርየት የለም ስለኔ እራሱን የሰጠው ጌታ ኢየሱስ ነው (2) ህይወቱን ሰጠ መስቀል ላይ ሞትን እንዳላይ (2 በእግዚአብሔር ፊት ስለኔ በፅድቅ ሊታይ ጣልቃ እየገባ መተማመኛ ከለላ ወገን አለኝ የሚያብስ እንባ አቻ  የሌለው ብቸኛ ምርጫ ጌታ ኢየሱስ ነው ከሞት ማምለጫው በስጋ በኩል በመጋረጃው በኢየሱስ ሆኜ ወደአብ ገባሁ ይህ ነው እውነቱ ስማኝ ወገኔ አንዱ ሞቶልኝ ፀንቷል መዳኔ ስለኔ ዛሬም የሚማልደው ሰው የሆነው ነው በአብ ቀኝ ያለው ስለኔ ዛሬ ሚማልደው ጌታ ኢየሱስ ነው (2) አለኝ ጠበቃ በሰማይ ድካም እንዳላይ (2

እውነት ያለህ እውነት ያለህ እውነት ነህ ህይወት ምትሰጥ ተላልፈህ ያሳለፍከኝ መንገዱን አማናዊው በሬ አንተ ነህ ሌባ እንዳልባል ወንበዴ እንዳልለያይ ከውዴ አልሻም ሌላ መግቢያ በር ትበቃኛለህ የኔ ክብር መንግስትህን አልወርስ ባቋራጭ ፅድቅን አላገኝ ባማራጭ ስለኔ የምትታየውን አንተ ብቻ ነህ መግቢያው አንተ ነህ………………..ሀሰትን የጣልክ እውነት አንተ ነህ………………..ሞትን የቀደምክ እውነት አንተ ነህ………………..የተሳለጥህ መንገድህ አንተ ነህ………………..ምትገለጥ በፍርድህ ካንተ የሚሻል የቅርብ ለነፍሴ ሰንበት ወደብ ከወዴት አለህ ዘመድ ሰማይ የሚያደርስ መንገድ ጲላጦስና ሄሮድስ የታረቁብህ ቅዱስ መድኃኒት የሆንክ ሀኪም ሞተህ የበቃህ ለዓለም በአንተ ነው………………..መግባት የቻልኩት ገነት በአንተ ነው………………..ሰላም ያገኘው ዕረፍት በአንተ ነው………………..ክብር ሆነልኝ ደስታ በአንተ ነው………………..በዜማ የቆምኩ በእልልታ መጋጠሚያዬ አለቴ መሰማሪያ ወደ እረፍቴ በእኔ እና በእግ/ር ዘንድ መካከል ያለህ ዘመድ አቻ የሌለህ አንደኛ ጥልን የገደልክ ብቸኛ ስምህ የሚያድን ፈዋሺ እርቃን ተሰቅለህ ድል ነሺ አንተ ብቻ 2 ነህ………………..መቃተትህ የተሰማልህ አንተ ብቻ 2 ነህ………………..አባትህ ደስ የተሰኘብህ አንተ ብቻ 2 ነህ………………..የትውልዱን እንባ ያስቀረህ አንተ ብቻ 2 ነህ………………..ሞትን ሽረህ በሰማይ ያለህ አንተ ብቻ 2 ነህ………………..በአየር ላይ ምንቀበልህ አንተ ብቻ 2 ነህ………………..ነጭ ለብሰን ምንዘምርልህ

ዘላለም የምትኖር የሁል ጊዜ ጀግና ሞትን የተበቀልክ አንበሳ ነህና ክብር ይሁን ላንተ ምስጋና ዜማ ይሁን ላንተ ምስጋና ቅኔ ይሁን ላንተ ምስጋና ለጥቅማችን ሞተሃልና ሰባቱን ማህተም ለፈታህ የምህረት ፀሃይ ላወጣህ ዝም እንደሚል በግ ለታረድክ መዳናችንን ለፈፀምክ ጭብጨባ ቅኔ ሽብሸባ ይብዛልህ አምልኮ መባ ይነጠፍ ፊትህ ዜማችን በጽዮን ላለህ ውዳችን የፀሃይ ግለት ላይበላን ርሀብ ጥሙ ላያየን የማዳን ራስ ቁር ደፍተን የፅድቅን ፅሩር ለብሰን መከራ ጭንቁን አምልጠን ልብሳችንን በደም ተረጭተን የባረከንን ልንባርክ ተሰለፍን ደሞ ለማምለክ ኃይልና ባለጠግነት አምልኮ ጥበብ በረከት ሊቀበል ለተገባው መፅሃፉን ለከፈተው ቀንና ሌሊት ያለ ዕረፍት ቅዳሴ ስባሄ አኮቴት ነግሰህ ላለኸው በግርማ አለን ውዳሴ ውብ ዜማ በማይነጥፍ የቅኔ ጅረት በማይቆም አምልኮ ስግደት በበጉ ብርሃን ተውበን እንዘምራለን ሌት ተቀን ተላቋል ትናጋችን አይቆምም ምስጋናችን ስለኛ ታርደሃልና ይገባል ላንተ ምስጋና

ካህኔ      ካህኔ ሊቀ ካህኔ ኢየሱስ ሊቀ ካህኔ      እኔና አብ መሃል ያለኸው ወገኔ 2x እንደ አሮን ልጆች ሞት አይገድብህም እንደ ሌዋዊያን ነውር የለበህም የማይለወጥ ነው ፍፁም ክህነት በመኃላ የፀና ነውና ሹመት    ቤዛዬ ቤዛዬ ኢየሱስ ቤዛዬ    ለነፍሴ የወጣ የፅድቄ ፀሐዬ  /2x/ ልሙተልሽ ብሎ ማን ፊቴ ቀደመ ከኢየሱስ በቀር ማንለኔ ታመመ አላውቅም አይኖርም የለም ሌላ ቤዛ ጠላቱን በዋጋ ደም ከፍሎ የገዛ    አዳኜ አዳኜ ኢየሱስ አዳኜ    የሞት መድኃኒቴ የሕይወት እልፍኜ /2x/ የዚያ ክፉ እባብ የመርዙ ማርከሻ የጠጣሁ መጠጥ ፍቱን መፈወሻ በመገረፍ ቁስል በጀርባህ ላይ ሰንበር አንዴ ተሰበረ የኃጢያቴ ቀንበር    ዓለቴ ዓለቴ ኢየሱስ ዓለቴ    የተተከልኩብህ ፅኑ መሠረቴ/2x/ የሕያው አምላክ ልጅ ማለት አይደክመኝም tይሄን ስጋና ደም አልገለጠልኝም በዚህ ዓለትነት ተመስርቻለሁኝ የማዕዘኑ ራስ አግኝቼሃለውኝ    መልኅቄ መልኅቄ ኢየሱስ ምልኅቄ    ላትለቀኝ የያዝከኝ የእግዚአብሔር ልጅ ፅድቄ /2x/

እርሱ ብቻ የማይሞት ነው በብርሃን የሚኖረው በአባቱ ቀኝ አለ ነግሶ አማኑኤል ክብርን ለብሶ ትናንትናን ዛሬ ውጧል ሁሉም ነገር ይለወጣል ሳይደበዝዝ የሚያበራ ሁሌም ጽኑ የእርሱ ስራ የአይሁድ ትግል ያልነቀለው ክፋታቸው ያልሸፈነው የደም ሐውልት ምሰሶአችን በእርሱ ጸንቷል ከፍታችን የዓለም ጀግኖች ተቀብረዋል የበረቱ ተሰብረዋል ገዳዩን ሞት የገደለ እንደ ጌታ ወዴት አለ መቃብርን የቀበረ ኃይለኛውን የሰበረ ኢየሱስ ነው ፅኑ ጌታ ማይሸነፍ ማይረታ

ዘላለም የምትኖር የሁል ጊዜ ጀግና ሞትን የተበቀልክ አንበሳ ነህና ክብር ይሁን ላንተ ምስጋና ዜማ ይሁን ላንተ ምስጋና ቅኔ ይሁን ላንተ ምስጋና ለጥቅማችን ሞተሃልና ሰባቱን ማህተም ለፈታህ የምህረት ፀሃይ ላወጣህ ዝም እንደሚል በግ ለታረድክ መዳናችንን ለፈፀምክ ጭብጨባ ቅኔ ሽብሸባ ይብዛልህ አምልኮ መባ ይነጠፍ ፊትህ ዜማችን በጽዮን ላለህ ውዳችን የፀሃይ ግለት ላይበላን ርሀብ ጥሙ ላያየን የማዳን ራስ ቁር ደፍተን የፅድቅን ፅሩር ለብሰን መከራ ጭንቁን አምልጠን ልብሳችንን በደም ተረጭተን የባረከንን ልንባርክ ተሰለፍን ደሞ ለማምለክ ኃይልና ባለጠግነት አምልኮ ጥበብ በረከት ሊቀበል ለተገባው መፅሃፉን ለከፈተው ቀንና ሌሊት ያለ ዕረፍት ቅዳሴ ስባሄ አኮቴት ነግሰህ ላለኸው በግርማ አለን ውዳሴ ውብ ዜማ በማይነጥፍ የቅኔ ጅረት በማይቆም አምልኮ ስግደት በበጉ ብርሃን ተውበን እንዘምራለን ሌት ተቀን ተላቋል ትናጋችን አይቆምም ምስጋናችን ስለኛ ታርደሃልና ይገባል ላንተ ምስጋና

በሰማይ.docx0.15 KB