en
Feedback
ሰማያዊ ወግ (The tradition of heaven)

ሰማያዊ ወግ (The tradition of heaven)

Open in Telegram

ንጉስ ዳዊት፣ ለልጁ ሰሎሞን "በርታ ሰውም ሁን!!" እንዳለው፤ ጳውሎስም "...በማመንና በማወቅ ወደሚገኝ አንድነት ሙሉ ሰውም ወደመሆን" እንዳለው፣ ሰው ለመሆን ሰማያዊ ወጎችን እናወጋለን።

Show more
473
Subscribers
+124 hours
+27 days
+130 days
Posts Archive
የሚባርከን አንጣ። ንጉስ ሰለሞን በአባቱ በዳዊት ዙፋን በተቀመጠ ጊዜ የእግዚአብሔርን መቅደስ ሰርቶ ጨረሰ። የቃል ኪዳኑንም ታቦት ወደ መቅደስ ባስገባ ጊዜ በታቦቱ ውስጥ ከሁለቱ ከሙሴ ፅላት በቀር ሌ
የሚባርከን አንጣ። ንጉስ ሰለሞን በአባቱ በዳዊት ዙፋን በተቀመጠ ጊዜ የእግዚአብሔርን መቅደስ ሰርቶ ጨረሰ። የቃል ኪዳኑንም ታቦት ወደ መቅደስ ባስገባ ጊዜ በታቦቱ ውስጥ ከሁለቱ ከሙሴ ፅላት በቀር ሌላ አልጨመረም። በመቅደሱ የእግዚአብሔር ክብር ብቻ ነበር። ካህናቱም ከእግዚአብሔር ክብር የተነሳ መቆም አልቻሉም ነበር። ሰለሞን የእግዚአብሔርን ክብር አይቶ ተደሰተ። ጉባኤው ሁሉ እያየው ተንበርክኮ እጁን ለመዘርጋትና ህዝቡን ለመባረክ አላፈረም። ሰለሞን ጠቢብ ንጉስ ነውና፣ ህዝቡን በመባረክና ጉልበቱን በህዝቡ ፊት ለእግዚአብሔር በመስገዛት መሰከረ። የሚባርከን አንጣ!!! እኔም የሰለሞን ቡራኬ ለሁላችን ይሆን ዘንድ በእምነት እነሆ የበረከት ቃል፦ የምትፀልዩትን ፀሎት እግዚአብሔር ከሰማይ ይስማችሁ። ተበድላችሁ ተገፍታችሁ ወደ መሰውያው ስትቀርቡ እርሱ ዳኛ ይሁንላችሁ። የጨከነባችሁ መንገዱ በራሱ ላይ ይሁን። የፅድቅ ጠላት ይመታላችሁ። በአደባባይ ክበሩ። ከፅድቅ አትቆሽሹ፣ ከክብር አትጉደሉ፣ አበሳችሁን እግዚአብሔር ያንሳላችሁ፣ እድፋችሁን ያሶግድላችሁ፣ አዲስ የፅድቅ ልብስ ያልብሳችሁ። ከተተከላችሁበት ምድር አትነቀሉ፣ ስፍራችሁን በግፍ የለቀቃችሁ እንደ ያዕቆብ በክብር ተመለሱ። ሰማይ በተዘጋ ጊዜ ዝናብም ባልዘነበ ጊዜ፥ ስትፀልዩ እግዚአብሔር ከሰማይ ይስማችሁ። በርስታችሁ ላይ የእግዚአብሔር የፅድቅ ዝናብ ይዝነብላችሁ። ዘራችሁ አይጨንግፍ፣ አትጨንግፉ፣ ተከናወኑ። በምድር ላይ ራብ፥ ወይም ቸነፈር፥ ወይም ዋግ፥ ወይም አረማሞ፥ ወይም አንበጣ፥ ወይም ኩብኩባ ቢሆን፥ ወይም ጦርነት የአገሩን ቀበሌዎችን ከብቦ ቢያስጨንቃችሁ፥ መቅሠፍትና ደዌ ሁሉ ቢሆን፥ እናንተ እጃችሁን ወደ እግዚአብሔር ስትዘረጉ ይስማችሁ። ለመፍትሄ ሁኑ። ንጉስ ሰለሞን በቃል ኪዳኑ ታቦት ፊት ህዝቡን በባረከባት በረከት ተባረኩ!።

የማለፊያ ቃል። ኢየሱስ የማለፊያ ቃሌ ነው። ስሙን ጠርቼ ሁሉን የማልፍበት ማለፊያዬ ነው። ከአስጨናቂዎቼ ወደ ድል የማልፍበት ስም ነው። ከህመም ወደ ፈውስ፣ ከለቅሶ ወደ ምስጋና ማለፊያዬ ነው። ከሰይ
የማለፊያ ቃል። ኢየሱስ የማለፊያ ቃሌ ነው። ስሙን ጠርቼ ሁሉን የማልፍበት ማለፊያዬ ነው። ከአስጨናቂዎቼ ወደ ድል የማልፍበት ስም ነው። ከህመም ወደ ፈውስ፣ ከለቅሶ ወደ ምስጋና ማለፊያዬ ነው። ከሰይጣን ወጥመድ፣ አሽክላና ማሰናከያ የማልፈው በኢየሱስ ስም ነው። ከለሊት ክፉ ግርማ ከቀን ፍላፃ የማልፈው በኢየሱስ ነው። የማይታለፈውን ያለፍኩት፣ ከአጥፊው የተከለከልኩት፣ የበላሁት፣ የጠጣሁት፣ የኖርኩት በኢየሱስ ነው። አጋንንት የማይለምደው ስም ኢየሱስ ነው፣ ዛሬም ስሙ ያሳልፋል፣ ዛሬም ስሙ ሃያል ነው። አጋንንት ስሙን ሲሰሙ የሚንቀጠቀጡለት ስፍራውን ለቀስ እንዲቅበዘበዙ የሚያደርግ ስም ኢየሱስ ነው። የጨለማን ሀይል ማለፊያ የቀትር ሀሩሩን መሸሸጊያ፣ ከፊት የቆመውን ጉልበተኛ የሚጥል ቃል ኢየሱስ ነው። እናንተ የዳናችሁ ተናገሩ!!!! ልጅነታችሁን በማን አለፋችሁ? ጨለማ ከነበረው የመከራ ዘመን ወደ ብርሃን ማን አሳለፋችሁ? በፍላፃ መሃል ድንበሩን እንዴት አቋረጣችሁ? ከህመማችሁ ማን ፈወሳችሁ? የረሃቡን ዘመን ማን አሳለፋችሁ? የእባቡን እራስ በማን ሃይል እረግጣችሁ አለፋችሁ?? ክፉውን ሁሉ እየመከተ የሚያሳልፈን ኢየሱስ ነው። የማለፊያ ቃላችን ኢየሱስ ነው። ነገን የማንፈራው አስተማማኝ የማለፊያ ቃል ስላለን ነው። እንደ ቀይ ባህር ከፊት የተዘረጋ እንደ ተራራ የተገተረ ነገር ቢገጥመን በኢየሱስ ስም እናልፈዋለን። ኢየሱስ የሚለው ስም ሁሉ ይንበረከኩለት ዘንድ ስልጣን የተሰጠው ነው። ፊል 2፥10 በእምነት በዚህ ቃል እናልፋለን፦ አንተ ተራራ ምንድን ነህ? በኢየሱስ ስም ደልዳላ ትሆናለህ። አንተ ሸለቆ ምንድን ነህ? በኢየሱስ ስም ትሞላለህ፣ ጨለማውስ ምንድን ነህ? በኢየሱስ ስም ትገለጣለህ። የማለፊያ ቃላችን ኢየሱስ ነው። በዚህ ቃል ሁሉን እናልፋለን። re

ምህረቱ ለዘላለም ነውና። እግዚአብሔር ምህረት ማድረግ ይወዳል፣ ምህረትን እምቢ ብንል እንኳን እርሱ ምህረት ማድረግ ይወዳል። ምህረቱን ብንንቅ ፍርድ ይጠብቀናል ግን ፍቅር ስለሆነ ምህረትም በኛ ስራ
ምህረቱ ለዘላለም ነውና። እግዚአብሔር ምህረት ማድረግ ይወዳል፣ ምህረትን እምቢ ብንል እንኳን እርሱ ምህረት ማድረግ ይወዳል። ምህረቱን ብንንቅ ፍርድ ይጠብቀናል ግን ፍቅር ስለሆነ ምህረትም በኛ ስራ ስላልሆነ ምህረት ማድረግ አይተውም። እግዚአብሔር ስለ አባቶች ይምራል፣ ብዙ አመታት በምህረት የተቆጠሩት በኛ ሳይሆን መረዳት በቅዱሳን አባቾች ነው። ሁለት ሺ አመት ያሳለፍነው እግዚአብሔር በልጁ ባደረገልን ምህረት ነው። ነብዮ ሚክያስ ከቀድሞ ዘመን ጀምሮ ለአባቶቻችን ምለህላቸዋልና ምህረትን ታደርጋለህ ብሏል። ምህረትን እኛ ባንረዳውም እንኳን እግዚአብሔር ይረዳዋል። በምህረት መጠራት እኛ ባንፈልግ እንኳን ቤተ ክርስቲያን ትጠራበታለች፣ ቤተ ክርስቲያን እድሜዋን በምህረት ዘመን ትቆጥራለች። ቅዱሳን እርስ በእርሳቸው በምህረት ይጠራራሉ። አዲስ ዘመን በመጣ ጊዜ በምህረቱና በቸርነቱ አመታትን ተቀዳጀን ይባባላሉ። ምህረቱ ለዘላለም ነውና የተቀደሰ ስሙን እንባርካለን፣ ነፍሳችን ምስጋናውን አትረሳም። ምህረቱ ለዘላለም ነውና በደላችንን ዘወትር ይቅር ይላል፣ ደዌአችንን ይፈውሳል። ህይወታችንን ከጥፋት፣ ከታወጀብን ሞት በምህረቱ ይከልላል። ምህረቱ ለዘላለም ነውና፦ በጎ ምኞታችንን ከበረከቱ ያጠግበናል፣ ጎልማሳነታችንን ያድሳል፣ ጉልበታችን ሲደክም መንፈሳችንን ያበረታል። ምህረቱ ለዘላለም ነውና፦ ለተበደሉት ይፈርዳል፣ ግራ ለተጋቡ መንገዱን ያሳያል፣ ለሚወዳቸው የቅርብ ወዳጅ ነው፣ አላማው ፍቅር ብቻ ነው። ምህረቱ ለዘላለም ነውና፦ እንደ ሳር የሆነውን ሰው አይተወውም፣ ምህረቱን ለልጅ ልጅ ያኖራል፣ ምህረቱ ለዘላለም ነው። መዝ 103 ምህረቱ ለዘላለም ነውና እንባርከዋለን። ዙፋኑን በሰማ ያዘጋጀ፣ መንግስቱ ሁሉን የምትገዛ አመታቱን በምህረቱ ያቀዳጃችሁ፣ እንኳን እንደገና ሌላ የምህረት አመት ተጨመረላችሁ።..

ዘጸአት፣ የቅዱስ ዮሴፍ ስጦታ እግዚአብሔርን የሚወዱ ይዘምራሉ፣ ቅዱስ ዮሴፎች የተለየ አሻራና ቀለም ያሳረፉበትን ድንቅ ዝማሬ ለቤተ ክርስቲያን አበርክተዋል። ዝማሬው ከወጣ ጥቂት ወራት ያለፉ ቢሆንም
ዘጸአት፣ የቅዱስ ዮሴፍ ስጦታ እግዚአብሔርን የሚወዱ ይዘምራሉ፣ ቅዱስ ዮሴፎች የተለየ አሻራና ቀለም ያሳረፉበትን ድንቅ ዝማሬ ለቤተ ክርስቲያን አበርክተዋል። ዝማሬው ከወጣ ጥቂት ወራት ያለፉ ቢሆንም "ከፀሎቴ ስለጠበከኝ" የሚለውን ዝማሬ ስሰማ የዝማሬው ጆሮ ገብነትና የሙዚቃው ጥራት አልበሙን እንደገና እንድሰማው ገፋኝ። ለእግዚአብሔር ዝማሬን እንዲህ ተጠንቅቆ መዘመር መታደል ነው፣ የቅዱስ ዮሴፍ ዝማሬዎች በትንቢተ ሃጌ የእግዚአብሔርን ቤት ለመስራት "ወደ ተራራ ውጡ እንጨትን ቁረጡ" እንደተባለ ዝማሬን ለማቅረብ ብዙ ርቀት እንደሄዱ ያስታውቃል። "ከፀሎቴ ስለጠበከኝ" ብዙዎቻችን በመንፈስ በስጋ ፈቃድ እንፀልያለን፣ ገና በፀሎት አልበሰልንምና እንደ ህፃን የምንጠይቀውን አናውቅም፣ እናት ህፃን ልጇ የጠየቃትን ሁሉ አትሰጠውም፣ ስኳር ይጣፍጣል ብላ ስኳር ብቻ አትመግበውም፣ ትምህርት ያድክማል ብላ ከትምህርት ቤት አታስቀረውም። ህፃን ወደ ወደደው ይራመዳል እናት ግን እጁን ይዛ ትመልሰዋለች፣ ወደ ፈለገው ሳይሆን ወደሚያስፈልገው እያለቀሰም ቢሆን ትመልሰዋለች። ለኔ "ከፀሎቴ ስለጠበከኝ" የሚለው ዝማሬ መዝሙሩ ከሚለው በላይ ለልባችን ብዙ የሚናገር መዝሙር ነው። በተለይ ዜማው ይደመጣል፣ ግጥሙ ሃሳቡ ከባድ አቀራረቡ ቀላል ነው። የግጥም ውበትም ይሄ ነው። የሙዚቃ ቅንብሩ ከፍ ያለ በመሆኑ የዝማሬው ሌላ ከፍታ ነው። የክርስቲያኖች ሁሉ የዝማሬ ሞዴል፣ ቅዱስ ዳዊት እሱ ብቻ አልዘመረም "ዘምሩ ዘምሩ ለአምላካችን ዘምሩ" እያለ በዝማሬው ህዝቡን ያነሳሳ ነበር። "ዘፀአት" አልበም ብዙዎችን ለመንፈሳዊ ቅናት የሚዳርግ አልበም ነው። "መስቀልና ህይወት" ሌላው ልብ የሚሞላ ዝማሬ ነው፣ እናንተ የቅዱስ ዮሴፍ ዘማሪያን ከሰማይ የዝማሬ መስኮት ይከፈትላችሁ፣ እናንተ የዜማ እቃ የተጫወታችሁ ጥበብ ይነደልላችሁ።...

ፍልሰታ ለማርያም የምስጋና በአል ማርያም በሃገራችን፣ በብዙ ሁኔታዎች የምትጠቀስ ናት። በሃዘን ማርያም ታፅናችሁ እንላለን፦ በአንድ ወቅት አንድ እናት ወጣት ልጃቸው በመሞቱ ምክንያት መፅናናት አልቻሉ
ፍልሰታ ለማርያም የምስጋና በአል ማርያም በሃገራችን፣ በብዙ ሁኔታዎች የምትጠቀስ ናት። በሃዘን ማርያም ታፅናችሁ እንላለን፦ በአንድ ወቅት አንድ እናት ወጣት ልጃቸው በመሞቱ ምክንያት መፅናናት አልቻሉ፣ ዘወትር ያለቅሳሉ ይቆዝማሉ፣ በሀዘናቸው ጊዜ ብዙ እናቶች ማርያም ታፅናናሽ እያሉ እንደ ባህሉ ቢያፅናኗቸውም ሊፅናኑ አልቻሉም። ቤተሰብ ግራ ተጋባና ካህን ወደ ቤት ጋበዙ፣ ካህኑም "አንቺ ሌሎች ልጆች አሉሽ፣ እመቤታችን ግን የነበራት አንድ ልጅ ብቻ ነበር፣ እሱንም ያለበደሉ ገደሉባት፣ እሷ ግን በአምላኳ የታመነች በመሆኗ በሀዘን አልተሰበረችም፣ እኛም እሷን ጠርተን አፅናንተንሽ ነበር፣ ልብሽን አታደንድኚ ተፅናኚ" አሉ። እኒህ እናት ወድያው ተፅናንተው ልብሳቸውን ቀይረው ለምስጋና ወደ ቤተክርስትያን ሲሄዱ እኔ ምስክር ነበርኩ። በደስታ ማርያም በሽልም ታውጣሽ እንላለን፦ እናቶች ሲወልዱ ጥየቃ የሚሄዱ ሁሉ በማርያም ስም ይመርቃሉ፣ ከቤት ሲወጡም "ማርያም በሽልም ታውጣሽ" ብለው ይወጣሉ። ማርያም አምላክ የሆነ ልጇን ስትወልድ ሴቶች የሚያዩትን ወግ አላየችም፣ ቦታ አልነበረምና በበረት ወለደችው፣ ነገር ግን ልጇን የወለደችበት በረት ወድያው ተቀየረ፣ ከሩቅ ሀገር የመጡ ጠቢባን ወርቅ አመጡ፣ የወለደችበትን ስፍራ በከርቤ አጠኑት። በእጣን መአዛ በረቱን ቤተ መቅደስ አስመሰሉት፣ ማርያም የወለደችው በረከት ነውና በረቱን መቅደስና ቤተ መንግስትም አስመሰለችው። በካቶሊካውያን፣ በምስራቃውያንና በኦሬንታል ኦርቶዶክስ፣ በወንጌላውያን፣ በሉተራን፣ በሪፎርሚስቶች፣ በአንጀሊካን፣ በሜቶዲስቶች እና በመጥምቃውያን አመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የኢየሱስ እናት መሆኗ ይታወቃል፣ "እመ አምላክ" መሆኗ ይታወቃል። በቁራን ውስጥም ብዙ ጊዜ ከመጠቀሷም በላይ አንድ ሙሉ ምእራፍ ተፅፎላታል። እመ ብርሃን...re

ደብረ ታቦር የብርሀን በአል። ተራራው ጫፍ ላይ የጌታ ፊት አንፀባረቀ፣ ሀዋርያቱ ያዩትን በቃላት ሲገልፁ አጣቢ ሊያነፃው እንደማይችል ነጭ ነበር፣ እንደ ፀሀይ ነበር፣ እንደ መብረቅ ነበር በማለት ያዩ
ደብረ ታቦር የብርሀን በአል። ተራራው ጫፍ ላይ የጌታ ፊት አንፀባረቀ፣ ሀዋርያቱ ያዩትን በቃላት ሲገልፁ አጣቢ ሊያነፃው እንደማይችል ነጭ ነበር፣ እንደ ፀሀይ ነበር፣ እንደ መብረቅ ነበር በማለት ያዩትን መሰከሩ። በተራራው ላይ ካዩት ክብር ሌላ ሙሴና ኤልያስ ከጌታ ጋር እየሩሳሌም ስለሚጠብቀው የመስቀል ሞት ሲነጋገሩ ሀዋርያቱ ሰሙ። ጌታችን በብዙ ክብር ሲያልፍ መስቀሉን አረሳም ነበር መስቀል ላይ ለመክበር ነበር የመጣው። የኛ አዳኝ መንገዱ ሁሉ ወደ ኢየሩሳሌም የስቅለት ስፍራው ነበር። ኢየሱስ ፊሊጶስ ቂሳሪያ ወደ ሚባል አይሁድ "እንረክስበታለን" ወደሚሉት ምድር ወሰዳቸው። ቂሳሪያ እጅግ በጣኦት የተሞላች ናት። ጌታ ኢየሱስ በጣኦርት መሀል ሁኖ እኔን ማን ትሉኛላችሁ አላቸው። ስምዖን ጴጥሮስ፦ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ" አለው። ማቴ 16፥16 ኢየሱስም ይሄን የገለፀልህ አባቴ ነው አለው። "በሉ ወደ እየሩሳሌም ለመሞት እንሂድ" አላቸው፣ ጴጥሮስም "አይሁንብህ እንዲህ አታድርግ" ሲል ገሰፀው። ጌታ በምንም ሁኔታ በስቅለት እኛን ማዳኑን አረሳም። በሌላ ስፍራ ቢታኒያ በነማርያም ቤት ተገኘ፣ አሌዛርን ከሞት አስነሳው። ብዙዎች በእርሱ አመኑ። ፈሪሳውያንና ፃፎ ይሄን ሰው ማስቆም አቅቶናል፣ አለሙ ሁሉ እየተከተለው ነው አሉ፣ እርሱ ግን በመስቀል ሞቶ ሊያድነን ይችላል ነበር። ቶማስም ደንግጦ "እኛም ከእርሱ ጋር ለመሞት እንሂድ" አላቸው ወንድሞቹን። ክብር በታየበት ተራራ ሰማይ ተከፈተ፣ "የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ በተሰማበት ከፍታ፣ ሀዋርያቱ እዚሁ እንሁን እዚሁ መኖሪያ እንስራ ሲሉ እሱ እንውረድ አላቸው። እርሱ የመጣው በመስቀል ሞቶ ሊያድነን ነውና። መድሀኒታችን ኢየሱስ ሁል ጊዜ ወደ መስቀሉ ይገሰግስ ነበር። መዳናችን መስቀሉ ላይ...... Cont...

"እግዚአብሔር የሰራት ድንቅ ቀን.." ብዙዎች የኔ የሚሉት ቀን አላቸው፣ ሰዎች የማይረሱት ቀን ይኖራቸዋል። ትዳር የያዙበት ቀን፣ እንዳንዶች ከአደጋ የተረፉበትን ቀን፣ የተመረቁበት ቀን፣ ስራ የጀመሩ
"እግዚአብሔር የሰራት ድንቅ ቀን.." ብዙዎች የኔ የሚሉት ቀን አላቸው፣ ሰዎች የማይረሱት ቀን ይኖራቸዋል። ትዳር የያዙበት ቀን፣ እንዳንዶች ከአደጋ የተረፉበትን ቀን፣ የተመረቁበት ቀን፣ ስራ የጀመሩበት ቀን የህይወቴ ድንቅ ቀን ናት ይሉ ይሆናል። አንዳንዶች ደግሞ የሚወዱት ሰው በሞት የተለየበትን ቀን ይናገሩ ይሆናል። በቤተስብ ላይ የደረሰውን አደጋ የሚያስታውሱና እስከ ህመሙ የሚኖሩም ብዙ አሉ። በጓደኛና በዘመድ የተከዱ፣ በፆታቸው ጉዳት የደረሰባቸው ነገሩን አፍነው ይዘው የማይረሱት ቀን የሆነባቸው ብዙ አሉ። ንጉስ ዳዊት ብዙ ክፉና ደግ ያሳለፈ ሰው ነበር። እንደ ዳዊት በህይወቱ ውጣ ውረድ ያሳለፈ የለም፣ በቤተሰቡ የተረሳ፣ በሚያምነው ንጉስ የተከዳ፣ ሀገሩ ሁሉ ለጠላው ንጉስ ሊያስረክበው የሚፈልገው፣ በየዋሻው በሽሽት የኖረ ነበር። ግን ደግሞ በልጅነቱ አንበሳና ድብ ገሏል፣ በጦር ሜዳ ብዙዎችን ጥሏል፣ ታላቁን ጦረኛ ጎልያድን በጠጠር ገሏል፣ ልጃገረዶች በፍቅሩ ወድቀው ዘፍነውለታል። ህዝቡ የናፈቀውን የቃልኪዳን ታቦት ወደ ሀገሩ መልሷል። ከእረኝነት ተነስቶ በኬብሮንና በመላው እስራኤል ነግሷል። በንግስና ዘመኑ ብዙ ድንቅ ቀናትን አሳልፏል። ዳዊትን "በህይወትህ ድንቅ ቀን የምትለው የቱን ቀን ነው?" ብላችሁ ብትጠይቁት "ይቺ ዛሬ እግዚአብሔር የሰራት ድንቅ ቀን ናት" ። ካሳለፈው ታምራት ከሞሉባቸው ቀናት ይልቅ የዛሬዋ ቀን ዳዊት ያከብራል። እናንተ የተወደዳችሁ ሆይ፣ ያለፈ ውድቀታችሁንና ስኬታችሁን እርሱት ባለፈ ነገር ላይ አትደገፉ ዛሬ ብላችሁ ጀምሩ። እግዚአብሔር የሰራላችሁ ድንቅ ቀን ዛሬ ናት፣ ዛሬን በክብር ኑሩ፣ ነገ የእግዚአብሔር ነው፣ ሀኪሙ ክርስቶስ ሊያክማችሁ በደጅ ነው፣ እርሱ ሲያክማችሁ ዳግም ጠባሳ እንዳይኖራችሁ አድርጎ ነውና በዝች ድንቅ ቀን በድንቅ ኑሩ። ...

"እግዚአብሔር የሰራት ድንቅ ቀን.." ብዙዎች የኔ የሚሉት ቀን አላቸው፣ ሰዎች የማይረሱት ቀን ይኖራቸዋል። ትዳር የያዙበት ቀን፣ እንዳንዶች ከአደጋ የተረፉበትን ቀን፣ የተመረቁበት ቀን፣ ስራ የጀመሩ
"እግዚአብሔር የሰራት ድንቅ ቀን.." ብዙዎች የኔ የሚሉት ቀን አላቸው፣ ሰዎች የማይረሱት ቀን ይኖራቸዋል። ትዳር የያዙበት ቀን፣ እንዳንዶች ከአደጋ የተረፉበትን ቀን፣ የተመረቁበት ቀን፣ ስራ የጀመሩበት ቀን የህይወቴ ድንቅ ቀን ናት ይሉ ይሆናል። አንዳንዶች ደግሞ የሚወዱት ሰው በሞት የተለየበትን ቀን ይናገሩ ይሆናል። በቤተስብ ላይ የደረሰውን አደጋ የሚያስታውሱና እስከ ህመሙ የሚኖሩም ብዙ አሉ። በጓደኛና በዘመድ የተከዱ፣ በፆታቸው ጉዳት የደረሰባቸው ነገሩን አፍነው ይዘው የማይረሱት ቀን የሆነባቸው ብዙ አሉ። ንጉስ ዳዊት ብዙ ክፉና ደግ ያሳለፈ ሰው ነበር። እንደ ዳዊት በህይወቱ ውጣ ውረድ ያሳለፈ የለም፣ በቤተሰቡ የተረሳ፣ በሚያምነው ንጉስ የተከዳ፣ ሀገሩ ሁሉ ለጠላው ንጉስ ሊያስረክበው የሚፈልገው፣ በየዋሻው በሽሽት የኖረ ነበር። ግን ደግሞ በልጅነቱ አንበሳና ድብ ገሏል፣ በጦር ሜዳ ብዙዎችን ጥሏል፣ ታላቁን ጦረኛ ጎልያድን በጠጠር ገሏል፣ ልጃገረዶች በፍቅሩ ወድቀው ዘፍነውለታል። ህዝቡ የናፈቀውን የቃልኪዳን ታቦት ወደ ሀገሩ መልሷል። ከእረኝነት ተነስቶ በኬብሮንና በመላው እስራኤል ነግሷል። በንግስና ዘመኑ ብዙ ድንቅ ቀናትን አሳልፏል። ዳዊትን "በህይወትህ ድንቅ ቀን የምትለው የቱን ቀን ነው?" ብላችሁ ብትጠይቁት "ይቺ ዛሬ እግዚአብሔር የሰራት ድንቅ ቀን ናት" ። ካሳለፈው ታምራት ከሞሉባቸው ቀናት ይልቅ የዛሬዋ ቀን ዳዊት ያከብራል። እናንተ የተወደዳችሁ ሆይ፣ ያለፈ ውድቀታችሁንና ስኬታችሁን እርሱት ባለፈ ነገር ላይ አትደገፉ ዛሬ ብላችሁ ጀምሩ። እግዚአብሔር የሰራላችሁ ድንቅ ቀን ዛሬ ናት፣ ዛሬን በክብር ኑሩ፣ ነገ የእግዚአብሔር ነው፣ ሀኪሙ ክርስቶስ ሊያክማችሁ በደጅ ነው፣ እርሱ ሲያክማችሁ ዳግም ጠባሳ እንዳይኖራችሁ አድርጎ ነውና በዝች ድንቅ ቀን በድንቅ ኑሩ። ...

ፍልሰቷ ለማርያም!!! ጊዜው የመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ነው፣ ሀጥያት ጉልበታም ነበር፣ ሁሉ መልካም የመሰለውን እየሰራ ይኖራል። ፃድቃን ቤተመቅደስ መምጣት ትተው ቤታቸው በራቸውን የዘጉበት ዘመን ነበር
ፍልሰቷ ለማርያም!!! ጊዜው የመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ነው፣ ሀጥያት ጉልበታም ነበር፣ ሁሉ መልካም የመሰለውን እየሰራ ይኖራል። ፃድቃን ቤተመቅደስ መምጣት ትተው ቤታቸው በራቸውን የዘጉበት ዘመን ነበር። ስምኦን የተባለ ሽማግሌ የቤተ መቅደስ አገልጋይና የሸንጎ አባል ቢሆንም ወደ ቤተ መቅደስ መምጣት ተወ። የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ በግና ፍየል፣ እርግብና ዋኖስ መሸጫ ሁኗል። ገንዘብ መለዋወጫ ሀዋላ አድርገውታል። ትጉህ ፃድቅና እግዚአብሔርን የሚፈራው አረጋዊው ስምኦን ቤቱን ዘግቶ ቁጭ አለ። ቤተ መቅደስ መምጣት ቀረ። በዛ ክፉ ዘመን አንዲት ሴት ለሰዎች ሁሉ መድሀኒት የሆነውን አቅፋ ቤተ መቅደስ መድረሷን በመንፈስ ቅዱስ አወቀ፣ ከዘራውን ይዞ ዘሎ ገሰገሰ፣ ከእናቱ ማርያም "እግዚአብሔር ወልድን" ተቀብሎ አቀፈው። ሰማይን አቅፎ ሰማይን እያየ "አይኖቼ ማዳንህን አዩ፣" በማለት ሀሴት አደረገ፣ ከአምላክ እናት ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ቅዱስ ቃላት ተለዋወጠ። አረጋዊው ስምኦን ከዛ በኋላ መኖርን አልተመኘም፣ ሀጥያት በበዛበት ዘመን ቅድስት እናቱን አገኘ፣ ሰውን በሸሸበት ዘመን "አምላኩን" አገኘ። "አሁን አሰናብተኝ ከዚህ በላይ የደስታ ፍፃሜ የለም" ብሎ የምድሩን ጨርሶ ሰማይን ተመኘ። ማርያም ሆይ እናቶች ሁሉ መወደድ ይገባቸዋል፣ እንቺ ግን የበለጠ መወደድ ይገባሻል፣ በኩር የሆነውን አምላክን ላንቺ ብቻ ሳይሆን ለሁላችንም ወልደሻልና። ማርያም ሆይ ሴቶች ሁሉ መከበር ይገባቸዋል አንቺ ግን የበለጠ መከበር ይገባሻል፣ ሄዋን እናታችን ባጠፋችው ጥፋት ወንዶች በሴቶች እንዳይፈርዱ መድሀኒቱን ወልደሽ ክሰሻቸዋልና። ቤተ መቅደሱ በእንስሳት እዳሪ ጠረኑን እንዳይቀይር፣ በልጅሽ መአዛ ልትሞዪው ልጅሽን አቅፈሽ መጣሽ፣ በር የዘጉ ጌታን ለማየት እንዲመጡ ልጅሽን መቅደስ አመጣሽው... Continued..

እንደ ልቤ የሚሆንልኝ። ዳዊትን ያሰለጠነው እግዚአብሔር፣ ዳዊትን እግዚአብሔር እንዴት እንዳሰለጠነው ወንድሙ እንኳን አላወቀም፣ እግዚአብሔር ሲያስታትጥቃችሁ ትጥቃችሁን ሰው አያየውም። ትንሹ ዳዊት አን
እንደ ልቤ የሚሆንልኝ። ዳዊትን ያሰለጠነው እግዚአብሔር፣ ዳዊትን እግዚአብሔር እንዴት እንዳሰለጠነው ወንድሙ እንኳን አላወቀም፣ እግዚአብሔር ሲያስታትጥቃችሁ ትጥቃችሁን ሰው አያየውም። ትንሹ ዳዊት አንዲት ግልገል በድብ ስትነጠቅ፣ ከድብ ጋር ይተናነቃል፣ ስለ በጎቹ ከአንበሳ ጋር ይታገላል፣ የአንበሳውን ክንድ እና መንጋጋ ሰብሮ ግልገሉን ያስጥላል። ትንሹ ዳዊት ሃገሩ በጠላት እንደተወረረች ሰማ። በትሩን አንጠልጥሎ ወደ ጦር ሜዳ መሰስ አለ ታላቅ ወንድሙ "የልብህን ክፋት አውቃለሁ" አለው ዳዊት ግን በሃገሩ የመጣውን ጠላት ሊተናነቅ ቆመ። ንጉሱ ሳኦል፣ የዳዊትን ትንሽነት አየ፣ በዳዊት የሚሰራውን እግዚአብሔርን ሳተ። "ቁመቱ ከስድስት ክንድ ይበልጣል፣ የምድራችን ጀግና ነው። የናስ ቁርና፣ ጥሩር ይለብሳል፣ የናስ ብረቱ አምስት ሺ ሰቅል ነው። እግሩን በነሃስ ገንባሌ ሸፍኗል፣ ትከሻው ሰፊ ነው። ጦሩ እንደ ሸማሬ ተወርውሮ ይወጋል፣ ጦሩ ስድስት መቶ ሰቅል ሙሉ ብረት ነው" እያለ ዳዊትን ለማስፈራት ሞከረ። ንጉስ የፈራው ይህ ብረት በዳዊት አይን ጠብታ ነበርች። ብዙ ሰዎች ከፊት የሚጠብቃችሁን የብረት ተራራ አድርገውታል፣ እንደ ንጉስ ሳኦል ከፊታችሁ የቆመው የእሳት ፍላፃ ሆኖባቸዋል፣ ነገሩን እንደ ዳዊት በእግዚአብሔር ጉልበት ተመልከቱት፣ ተከምሮ የሚታያችሁ እንደ እንቧይ ካብ የሚናድ ነው፣ የነሃስ አጥር የመሰላችሁ በምስጋና የሚፈርስ ገለባ ነው። ንጉስ ሳኦል ስለ ጎልያድ ያወራው ግዙፍ ወሬ በአንዲት ጠጠር የሚጣል ነው። የጎልያድን ጭንቅላት ለመቁረጥ ዳዊት ሰይፍ መያዝ አያስፈልገውም፣ ጎልያድ አንገቱ የሚቆረጥበትን ሰይፍ ለዳዊት ይዞለታል። ጠላት በሚያሳያችሁ የጥፋት መሳሪያ እራሱ የሚጠፋበት ነው። የምንዋጋበት መሳሪያችን የኢየሱስ ስም ነውና በሰማይ ይሁን በምድር፣ ከምድርም በታች ድል አላችሁ።...

እግዚአብሔር በስራ ላይ ነው። እግዚአብሔር አዳምና ሄዋንን ፈጠረ፣ ሁለት ነበሩ፣ "ብዙ ተባዙ ምድርን ሙሏት።" ሲል የበረከትን ቃል አስቀመጠ። ከዛ ከመብዛት ማንም አላቆማቸውም። አቤል ቃየልን ሲገል፣
እግዚአብሔር በስራ ላይ ነው። እግዚአብሔር አዳምና ሄዋንን ፈጠረ፣ ሁለት ነበሩ፣ "ብዙ ተባዙ ምድርን ሙሏት።" ሲል የበረከትን ቃል አስቀመጠ። ከዛ ከመብዛት ማንም አላቆማቸውም። አቤል ቃየልን ሲገል፣ ያበቃ ይመስል ነበር፣ የባቢሎን ግንብ ሲገነባ፣ እግዚአብሔር በውሃ ምድር ሲመታ ያበቃ ይመስል ነበር፣ ግን አያበቃም አንዴ እግዚአብሔር "ተባረኩ" ብሏልና እንበዛለን። በእናንተ ላይ እግዚአብሔር ያስቀመጠው የበረከት ቃል ከመሆን ማንም አያግደውም። ሳይሳካላችሁ፣ የተመኛችሁትን ሳታገኙ፣ ከምትሄዱበት ሳትደርሱ፣ የልባችሁን መሻት ሳታገኙ ምንም አትሆኑም። እግዚአብሔር ስለናንተ በስራ ላይ ነው። በዚህ ሁሉ መከራ እግዚአብሔር ልጆቹን ያኖራል። ምግብ ይወደዳል እግዚአብሔር ግን ያበላል፣ መኖሪያ ይወደዳል እግዚአብሔር ግን ያኖራል። ጠላት ያቅዳል እግዚአብሔር ያፈርሳል። ጠላት ያውጃል እግዚአብሔር አዋጅን ይሽራል። ሰው እንዳሰበልን አንሞትም በእግዚአብሔር እንኖራለን። ሰው እንዳሰበ አይበትነንም እግዚአብሔር ይሰበስበናል። ሰው እንዳሰበ አይቀማንም እግዚአብሔር ይሰጠናል። ሰው እንዳሰበ አያጎለንም እግዚአብሔር ይሞላናል። ሰው እንዳሰበ አያስቀረንም እግዚአብሔር ያደርሰናል። ሰው እንዳሰበ አይጥለንም እግዚአብሔር ያቆመናል። ሰው እንዳሰበ አያስለቅሰንም፣ እግዚአብሔር ደስታ ይሆነናል። ሰው እንዳሰበ ባዶ አንሆንም እግዚአብሔር ይሞላናል። ሰው እንዳሰበ ተንቀን አንቀርም፣ እግዚአብሔር ማእረጋችን ነው። እግዚአብሔር እየሰራ ነው። ሰው እንዳሰበ አንረሳም፣ እግዚአብሔር በጠላታችን ፊት ገበታችንን ያዘጋጅልናል፣ ፅዋችንን ያትረፈርፈዋል፣ ምስክርነትን የሚወድ አምላክ በበረከቱ ምስክርነቱን ያፍጥንላችሁ። እግዚአብሔር መልካም ብቻ ነው፣ የእግዚአብሔር መልካምነት በፊታችሁ ያልፋል።

እኔ ግን በእግዚአብሔር ፍቅርን የሚገድል ጥላቻን የሚተክል ምነው በዛ?? ምነው ዳንኪራው ከቅዳሴው በለጠ? ምነው ጥላቻ ከፍቅር በለጠ? ምነው ክፉ ዜና ጮኸ? ምነው ሰይጣን የሚወደውን ወደድን? ምነው
እኔ ግን በእግዚአብሔር ፍቅርን የሚገድል ጥላቻን የሚተክል ምነው በዛ?? ምነው ዳንኪራው ከቅዳሴው በለጠ? ምነው ጥላቻ ከፍቅር በለጠ? ምነው ክፉ ዜና ጮኸ? ምነው ሰይጣን የሚወደውን ወደድን? ምነው የሰይጣን ፍሬ በየአደባባዩ ታየ። ጥላቻ የማን ነው? ግድያ የማን ነው? ድሃን ማፈናቀል የማን ነው? ህፃን ማሰቃየት የማን ነው? ጦርነት የማን ነው?? ፀልየን የቆመው ጦርነት ምነው ጀመረ? እናቶች ምህላ ገብተው ያስቆሙትን ጦርነት፣ ፀሎት የማያውቁ ለምን ጀመሩት? የአንተም ሰላም ለጦርነት ተጠቀምንበት። ገዳይ እያረፈ ይጀምራል። አንተ ሰላም ስትሰጠን እኛ ለጦርነት አደረግነው። ስለዝናብ ፀልይን ሰጠኸን፣ ዝናብ ስትሰጠን እንረሳሃለን፣ አንተ ያበቀለውን እህል በልተን አንተ ላይ ጠገብን። ካለ አንተ መኖር እንደማንችል እንረሳለን። እንጀራ ቆርሰን አፍችን ብናደርስ ስለረዳኸን፣ እጁ ታጥፋ የቀረችበር፣ ጥርሱ ማኘክ እንቢ ያለችው ብዙ አለ። እየተራመዱ ድንገት እግራቸው አልታዘዝ ሲላቸው እናውቃለን። ዳዊት፣ ኤርሚያስ፣ እንባቆም፣... በመከራ ጊዜ እግዚአብሔርን በሃዘን ጠይቀውታል፣ ለምን?? ይሄ ሆነ??" ብለውታል፣ ለምን ሲባል መልስ ያለው እግዚአብሔር ብቻ ነው፣ ብቸኛ መፍትሄ እግዚአብሔር ብቻ ነው፣ በሚሆንብን ወደ ሰው አቤት አንልም፣ ወደ እግዚአብሔር እንገሰግሳለን እርሱም ያከናውንልናል። እንባቆም እንዳመነው እኛም እናምነዋለን። "ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥ በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥ የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥ በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፥ እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤ በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ። ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤ እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤ በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል።" እንባ 317-19

ቃለ እግዚአብሔር። ብዙዎች በየትኛውም ጥበብ ልትለውጧቸው አትችሉም። ልጆቻችሁን የትኛውንም ሃብት መድባችሁ በአለም የታወቀ ዩኒቨርሲቲ ብታስተምሯቸው መለወጥ አይችሉም። መፅሀፍ ቅዱስ ሁለንተናን ይለውጣ
ቃለ እግዚአብሔር። ብዙዎች በየትኛውም ጥበብ ልትለውጧቸው አትችሉም። ልጆቻችሁን የትኛውንም ሃብት መድባችሁ በአለም የታወቀ ዩኒቨርሲቲ ብታስተምሯቸው መለወጥ አይችሉም። መፅሀፍ ቅዱስ ሁለንተናን ይለውጣል። መፅሀፍ ቅዱስ ፈልጎ ያገኛችኋል። ለመፅሀፍ ቅዱስ ፍቅር የነበራት፣ ከቦርሳዋ መፅሀፍ ቅዱስ ጠፍቶ የማያውቅ በብዛት ቅዱሱን መፅሀፍ ስታነብ የምትታይ አንዲት ሴት፣ መፅሀፍ ቅዱሱን እንዴት እንደምታነብና እንደምትወድ ስትጠየቅ። "እኔኮ መፅሀፍ ቅዱስ አላነብም እሱ ያነበኛል፣ እኔ መፅሀፍ ቅዱስን አላፈቅርም፣ ቃሉን ሳነብ መፈቀሬን እረዳልሁ እንጂ" ስትል መልሳ ነበር። እውነት ነው፣ መፅሀፍ ቅዱስ እርሱ እራሱ መስታወት ነው። እራሳችንን ያሳየናል፣ እንደመታጠቢያ ቤት መስታወት ጉድፋችንን እንድናስወግድ ገበናችንን ሸፍኖ ያሳየናል። ሁሉ እንደ ሀዘኑ የሚፅናናበት፣ ሁሉ እንደ ድክመቱ የሚበረታበት፣ ሁሉ ከእንቅልፉ የሚነቃበት ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል ነው። ቅዱስ አውጎስጢኖስ በስካርና በዝሙት ከኖረበት ህይወት ወደ ቅድስና የመጣው መፅሀፍ ቅዱስ አንብቦ ነው። በአግባብ ተመላለሱ። በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን፤ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት" የሚለውን ክፍል አነበበ ተቀድሶ ቀረ። ሮሜ 13 ታዋቂው የወንጌል ሰባኪ ኒክ ክሩዝ ትንቢተ ኢሳያስ ወደ እኔ ተመልከቱና ዳኑ የሚለውን አነበበ፣ ከውንብድና ህይወቱ ተለወጠ። ጆን ኒውተን በከባድ ሃጥያት ደስታ በማጣት የሚኖር ሰው ነበር፣ በባሪያ ንግድ የተሳተፈ ነበር። በባህር ጉዞ እያለ በሃዘን ወደ እግዚአብሔር ጮኸ፣ እግዚአብሔር እራራለት መፅሀፍ ቅዱስን አነበበ ሁላችን የምናውቀውን "Amazing Grace" የተባለውን መዝሙር ፃፈ። የእግዚአብሔር ቃል የሚያነቡትን ይለውጣል እምነታቸውን ያሳድጋል፣ ልባቸውን ያሳድጋል።...

መኖሪያችን ክፉ በሆነ መንገድ በየምሽት ክለቡ የሙዚቃ ስራ እሰራ ነበር፣ የምኖረውም በዚህ ሙያ ነው፣ በዚሁ ሙያዬ ስራዎችን ለማቅረብ ከባንዶች ጋር አሜሪካ ገባን፣ ህይወቴን የሚቀይርበት እድል አገፕሁ
መኖሪያችን ክፉ በሆነ መንገድ በየምሽት ክለቡ የሙዚቃ ስራ እሰራ ነበር፣ የምኖረውም በዚህ ሙያ ነው፣ በዚሁ ሙያዬ ስራዎችን ለማቅረብ ከባንዶች ጋር አሜሪካ ገባን፣ ህይወቴን የሚቀይርበት እድል አገፕሁ። አሜሪካ ገብተን ሆቴል እንደያዝን በመጀመሪያው ቀን እንቅልፍ አጣው፣ "መሞቻህ ነው" የሚል ድምፅ ሰማሁ፣ ሳልተኛ ነጋ። በፍጥነት ወደ ፕሮሞተሩ አቀናሁ፣ ከዚህ በኋላ ከሙዚቃ ቡድኑ መውጣቴን ነገርኩት፣ በጣም ተገረመ "ምን እያልክ ነው፣ አንተን የሚተካ ሰው የለም፣ ይሄን ስራ ጨርሰህ ታቆማለህ" አለኝ። "በጭራሽ" አልኩት። በጣም ተገርሞ አየኝ "ይሄን እድል አታበላሽ" ታምሜ መሰለው። "በደህናህ አይመስለኝም፣ ምን ትበላለህ፣ በምን ትኖራለህ?" አለኝ። እግዚአብሔር በአፌ ያስቀመጠውን ቃል ተናገርኩ። "መኖሪያዬ የዘላለም አምላክ ነው" አልኩት። በዛው ቀን የት እንደምሄድ ሳላውቅ ከሆቴሉ ወጣሁ፣ በማላውቀው ሃገር ሁሉን ትቼ ወደ መንገድ ዳር ወጣሁ። ከዛ በኋላ እንዴት እንደሆነ በማላውቀው ሁኔታ ሁሉን ነገር እግዚአብሔር አዘጋጅቶልኝ ነበር። በጥቂት ቀን ውስጥ ካናዳ በሚገኝ ታዋቂ ቤተክርስቲያን ትልቅ የሙዚቃ ቡድን እንዳደራጅ ስራ ተሰጠኝ፣ እግዚአብሔር ሙያዬን ሳልተው እርሱን እንዳገለግል እድል ሰጠኝ። ምንም ሳይኖረኝ መኖሪያዬ የዘላለም አምላክ ነው፣ ብዬ የታመንኩት አምላክ፣ ማንም ሰው በቀላሉ ሊያገኘው የማይችለውን እድል ሰጠኝ፣ ከዛ በኋላ ደስተኛ ሆንኩ፣ አሁንም ደስታዬ እየጨመረ እኖራለው። አለኝ። ይሄ የጓደኛዬ እውነተኛ ታሪክ ነው። እኛ ሁላችንም ተጓዦች ነን። የምንጓዘው በእምነት ነው። በእጃችን ካለው ስራ ይልቅ እግዚአብሔር ማመን ይገባናል። ሃዋርያት፣ ኢየሱስ ሲልካቸው፣ ምንም እንዳይዙ እንዲያምኑት ነግሯቸው ነበር ሲመለሱ ግን ምንም አልጎደላቸውም። በእምነት እንጓዛለን ምንም አይጎልብንም። ውጡ

ክርስቶስ ሆይ ክርስቶስ ሆይ ካንተ በላይ ውብ ቃል የለም፣ ባንተ ቃል ውብ የሆኑት ሰማይ ምድር ተፈጥረዋል። ቃልህ አንዴ ፈጥሮ አልተወንም፣ በየእለቱ ይሰራናል። "ይሁን" እያለ ውበትን የፈጠረ ቃልህ
ክርስቶስ ሆይ ክርስቶስ ሆይ ካንተ በላይ ውብ ቃል የለም፣ ባንተ ቃል ውብ የሆኑት ሰማይ ምድር ተፈጥረዋል። ቃልህ አንዴ ፈጥሮ አልተወንም፣ በየእለቱ ይሰራናል። "ይሁን" እያለ ውበትን የፈጠረ ቃልህ እንዴት ውብ ነው። በሰው ልብ ብዙ ነገር አለ፣ አንተ የመከርከው ቃል ብቻ ይፀናል። ክርስቶስ ሆይ ምክርህ እንዴት ውብ ነው። አንተ ስትናገር "አልሰማም" የሚል አንዳች የለም። ክርስቶስ ሆይ ተናገር እኛም እንሰማሃለን። ክርስቶስ ሆይ ኦ ድምፅህ፣ የሚያጓራውን አውሎ ነፍስ ይገስፃል። መስማት ያልቻለውን ጆሮ ይከፍታል፣ መናገር ያልቻለውን ምላስ ያናግራል። ቃልህን የሚቋቋም የለም፣ ዳጎን ቢሆን ይሰበራል፣ ኢያሪኮ ቢሆን ይፈርሳል። ክርስቶስ ሆይ ድምፅህ እንዴት ውብ ነው!!! ሙሉ ዘመኑን በአልጋ የዋለው ድምፅህን ሰምቶ ተነሳ፣ አይነ ስውር የነበረው ድምፅህን ሲሰማ አይኑ በራ። "ማን ነው የነካኝ" በሚል ቃልህ ከ12 አመት ጀምሮ ከማህፀና ደም ሲፈሳት የነበረች ሴት መዳኗን በሰውነቷ አወቀች። ክርስቶስ ሆይ ያንተን ውበት ለማየት እውር የነበረው አይኑ ይበራል፣ ድምፅህን ለመስማት የደንቆሮው ጆሮ ትከፈታለች፣ አንተን ያየ ሁሉ ስላንተ ለማውራት ምላሱ ይፈታል። በዚህ ምድር አንተን የማይወድ እንዴት ምስኪን ነው!!!! አንተ እግዚአብሔር የሰጠን ርእስ ነህ፣ አንተ ክርስቶስ ታሪክ ነህ፣ እውነት ነህ፣ ትንቢት ነህ፣ እናወራሃለን፣ እንኖርሃለን፣ እንመሰክርሃለን። ስላንተ ለማውራት ምቹ ስፍራ አይባልም፣ አለማቱ ሁሉ የተጋጠመው ባንተ ነው። ስላንተ ምቹ ጊዜ አይባልም የጊዜ ባለቤት አንተ ነህ፣ ስላንተ ላናወራ አንችልም፣ ስላንተ ዝም እንዳንል እርዳን። አንተን የሰሙ ሌላ ድምፅ እንዳይሰሙ ተመኝተዋል፣ አንተ ያዩ አባቶች ሌላ እንዳያዩ ቆርጠው የእምነት ምስክርነትን ትተውልን አለፉ፣ የምድርና የሰማይ ውበት ክርስቶስ

ሃሌሉያ "አለም ዋንጫ" ባሳለፍነው የአለም ዋንጫ ታዋቂው ጀስቲን ቢበር በፍፃሜው ቀን ሙዚቃ ከሚያቀርቡ ዳንኪረኞች አንዱ ነበር። ብዙዎቹ በብዙ ሙዚቀኞች፣ በብዙ ዳንሰኞች፣ በብዙ ብልጭልጭ ዳንኪራቸውን
ሃሌሉያ "አለም ዋንጫ" ባሳለፍነው የአለም ዋንጫ ታዋቂው ጀስቲን ቢበር በፍፃሜው ቀን ሙዚቃ ከሚያቀርቡ ዳንኪረኞች አንዱ ነበር። ብዙዎቹ በብዙ ሙዚቀኞች፣ በብዙ ዳንሰኞች፣ በብዙ ብልጭልጭ ዳንኪራቸውን አቅርበዋል። ጀስቲን ቢበር ተራው ሲደርስ አንዲት አኩስቲክ ጊታር ይዞ፣ ያለ አጃቢ "Everything Hallelujah" የተሰኘ ዘፈን አቀረበ። ያቀረበው ዘፈን በመጨረሻ አልበሙ ያወጣው ቢሆንም ሀሳቡ ግን ክፉ አይደለም፣ ሃሳቡ በደስታ ስንደንስ ፀሀይ አየችን፣ አዲስ ቀን መጣ ሃሌሉያ፣ በውሃ እደሰታለሁ ሃሌሉያ፣ ሁሉ ደስ ይላል፣ ወደ መስክ ስወጣ፣ ውበትን ሳይ ሃሌሉያ። ዝናብ ከሰማይ ሲዘንብ፣ የሚነፍሰውን አየር ስተነፍስ፣ በዚህ ሁሉ ስዘምር ሃሌሉያ፣ በደስታ ሳሸበሽብ ሃሌሉያ" ይላል። ይሄ የዘፈኑ ጥቂቱ ሃሳብ ነው። በመጨረሻ ስለ አለም ዋንጫው ሃሌሉያ እያለ ይጨርሳል። የእሱ የሙያ ጓደኞች እንደፈለጉ ባብለጨለጩት፣ ያለ ጥንቃቄ በተጠቀሙት ዳንኪራ ማንም አስተያየት አልሰጠም። ጀስቲን ቢበር ባቀረበው "Everything Hallelujah" ዘፈን ግን ብዙ አስተያየት ሰማን። አንዳንዶች "Hallelujah የአለም ዋንጫ ዘፈን አይደለም" አሉ። የአለም ዋንጫ ለምን Hallelujah ይከለክላል?? ጀስቲን ቢበር ብዙ ስኬቶችን ያገኘ፣ በመጨረሻም ደስታን ያጣ ሰው ነው፣ በዚህ በጥቂት አመታቶች ግን ትንሽ ተረጋግቶ በየስፍራው ስለ ኢየሱስ ሲያወራ ተሰምቷል፣ "አለቀለት" ከተባለ ህይወቱ ኢየሱስ እያከመው ነው። ጀስቲን ቢበር በጣም ህፃን ሁኖ አለም ያከበረችው ሰው ነው፣ አሁን የአለም ዝና ጥቅም እንደሌለው ሲመሰክር ሰምቼዋለው፣ ታድያ አለም በደገሰችው ድግስ አብዛኛው አርቲስት የሴቶችን ጭን እያሳየ በብልጭልጭ ሲደንስ እሱ ግን አንድ ጊታር ብቻ ይዞ Hallelujah ማለቱ ትልቅ ድል ነው። ማስተዋል ይስጠን።

ሲሰሙት ደስ የሚል!!!! በዚህ ምድር ኢየሱስን እያወቁ አለመደነቅን የመሰለ መበደል የለም። ኢየሱስ በመቅደስ እለት እለት ሲያስተምር ሁሉም በደስታ ይሰሙት ነበር፣ በዚህ ቅናት ያደረባረባቸው ሊገድሉት
ሲሰሙት ደስ የሚል!!!! በዚህ ምድር ኢየሱስን እያወቁ አለመደነቅን የመሰለ መበደል የለም። ኢየሱስ በመቅደስ እለት እለት ሲያስተምር ሁሉም በደስታ ይሰሙት ነበር፣ በዚህ ቅናት ያደረባረባቸው ሊገድሉት ይፈልጉ ፈለጉ፣ ነገር ግን ሕዝቡ ሁሉ ተንጠልጥለውበት ነበርና አልቻሉም። በእውነት ህዝቡ ሁሉ ተንጠልጥለውበት ነበር የሚለውን ሳነብ ልቤ ሀሴት ያደርጋል። በወጉ ሰላም ለማለት ፍላጎት ባጡ አገልጋዮች መሃል ስንገኝ ክርስቶስ ላይ ግን ይንጠለጠሉበት ነበር። ሉቃስ 19:47 ኢየሱስ ህዝቡን በምሳሌ ያስተምት ነበር፣ ፈሪሳውያንና የሄሮድስ ወገኖች ግን ተበሳጭተው ሊይዙት ፈለጉ፣ ህዝቡ በደስታ ግን ይሰሙት ስለነበር ማድረግ አልቻሉም። ስለ ኢየሱስ መስማት ሀሴት ነው። ከዛም በላይ የታሰሩ ይፈታሉ፣ በሽተኞች ይፈወሳሉ፣ ኢየሱስ ባለበት አጋንንት የለም፣ ኢየሱስ ደስታ ነው፣ በዚህ ምድር እውነተኛ የምስራች ተብሎ መነገር የሚገባው ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። ስለ ኢየሱስ ሲወራ እስረኛን ይፈታልና አሳሪው ይበሳጫል፣ በሽተኞች ይፈወሳሉና አሳማሚ ይበሳጫል፣ ክርስቶስ እሳት ያጠፋልና እሳት ጫሪዎች ደስ አይሰኙም፣ ክርስቶስ ፈውስ ነውና መድሃኒት ሻጮች ሰላም ያጣሉ። ኢየሱስ ብርሃናችን ነውና በጨለማ ያሉ ይሄን ስም መስማት አይፈልጉም። ስለ ኢየሱስ ስታወሩ ደስ የማይሰኝ የሰላም ሰው አይደለም። ነገሩ እንዲህ ነው፣ ብዙ እስረኛ ወዳሉበት ወይኒ ቤት እስረኛውን ለማስፈታት ሄዳችሁ እንበል፣ የእስር ጠባቂው ዝም ብሎ የሚያይ ይመስላችኋል?? በጭራሽ!! እስረኞች ነፃ እንዳይወጡ እስከመጨረሻው በእሳት ምላጭ ይፋለማችኋል። ኢየሱስ ነፃነት ነውና ነፃ ያልወጡ ይቃወሟችኋል። በእሳት በተያያዘ ቤት ከእሳቱ ውስጥ ሰዎችን ስናወጣ የእሳቱ ሙቀት አይንካን አንልም፣ በውሃ እየሰመጠ ያለን ሰው ከውሃው ስናወጣ ውሃው አይንካን አይባልምና።

የስጋ ድካም ስጋ ደካማ ነው። የቱንም ያህል ብትንከባከቡት ስጋ ደካማ ነው፣ ለፀጉራችሁ በጊዜው ይሸብታል፣ ለፊታችሁ "ክሬም፣ ሰን ስክሪን" ብትጠቀሙም፣ በጊዜው መጨማደዱ አይቀርም። ዘመን ሲጨምር የቱ
የስጋ ድካም ስጋ ደካማ ነው። የቱንም ያህል ብትንከባከቡት ስጋ ደካማ ነው፣ ለፀጉራችሁ በጊዜው ይሸብታል፣ ለፊታችሁ "ክሬም፣ ሰን ስክሪን" ብትጠቀሙም፣ በጊዜው መጨማደዱ አይቀርም። ዘመን ሲጨምር የቱንም ያህል እራሳችሁን ብትንከባከቡትም ታረጃላችሁ። ለጤና ተስማሚ ምግብ ብትመገቡም፣ ስጋ ከማርጀት አይመለስም፣ ብዙ ዘመን የመገባችሁት ሰውነት ጥቂት ቀን ምግብ ሲያጣ ፊታችሁ ጠጠቁራል፣ አስር አመት ያለማቋረጥ በሰአቱ የመገባችሁት ሰውነት 10 ሰአት አይታገሳችሁም፣ ብዙ አመት በልቻለው ዛሬን ልታገስ አይላችሁም፣ ስጋ ውለታ ቢስ ኑው። ህፃናት ልጆቻችሁን ቀኑን ሙሉ፣ ብዙ ብታበሏቸው ወፍራምና ሞኝ ይሆናሉ፣ ጎበዞች እንዲሆኑ ብላችሁ የተመጣጠነ ምግብ ያበላችኋቸው ልጆች ጤና ያጡና፣ የወደቀ ጣሳ ማንሳት የማይችሉ ይሆናሉ። እራሳችሁን መንከባከብ ከፈለጋችሁ፣ እያረጃችሁ ስትሄዱ መለምለም ከፈለጋችሁ እየሱስ ክርስቶስን ውደዱት፣ ውበታችሁ እየጨመረ፣ ጤናችሁ እየጨመረ፣ ስኬታችሁ እየጨመረ መሄድ ትፈልጉ ይሆን? ወደ ክርስቶስ ኑ!!! እንደ ሀዋርያው ጳውሎስ፣ ጌታን ልበሱት። ጌታን የለበሱ፣ ስጋቸውን እንደ እሾህ የሚወጋ ህመም እንኳን ተሰቷቸው ደስ ይሰኙ፣ ይለመልሙ ነበር። ቅዱስ ጳውሎስ ፦ የዘላለም እንጀራ የሆነውን ክርስቶስን መረጠ እና፣ በድካም በረታ፣ በግርፋቱ አተረፈ፣ በሞቱ የዘላለም ህይወት አገኘ። 40 ግርፋት 5 ጊዜ ተገረፈ፣ 3 ጊዜ በበትር ተመታ፣ በድንጋይ ተወገረ፣ መርከቡ 3 ጊዜ ተሰበረ፣ በአደጋ በባህር ውስጥ አለፈ፣ ስጋው እንቅልፍ ቢያጣም፣ ወንጌሉን በመስበክ ብርቱ ነበረ፣ ሁሉን የሚገድል መርዘኛ እባብ እሱን አልገደለውም፣ ይልቅ እንደ ብናኝ ከራሱ ላይ ወደ እሳት አራገፋት። እለት እለት ስጋን የሚያደክሙትን ፈተናዎች ለማለፍና ለመበርታት የናዝሬቱ እየሱስ ክርስቶስን ብሉ።

በዚህ ቃል ተፅናኑ። ደካሞች እንደደከሙ አይቀሩም፣ ሀዘንተኞች እንዳዘኑ አይቀሩም፣ ፊታቸው በሃዘን ለጠቆረ እግዚአብሔር ተስፋ አለው፣ ያዘኑ ፈገግ የሚሉበት ቀን ይመጣል። ወደ እልፍኛቸው ገብተው ያለቀ
በዚህ ቃል ተፅናኑ። ደካሞች እንደደከሙ አይቀሩም፣ ሀዘንተኞች እንዳዘኑ አይቀሩም፣ ፊታቸው በሃዘን ለጠቆረ እግዚአብሔር ተስፋ አለው፣ ያዘኑ ፈገግ የሚሉበት ቀን ይመጣል። ወደ እልፍኛቸው ገብተው ያለቀሱ፣ በሰው ፊት ግን በፈገግታ የዋሉ እግዚአብሔር አይቷቸዋል፣ ሀዘናቸውን ወደ ደስታ፣ ድካማቸውን ወደ ብርታት ይቀይራልና በዚህ ቃል ተፅናኑ። ግራ ለተጋቡ፣ እውነተኛ መፅናኛ እግዚአብሔር ነውና በዚህ ቃል ተፅናኑ። አሮጌው ያልፋል ሁሉን አዲስ ያደርጋልና በዚህ ቃል ተፅናኑ፣ የሰለጠነባችሁን ይሰብርላችኋልና በዚህ ቃል ተፅናኑ። ስራ ትርፍ ያላስገኘላችሁ፣ በትምህርት መሻገር ያቃታችሁ፣ ሰው ከቁም ነገር የማይጥፋችሁ፣ በምድር ሚዛን ጎደላችሁ፣ ጓደኛ የሌላችሁ፣ ቤተሰብ ችላ ያላችሁ፣ ያቆብ ሮቤልን እንዳለው "ተውት አይሙት፣ ዝም ብሎ ይኑር!" እንዳለው በቤተሰብ በዘመድ "እንዲሁ ተዉት!" ተብላችሁ የተናቃችሁ፣ ሰው እንደሚላችሁ እግዚአብሔር አይላችሁምና በዚህ ቃል ተፅናኑ። እራሱን ታምኖ የሚሰራ አምላክ የናንተን እርዳታ ሳይጠብቅ ይሰራልና በዚህ ቃል ተፅናኑ። ገብያችሁ ትንሽ ቢሆን እግዚአብሔር በረከታችሁ ነው፣ ሮጣችሁ ባይሳካላችሁ እግዚአብሔር ስኬታችሁ ነው። እግዚአብሔርን የሚያህል እረዳት አለላችሁና ሰው ምን ያደርጋችኋል። ለሰው ምንም ብትሆኑ ለአምላክ ግን በነፍስ የተገዛችሁ ውድ ናችሁ። ውድ ናችሁ!!!! የሰራችሁ የሰማይ እጅ ነው። እናንተን የሰራ ጥበበኛ ሳይሆን እራሱ ጥበብ ነው። ከሰው ፊት አትደበቁ የሚያኖራችሁ የዘላለም አምላክ ነው። ሰማይ ይፈልጋችኋል፣ ክርስቶስ ከሰማይ ዙፋኑ የመጣው ክብራችሁን ስለሚያውቅ ነው። ስትጎሉ የማይወድ ጌታ ሊፈልጋችሁ መጥቷል። መልካም ነገር ሁሉ ስለሚገባችሁ ነው ክርስቶስ በመስቀል የሞተላችሁ። በመስቀል መከራን የተቀበለው ለናንተ ነውና በዚህ ቃል ተፅናኑ።...

እግዚአብሔር በአላት። የእስራኤል ህዝብ ከግብፅ ባርነት እንደወጣ በየመንገዱ በአል ያደርግ ነበር፣ ድንኳን የመትከል በአል፣ ድንኳን የማንሳት በአል፣ የሞሎት የኮከቦች በአል፣ የወርቅ ጥጃ በአል፣ የሞ
እግዚአብሔር በአላት። የእስራኤል ህዝብ ከግብፅ ባርነት እንደወጣ በየመንገዱ በአል ያደርግ ነበር፣ ድንኳን የመትከል በአል፣ ድንኳን የማንሳት በአል፣ የሞሎት የኮከቦች በአል፣ የወርቅ ጥጃ በአል፣ የሞአብና ምድያም መስዋእት በአል፣ የመናፍስት መጠየቅ በአል፣ ለአማልክት መስዋእት ማቅረብ በአል፣ የልጆች መስዋእት ለሞሎክ በአል... እጅግ ብዙ በአላትን ከአህዛብ ተቀብለው ሲያከብሩ ይውሉ ነበር። እግዚአብሔር ለእርስቱ የመረጠው ህዝብ ያገኘውን ሁሉ የሚያከብር ሆነ፣ የሌሎች አማልክትን በአል ያክበራሉ። በኛ ዘመን ብዙ የአህዛብ በአል ሳይታወቀን እየወረሰን ነው፣ ገና ትምህርት ለሚጀምሩ ህፃናት በየቤቱ በአል ይደረጋል፣ በተባበሩት መንግስታት አማካይነት ብዙ የስላቅ በአላት አለ። የውሸት ቀን፣ የትራስ ቀን፣ የሰነፍ ቀን፣ የፒዛ ቀን፣ የቸኮሎት ቀን... እኚህን የመሰሉ አስቂኝ ቀኖች ይከበራሉ፣ አላማቸውም ገብያ ነው፣ እኛም እናከብራቸዋለን። ሰማይ ሳይሆን ገብያ የሚመራውን በአል እናከብራለን። ክርስቲያን እግዚአብሔርን ያህል አፍቃሪ፣ ክርስቶስን ያህል ባለፀጋ መንፈስ ቅዱስን ያህል አፅናኝ እያለው፣ ቀኖችን በአህዛብ አምላክ አይዋጅም። ለእግዚአብሔር የምስጋና ቀን ማወጅ ትልቅ በረከት ነው፣ አህዛብ እንደሚያደርጉ በየወቅቱ ለመብላትና ለመጨፈር መነሳት እግዚአብሄራዊ አይደለም። ኢሳያስ፣ መባቻችሁንና በዓላቶቻችሁን ነፍሴ ጠልታለች፤ ሸክም ሆነውብኛል፥ ልታገሣቸውም ደክሜያለሁ። ይላል እግዚአብሔር ብሎ ተናግሯል። ኢሳ 1:14 ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር ማድረግ መልካም ነው፣ ለእግዚአብሔር የምስጋና ቀን ማወጅ ድንቅ ነው፣ በእግዚአብሔር በራሱ ደስ መሰኘት መባረክ ነው፣ ነገር ግን እግዚአብሔር የሌለበት፣ ክርስቶስ የሌለበት በአል ብክነት ነው። ዛሬ የስላሴን በአል ያከበራችሁ፣ ክብር አይጉደልባችሁ።