en
Feedback
አቃኒም

አቃኒም

Open in Telegram

@akanim ይቀላቀሉ + የኦርቶዶክሳዊያን መምህራን ትምህርቶች የሚቀርቡበት + በኦርቶዶክሳዊያን መምህራን የተጻፉ መጻሕፍት በpdf መልኩ የሚቀርብበት + አዳዲስ መጻሕፍት ሲታተሙ ቀድመን የምናሳውቅበት +, አጭር የመጽሐፍት ዳሰሳ የምናቀርብበት #ይቀላቀሉ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኝ ከሆንክ ኦርቶዶክስን ማወቅ ኦርቶዶክሳዊነትን መኖር አለብህ!!!

Show more
1 114
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1030 days
Posts Archive
Repost from N/a
ለመንፈሳዊ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ! በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ጋር በመተባበር ከሐምሌ 7, 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ወ
ለመንፈሳዊ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ! በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ጋር በመተባበር ከሐምሌ 7, 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ወራት የሚቆይ የክረምት መንፈሳዊ ኮርስና አጫጭር ሥልጠናዎች ተዘጋጅተዋል። ስለሆነም መማር የምትፈልጉ ሁሉ እስከ ሐምሌ 7 ድረስ ምዝገባ እየተካሄደ ስለሆነ በሰንበት ት/ቤቱ ጽ/ቤት እየተገኛችሁ እንድትመዘገቡ መንፈሳዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን! ➤በቋሚነት የሚሰጡ ኮርሶች ➾በአማርኛ ቋንቋ 1, ንጽጽራዊ ትምህርተ ሃይማኖት 2, ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነት(ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር) ➾በኦሮሚኛ ቋንቋ 1, ነገረ ሃይማኖት 2, ነገረ ክርስቶስ 3 ነገረ ማርያም 4, ነገረ ቅዱሳን 5, ነገረ ድኅነት ለሕጻናት ➤የፊደል ገበታ(በሦስት ቋንቋዎች በአማርኛ በኦሮሚኛ እና በእንግሊዝኛ)፤ የግእዝ ቋንቋ፤ ሥነ ሥዕልና የትምህርተ ሃይማኖት መግቢያ ይሰጣል። ይመዝገቡ! ይማሩ! “በክርስቶስም ትምህርት ለማይኖር ሰው አምላክ የለውም፤ በክርስቶስ ትምህርት ለሚኖር አብና ወልድ አሉት።” 2ዮሐ 1፥9

🔣Apple MacBook's MacBook Air (M2 chip) 2022 🔣 ⭐13.6 -inch Liquid Retina XDR display 1 billion colors ⭐8GB unified memory ⭐2
+3
🔣Apple MacBook's MacBook Air (M2 chip) 2022 🔣 ⭐13.6 -inch  Liquid Retina XDR display 1 billion colors ⭐8GB unified memory ⭐250 GB SSD storage OpenBox 140 Cycle Count 💰125,000 📱 0956382434                     Contact us

#ይሸጣል ➡️ MSI GF63 💻 Intel Core i5-10th Generation 🖥 Screen : "15.6" 📼 Storage : 256GB SSD + 1TB HDD ⏳ Ram : 16 GB 🔘GRAPHI
+2
#ይሸጣል ➡️ MSI GF63 💻 Intel Core i5-10th Generation 🖥 Screen : "15.6" 📼 Storage : 256GB SSD + 1TB HDD ⏳ Ram : 16 GB 🔘GRAPHICS: GeForce GTX 1650 4GB 💵Price -  83,000 brr        Call: 📞 0956382434                                Contact us

Repost from N/a
በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ነገረ መስቀሉ በልዩ ሁኔታ የሚታሰብበትን ሰሙነ ሕማማትን ምክንያት በማድረግ ነገረ መስቀልን ማዕከል ያደረ
በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ነገረ መስቀሉ በልዩ ሁኔታ የሚታሰብበትን ሰሙነ ሕማማትን ምክንያት በማድረግ ነገረ መስቀልን ማዕከል ያደረገ "ጉባኤ ሕማማት በደብረ ገነት" በሚል ርእስ ከሰኞ እስከ ሐሙስ ለተከታታይ አራት ቀናት የሚቆይ መንፈሳዊ ጉባኤ ተዘጋጅቷል። በመርሐ ግብሩ ላይ ➤ስግደት ➤ወንጌል ➤ነገረ መስቀሉን የሚያሳስቡ ዝማሬያት ይቀርባሉ እርስዎም የቀራንዮ ምሳሌ በሆነችው በቅድስት ቤተክርስቲያን ተገኝተው ስለነገረ መስቀሉ እንዲማሩ በክርስቶስ ፍቅር ጥሪያችንን እናስተላልፋለን! ጉባኤ ሕማማት በደብረ ገነት❤

Repost from N/a
ጥምቀትን በአዶላ ወዩ ከተማ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የበዓላት ቀኖና መሠረት ከጥር 10 ጀምሮ በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት የሚከበረው የከተራና የጥምቀት በዓል በአዶላ ከተማም ከጥር
ጥምቀትን በአዶላ ወዩ ከተማ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የበዓላት ቀኖና መሠረት ከጥር 10 ጀምሮ በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት የሚከበረው የከተራና የጥምቀት በዓል በአዶላ ከተማም ከጥር 10 ከከተራው ቀን ጀምሮ እስከ ጥር 13 በልዩ መንፈሳዊ ድምቀት ይከበራል። በከተማችን በሚከበረው የከተራና የጥምቀት በዓል የሀገረ ስብከታችን  ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ በተገኙበት የስድስቱም አድባራት ታቦታት፤ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፤ ካህናትና ዲያቆናት፤ የሰንበት ት/ቤቶች ዘማርያን፤ የበዓሉ ናታኒሞች ወጣቶች፤ የከተማችን መላው ምእመናን በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ይከበራል። ከዘጠና ዓመታት በላይ አገልግሎት በሰጠው የጥምቀት በዓል ማክበርያ ሥፍራ ላይ መቃኞ ቤተክርስቲያን መሠራቱና በብፁዕ አባታችን በአቡነ ዜና ማርቆስ ጸሎትና ቡራኬ የስድስቱም አድባራት ወደ መቃኞ ቤተክርስቲያን ገብተው ቅዳሴ ቤቱ መፈጸሙ የዘንድሮውን በዓል ልዩ ያደርገዋል። ለጥምቀት ያልሆነ..... ጥምቀትን በአዶላ!

Repost from N/a
የሥልጠና ጥሪ ለከተማችን ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች! በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከደብሩ ኦርቶዶክሳዊ ወጣቶች ማኅበር ጋር በመተባበር ከፊታችን በታላቅ ድምቀት የሚከበረውን የጥምቀ
የሥልጠና ጥሪ ለከተማችን ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች! በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከደብሩ ኦርቶዶክሳዊ ወጣቶች ማኅበር ጋር በመተባበር ከፊታችን በታላቅ ድምቀት የሚከበረውን የጥምቀት በዓል ምክንያት በማድረግ በቀን 07/05/2017 ዓ.ም ከቀኑ 11:00-12:30 ድረስ "መጽሐፍ ቅዱሳዊ የምሥጢረ ጥምቀት አስተምህሮ" በሚል ርእስ ሥልጠና ይሰጣል። በሥልጠናው ላይ ➤ምሥጢረ ጥምቀት ➤የጥምቀት ምንነት? ➤በብሉይ ኪዳን ስለጥምቀት የተነገሩ ትንቢቶችና ምሳሌያት ➤የጥምቀት መሥራች ማነው? ➤በማን ስም እንጠመቃለን? ሐዋርያት በማን ስም አጠመቁ? ➤የጥምቀት አይነቶች ➤በጥምቀት የምናገኛቸው መለኮታዊ ሥጦታዎች ➤ለጥምቀት የተወሰነ እድሜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀበት መልኮታዊ ዓላማ ምንድነው? የሚሉና ሌሎች ጥያቄዎችን የሚመለሱ ይሆናል። ስለሆነም የከተማችን ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች በሥልጠናው ላይ በመገኘት ስለምናከብረው የጥምቀት በዓል ምንነት እና የምሥጢረ ጥምቀትን ትምህርት ይማሩ መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!

Repost from N/a
በአዶላ ዋደራ ሐረንፈማ ወረዳ ቤተክህነት በዋደራ ወረዳ በዋደራ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የገናናው መልአክ የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ ከታኅሳስ 18-2
በአዶላ ዋደራ ሐረንፈማ ወረዳ ቤተክህነት በዋደራ ወረዳ በዋደራ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የገናናው መልአክ የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ ከታኅሳስ 18-20 ለተከታታይ ሦስት ቀናት መንፈሳዊ ጉባኤ ተዘጋጅቷል። በበዓሉ ላይ የሀገረ ስብከታችን ልዑካን፤ የወረዳ ቤተክህነት የሥራ ኃላፊዎች፤ የአድባራትና የገዳማት አስተዳዳሪዎች፤ መምህራነ ወንጌልና ዘማርያን ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ይከበራል። ስለሆነም እርስዎም በጉባኤውና በበዓሉ በመገኘት ከበዓሉ ረድኤት በረከት ይሳተፉ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን! የወረዳው ጽ/ቤት ከደብሩ ሰበካ ጉባኤ ጋር በመተባበር!

Repost from N/a
ታላቅ መንፈሳዊ ጥሪ! በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት አዲስ የመረጣቸውን አመራሮችን ለማስተዋወቅና የሥራ እቅዶቹኝ ለማቅረብ በቀን 13/04
ታላቅ መንፈሳዊ ጥሪ! በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት አዲስ የመረጣቸውን አመራሮችን ለማስተዋወቅና የሥራ እቅዶቹኝ ለማቅረብ በቀን 13/04/2017 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ ልዩ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል። በመርሐ ግብሩ 1, አዲሶቹ የሰንበት ትምህርት ቤቱ አመራሮች ይተዋወቃሉ። 2, ቀድመው ሲያገለግሉ ለነበሩት አመራሮች የምስጋናና ሽኚት ይደረግላቸዋል። 3, ቀጣይ ሰንበት ት/ቤቱ በልዩ ትኩረት ስለሚሠራቸው ዋና ዋና ተግባራትን በተመለከተ ገለጻና ማብራርያ ይሰጥበታል። 4, የወንጌልና የዝማሬ መርሐ ግብር ይኖራል። በዕለቱም መላው የሰንበት ት/ቤቱ አባላት፤ የደብሩ አስተዳዳሪና የሰበካ ጉባኤ ጉባኤ አባላት፤ የደብሩ ማኅበረ ካህናትና ዲያቆናት፤ በደብሩ የሚገኙ አንጋፋ ማኅበራት፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፤ ምእመናንና ምእመናት ይገኛሉ። ስለሆነም በእለቱ ሁላችሁም ተገኝታችሁ ለሰንበት ትምህርት ቤት ያላችሁን ፍቅር እንድትገልጹ መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን! የደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት

Repost from N/a
ታላቅ መንፈሳዊ ጥሪ! በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት አዲስ የመረጣቸውን አመራሮችን ለማስተዋወቅና የሥራ እቅዶቹኝ ለማቅረብ በቀን 13/04
ታላቅ መንፈሳዊ ጥሪ! በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት አዲስ የመረጣቸውን አመራሮችን ለማስተዋወቅና የሥራ እቅዶቹኝ ለማቅረብ በቀን 13/04/2017 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ ልዩ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል። በመርሐ ግብሩ 1, አዲሶቹ የሰንበት ትምህርት ቤቱ አመራሮች ይተዋወቃሉ። 2, ቀድመው ሲያገለግሉ ለነበሩት አመራሮች የምስጋናና ሽኚት ይደረግላቸዋል። 3, ቀጣይ ሰንበት ት/ቤቱ በልዩ ትኩረት ስለሚሠራቸው ዋና ዋና ተግባራትን በተመለከተ ገለጻና ማብራርያ ይሰጥበታል። 4, የወንጌልና የዝማሬ መርሐ ግብር ይኖራል። በዕለቱም መላው የሰንበት ት/ቤቱ አባላት፤ የደብሩ አስተዳዳሪና የሰበካ ጉባኤ ጉባኤ አባላት፤ የደብሩ ማኅበረ ካህናትና ዲያቆናት፤ በደብሩ የሚገኙ አንጋፋ ማኅበራት፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፤ ምእመናንና ምእመናት ይገኛሉ። ስለሆነም በእለቱ ሁላችሁም ተገኝታችሁ ለሰንበት ትምህርት ቤት ያላችሁን ፍቅር እንድትገልጹ መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን! የደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት

Repost from N/a
ታላቅ የትምህርትና የሥልጠና መርሐ ግብር በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከደብሩ ማኅበረ ሩሃማ ጋር በመተባበር ወጣቶችን እና ጎልማሶችን ማዕከል ያደረገ፤ በፕሮጀክተር የታገዘ ተከታ
ታላቅ የትምህርትና የሥልጠና መርሐ ግብር በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን  ከደብሩ  ማኅበረ ሩሃማ ጋር በመተባበር ወጣቶችን እና ጎልማሶችን  ማዕከል ያደረገ፤ በፕሮጀክተር የታገዘ ተከታታይ የነገረ ድኅነት ትምህርትና ሥልጠና ተዘጋጅቷል። ➤የትምህርት አይነት፦ ነገረ ድኅነት ➤ዕለት፦ ዘወትር እሑድ ➤ሰዓት፦ ከጠዋት ከ3:00 -4:00 ➤ ቦታ፦ በደብሩ የሰንበት ት/ቤት አዳራሽ ሁላችሁም ተጋበዛችኋል!! "የቤተክርስቲያንን ዶግማ፤ ቀኖናና ትውፊት መማርና ማወቅ የሁላችንም መንፈሳዊ ግዴታችን ነው"

Repost from N/a
ጉባኤ ቴኦቶኮስ❤
ጉባኤ ቴኦቶኮስ❤

Repost from N/a
በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በ2016 ዓ.ም የተከናወኑ ዋና ዋና የስብከተ ወንጌል አገልግሎት በጥቂቱ፦ ➤በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በዕለተ እሐዱ ከቅዳሴ በኋላ፤ በሰባቱም ወርኃዊ በዓላት እና በአጽዋማት በተለይም በዐቢይ ጾምና በፍልሠታ እና በንግሥ በዓላት ከቅዳሴ በኋላና በሰርክ መርሐግብር የወንጌል አገልግሎት ተከናውኗል። እንዲሁ በኀዘንና በደስታ አጋጣሚዎች በዐውደ ምህረት አጋጣሚውን ማዕከል ያደረጉ ትምህርቶችና ስብከቶች ተሰጥተዋል። በተጨማሪ ምእመናን መሠረታዊውን የቤተክርስቲያንን ትምህርት ይማሩ ዘንድ ➤ "አርብን በደብረ ገነት" በሚል ርእስ ዘወትር አርብ የሳምንታዊ ጉባኤ ➤ "ጉባኤ ቴኦቶኮስ" በሚል ርእስ ወር በገባ ከ21-24 ለተከታታይ አራት ቀናት የሚቆይ ወርኃዊ ጉባኤ ➤ከአዘጋጅ አካላት ጋር በመሆን ከነሐሴ 21 -26 ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በማዘጋጀት ምእመናን ወንጌል እንዲማሩ ተደርገጓል። ➪ ዓመቱን ለሦስት በመክፈል በደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር ለሶስት ዙር ያህል የኮርስ መርሐ ግብር በማዘጋጀት ወጣቶች ቤተክርስቲያንን እና አስተምህሮዋን እንዲያውቁ እንዲረዱ እና እንዲያደርጉ ተደርጓል። በዚህ ክረምትም ከበሰንበት ት/ቤት፤ የማኅበረ ሩሃማ እና በኦርቶዶክሳዊ ወጣቶች ማኅበር ጋር በመተባበር ከ70 የሚበልጡ ወጣቶችና ጎልማሶች በኮርስ መርሐ ግብሩ ላይ በመሳተፍ እየተማሩ ይገኛሉ ። ➤በደብሩ በሚሰጠው የኮርስ መርሐ ግብር ላይ ከተሳተፉት ውስጥ የተሻለ የትምህርት አቀባበልና የአገልግሎት ቅልጥፍና ያላቸውን ወጣቶች በመምረጥ የተተኪ መምህራን ኮርስ ወይም የስብከት ዘዴ በማስተማር በሀገረ ስብከታችን ሊቀጳጳስ በብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ አባታዊ መመርያና ቡራኬ 1 ካህን፤ 6ዲያቆናትና 1የሰንበት ት/ቤት ወጣት በአጠቃላይ 8 ተተኪ መምህራን ተመርቀዋል። ➤የደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤትን በትምህርትና በሥልጠና ከማጠናከር ባለፈ ሰንበት ትምህርት ቤቱ የተሻለ መተዳደሪያ ደንብ እንዲኖረው ከሰንበት ትምህርት ቤቱ ኮሚቴዎች ጋር በመሆን ደንቦችን በማርቀቅ፥ የሌሎች ሰንበት ትምህርት ቤት ደንቦችን በማስተያየት ለደብሩ የሚመጥን የተሻለ ሰንበት ት/ቤት የማድረግ ሥራ ተሠርቷል። ➤ በደብሩ ከሚገኙ ማኅበራት መካከል አንዱ ማኅበረ ሩሃማ ነው። በዚህ ማኅበር ታቅፈው ቅድስት ቤተክርስቲያንን የሚያገለግሉ ምእመናን ዘወትር እሑድ ከጠዋቱ 3:00 -4:00 የቤተክርስቲያንን ዶግማና ቀኖና መሠረት ያደረገ የቤተክርስቲያን ትምህርት እና የወንጌል አገልግሎት ተሰቷል። ➤ወጣቶች በተለያየ መንገድ ቤተክርስቲያንን ለማገልገል በደብሩ ኦርቶዶክሳዊ ወጣቶች ማኅበር በሚል ማኅበር ታቅፈው እያገለገሉ ይገኛሉ። እኚህ የቤተክርስቲያን ወጣቶች ዘወትር ዕሮብ ከ11:00- 12:30 በደብሩ አዳራሽ በመገኘት የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ እንዲያውቁና ወንጌል እንዲማሩ ተደርጓል። ➤እንዲሁም ከደብሩ ማኅበራትና ሰንበት ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር ምእመናን የቤተክርስቲያንን ዶግማ፥ቀኖና እና ትውፊት እንዲያውቁ በተለይም ወጣቶችን ማዕከል ያደረገ በፕሮጀክተር የታገዘ በየወሩ የሚዘጋጅ ሥልጠና በየወሩ ተሰጥቷል። "ስብከተ ወንጌል የቤተ ክርስቲያን ህልውና ነው፤ ለስብከተ ወንጌል ትኩረት ይሰጠው ስንል ለብተ ክርስቲያን ህልውና ትኩረት ይሰጠው ማለታችን ነው።" መጋቤ ብሉይ አእመረ አሸብር "እንዲሁ እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ። የማንጠቅም ባሪያዎች ነን፥ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል በሉ።" (የሉቃስ ወንጌል 17:10)

Repost from N/a
photo content

Repost from N/a
photo content
+2

photo content

ታላቅ የመንፈሳዊ ጉባኤ ጥሪ! በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ነሐሴ 24 ቀን በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት የሚከበረውን የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖትን ዓመታዊ ክብረ በዓልና
ታላቅ የመንፈሳዊ ጉባኤ ጥሪ! በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ነሐሴ 24 ቀን በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት የሚከበረውን የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖትን ዓመታዊ ክብረ በዓልና የደብሩን ማኅቶተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ከነሐሴ 21-26 ቀን ድረስ የሚቆይ መንፈሳዊ ጉባኤ ተዘጋጅቷል። በጉባኤው ላይ የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ፤ አንጋፋና ታላላቅ መምህራንና ዘማርያን፤ የሀገረ ስብከታችን እና የወረዳ ቤተክህነታችን የሥራ ኃላፊዎች፤ የአድባራትና የገዳማት አስተዳዳሪዎች፤ የየአድባራቱ የሰንበት ት/ቤት መዘምራን፤ ምእመናንና ምእመናት ይገኛሉ። ስለሆነም እርስዎም ከቤተሰብዎ ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመሆን ከወንጌሉ ማዕድ እንድትካፈሉ መልእክታችንን እናስተላልፋለን!

ለመንፈሳዊ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ ➾በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የደብሩ ስብከተ ወንጌል ከደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት፤ ከደብሩ ማኅበረ ሩሃማ እና ከኦርቶዶክሳዊ ወጣቶች
ለመንፈሳዊ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ ➾በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የደብሩ ስብከተ ወንጌል ከደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት፤ ከደብሩ ማኅበረ ሩሃማ እና ከኦርቶዶክሳዊ ወጣቶች ማኅበር ጋር በጋራ በመሆን የክረምት ኮርስ መርሐ ግብርና ሥርዓተ ትምህርት በማዘጋጀት መዝገባ እየተካሄደ ይገኛል። የሚሰጡ ትምህርቶች ➾ትምህርተ ሃይማኖት ➾ንጽጽራዊ ትምህርተ ሃይማኖት ➾ነገረ ቤተክርስቲያን ➾ነገረ ክርስቶስ ➾ነገረ ማርያም ➾ነገረ ቅዱሳን የትምህርቱ መርሐ ግብር ➾በርቀትና በመደበኛ ኮርሱ የሚሰጠው በሁለቱም ቋንቋ ነው። የመመዝገቢያ ቦታ፦ በደብሩ ሰ/ት/ቤት እና በደብሩ ማኅበራት ጽ/ቤት #ዓላማችን፦ መንፈሳዊ ሕይወትን ከመንፈሳዊ እውቀት ጋር አስተባብሮ የያዘ ትውልድ ማፍራት ነው።

በሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ አባታዊ መመርያ መሠረት ዛሬ በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከታኅሳስ 11 ጀምሮ ለስድስት ተከታታይ ወራት የተተኪ መምህራን
በሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ አባታዊ መመርያ መሠረት ዛሬ በአዶላ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከታኅሳስ 11 ጀምሮ ለስድስት ተከታታይ ወራት የተተኪ መምህራን ኮርስ ሲማሩ የነበሩ ተተኪ መምህራን ከቅዳሴ በኋላ በልዩ መንፈሳዊ ድምቀት በዐውደ ምህረት ተመረቁ። በምረቃው ዕለት የወረዳ ልዑካን፤ የአድባራት አስተዳዳሪዎች፤ የስብከተ ወንጌል ኃላፊዎች፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ምእመናን እና ምእመናት በልዩ ድምቀት ተገኝተዋል። በምርቃቱ ላይ ተመራቂ መምህራን በትምህርት ሂደቱ ላይ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የምሥጋና ሥጦታ የሰጡ ሲሆን የደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ት ለተተኪ መምህራንና ላስተማሩት መምህራን ሥጦታ አበርክተዋል። በዕለቱ የተመረቁ መምህራን እስከ መጨረሻው ሕቅታ ድረስ የወንጌል አገልግሎት ለማገልገል ቃል ገብተዋል። የረዳን ያገዘንን እግዚአብሔርን እያመሰገንን የተተኪ መምህራንን የትምህርት ሂደት ያገዙንን ➤የሀገረ ስብከታችንን ሊቀ ጲጳስ ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ ➤የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ➤የደብሩ ማኅቶተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት ➤ለደብሩ ማኅበረ ሩሃማ ➤ለደብሩ ኦርቶዶክሳዊ ወወጣቶች በተመረቁ መምህራን ስም እናመሰግናል!

photo content
+9