Goro PHCU - Dire Dawa
Open in Telegram
Goro PHCU–Dire Dawa is Public Platform, of Goro PHCU, created to communicate & disseminate only health and health related informations, updates, news, and facts. Youtube link: https://youtube.com/@ghcdire
Show more827
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-330 days
Posts Archive
Repost from Seed Phrase Search_Crypto Wallet
Our team created software that searches for forgotten crypto wallets 💰
📣 EVERY CLIENT with a subscription gets not only the money making software itself, but also great service and customer support ✔️ so you can get started WITH PEACE OF MIND 😌🔟
Act before the people who dream, and get all the benefits of our community 💰
👉 Perfectly working software
👉 Video and text instructions for software
👉 Support for BTC | ETH | LTC | BNB | SOL | USDT
👉 Over 300 satisfied clients
👉 Free software updates
👉 Private development by our team
👉 24/7 support
👉 Profit without any risk
Software subscription 🎚️
⭐️ One blockchain - 80$
⭐️ Two blockchain - 160$
⭐️ Three blockchain - 250$
⭐️ Four blockchain - 340$
⭐️ Five blockchain - 420$
⭐️ Six blockchain - 500$
Admin ➡️@mr_mmarks
#በወረዳችን ከሚገኙ የእድር አመራሮች ጋር የወባ ወረርሽኝ ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ ።
በዛሬው እለት ከጎሮ ጤና ጣቢያ ጋር በጋራ በመሆን በወረዳችን ውስጥ የሚገኙ የእድር አመራሮችን በጎሮ ጤና ጣቢያ አዳራሽ ስለወባ ወረርሽኝ አሁናዊ ሁኔታን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ የሰራን ሲሆን በዋናነት የእድር አመራሮች በማህበረሰብ ላይ ያለቸውን ተሰሚነት በመጠቀም ማህበረሰባችንን ከወባ ወረርሽኝ ለመከላከል እና ጤናማ ማህበረሰብ እንዲኖር ለማድረግ መደረግ ስለሚገባው ጥንቃቄ የሚያሳውቅ ትራክ በመስጠት በእድሩ ስር በሚገኙ አባላት ላይ በመስራት ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ በመግባባት አጠናቀናል ።
ድ.ዳ አስተዳደር
ወረዳ ⓶ አስተዳደር ፅ/ቤት
ቀን 26/ 02/ 17 ዓ.ም
#ከሃይማኖት አባቶች ጋር የወባ ወረርሽኝን በተመለከተ ውይይት ተደረገ ።
በዛሬው እለት ከጎሮ ጤና ጣቢያ ጋር በጋራ በመሆን የወባ ወረርሽኝን በተመለከተ በወረዳችን ከሚገኙ የሀይማኖት አባቶች ጋር ውይይት ያደረግን ሲሆን በቀጣይ ጊዜያት የሃይማኖት አባቶቻችን በየሃይማኖት ተቋማቶቻቸው ላይ ከሚሰጡ ሃይማኖታዊ ትምህርቶች ማብቂያ ላይ ለመእመናኑ መልዕክት በማስተላለፍ ሃይማኖታዊ አባትነታቸውን እንደሚወጡ እና በቀጣይም የማህበረሰብ ጤናን በተመለከተ በጋራና በትብብር ለመስራት ቃል ገብተዋል
ድ.ዳአስተዳደር
ወረዳ ⓶ አስተዳደር ፅ/ቤት
ቀን 26/ 02/ 17 ዓ.ም
በዛሬው ቀን 19/02/2017 የወረዳ 2 አስተዳደር የጤና ማስተባበሪያ ከጎሮ ጤና ጣቢያ እና ከቦረን ጤና ጣቢያ ጋር በጋራ በመሆን በ3ቱም ቀጠና ከ22መንደር ለተውጣጡ የማህበረሰብ ክፍሎች የወባ ወረርሽኝ አሁናዊ ሁኔታ ያለበትን ደረጃ እንዲሁም ዋናው የበሽታው ስርጭት መንስኤዎችን በተመለከተ ሰፊ ውይይት አድርገናል በመሆኑም ሁሉም ሰው ወባን ማጥፋት ከኔ ይጀምራል የሚለውን እሳቤ በመያዝ አሁን በተጨባጭ እየታየ ያለውን የማህበረሰባችንን መዘናጋት በሚገባ ተገንዝቦ ህብረተሰቡ ከግዴለሽነትና ከቸልተኝነት በመውጣት ከቤቱ ጀምሮ አካባቢውን በማፅዳት የውሀ አጠቃቀምን በሚገባ በጥንቃቄ በመክደን ለትንኝ መራቢያ ምቹ እንዳይሆን በማድረግ የራሱን ሀላፊነት መወጣት እንዳለበትና የበሽታውን ስርጭት በመቀነስ ጤናማ የሆነ ቤተሰብንና አካባቢን መፍጠር እንዳለበት ሰፈ ውይይት በማድረግ የእለቱን መድረክ አጠናቀናል
ወቅታዊ ጉንፋን እና ጉንፋን መሰል የመተፈንሻ አካላት ህመም በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ
___
የጉንፋን ሕመም በተፈጥሮ የላይኛውን የመተንፈሻ የሰውነት ክፍሎች ማለትም አፍንጫን፣ ጎሮሮን እና የአየር መተላለፊያ ባንቧን የሚያጠቃ ተላላፊ ሕመም ነዉ።
ሪኖ ቫይረስ ለጉንፉን መከሰት ዋና ምክንያት ሲሆን፣ ኮሮና፣ ኢንፍሉዌንዛ፣ ፓራ ኢንፍሉዌንዛ፣ አር ኤስ ቪ(RSV) ቫይረሶች ደግሞ ለጉንፉን መሰል ህመሞች መከሰት ዋና ዋና ምክንያቶች ናቸዉ። ከተጠቀሱት ቫይረሶችም ለጉንፋን ሕመም መከሰት 50 በመቶ ድርሻውን የሚይዘው ሪኖ ቫይረስ ነው፡፡ በደረቅ ነፋሳማ ወቅት የአፍንጫ የውስጠኛው ስስ ሽፋን “ሙከስ መምብሬን” ስለሚደርቅ የጉንፋን ሕመም እና ተላላፊነቱ ይጨምራል፡፡ የክረምት ወራት ወይም የዝናብ ወቅት ማብቃቱን ተከትሎ መስከረምን ጨምሮ በጥቅምትና ህዳር ወራት እንደዚህ አይነት ጉንፋን መሰል ህመም የሚጠበቅ ነው፡፡
ሕመሙ ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፈውም በቫይረሱ የተጠቃ ሰው በሚያስልበት ወይም በሚያስነጥስበት ጊዜ እንደሆነና በተጨማሪም ሰዎች ቫይረሱ ያረፈበትን የበር እጀታ፣ ጠረጴዛ ወይም በሕመምተኛው የተነካካንን ሰው እጅ ከነኩ በኋላ አፋቸውንና አፍንጫቸውን ሲነካኩ ቫይረሱ ለመተላለፍ በሚፈጠርለት ምቹ ሁኔታ ነው።
የጉንፋን ሕመም የመጀመሪያ ምልክቱ ከመጀመሩ አንድ ቀን በፊት ተላላፊ ሊሆን ይችላል፤ ሕመሙ ከጀመረ ከ 5 እስከ 10 ባሉት ቀናት ደግሞ ሕመምተኛው ቫይረሱን ያስተላልፋል። ህመሙ አብዛኛዉን ጊዜ እስከ 2 ሳምንት ሊቆይ ይችላል። ምልክቶቹም እንደ የአፍንጫ ፈሳሽ መብዛት፣ ሳል፣ ትኩሳት፣ ራስ ምታትና ጉሮሮን መከርከር፣ ማስነጠስ፣ አይን ማሳከክ እና መቅላት፣ ማስታወክ፣ ከፍ ሲልም የትንፋሽ ማጠር፣ ከፍተኛ ድካምና የምግብ ፍላጎት መቀነስ ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ።
በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከ2003 ዓ ም ጀምሮ የእንፍሉዌንዛ እና መሰል የመተንፈሻ አካላት በሽታዎች ቅኝትና ምላሽ በሁሉም ክልሎች እና ከተማ መስተዳድሮች እየተሰራ ይገኛል። ከመስከረም ወር ጀምሮ መሰል ህመም ተሰምቷቸው ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ ናሙና ከሰጡት ታካሚዎች ውስጥ አር ኤስ ቪ የተገኘባቸዉ ቁጥር የመጨመር ሁኔታ ያሳያል፡፡ በዚሁ ወቅት የተከሰተው ጉንፋን መሰል ህመም (አር ኤስ ቪ) በተለይ በህጻናት ላይ በብዛት የተከሰተ ሲሆን ለዚህም ወቅቱ ትምህርት ቤት የተከፈተበት በመሆኑ ለበሽታው መስፋፋት አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ባለፈዉ 1 ወር ዉስጥ ተመርምረዉ አር ኤስ ቪ ከተገኘባቸዉ ታካሚዎች መካከል 84% ያክሉ እድሜያቸዉ ከ5 አመት በታች ነዉ። እንደዚሁም ባለፈዉ ሳምንት ለአር ኤስ ቪ ከተመረመሩት 81 ናሙናዎች 49 (60.5%) ያህሉ ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል።
አስፈላጊው ጥንቃቄ ካልተደረገ በሽታው የመዛመት እድሉ ከፍ ሊል እንደሚችል፤ በተለይ ቀዳሚ ተጎጅ ሊሆኑ የሚችሉ እንደ ህጻናትና አረጋውያን ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች አና ተጓዳኝ የጤና ችግር እንደነ አስም፣ የስኳር በሽታ፣ ካንሰር እና ሌሎች ሥር የሰደዱ በሽታዎች ያሉባቸው ሕሙማን ከፍተኛ ጥንቃቄ ልናደርግላቸው እና ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ አስፈላጊዉን ምርመራና ህክምና ሊያደርጉ ይገባል፡፡ በተጨማሪም የጉንፋን ሕመም የጆሮ ኢንፌክሽን እና የሳንባ ምች ሕመምን ጨምሮ ለተለያዩ ሕመሞች ተጋላጭ ሊያደርግ ይችላል፡፡
ጉንፋን መሰል በሽታን ከምንከላከልባቸው መንገዶች መካከልም የእጅ ንጽህናን መጠበቅ፣ ሰዎች በተሰበሰቡበት ቦታ የአፍና አፍንጫ ጭምብል(ማስክ) በማድረግና በዕለት ኑሯችን የምንጠቀምባቸውን በከባቢዎቻችን የሚገኙ ቁሳቁሶችን ማጽዳት እና የብዙሃን ማጓጓዣ ትራንስፖርት ላይ መስኮቶችን በመክፈት በቂ የአየር ዝዉዉር እንዲኖር በማድረግ የበሽታዉን የመተላለፍ ዕድል መቀነስ ይቻላል፡፡ ስለዚህ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን የጥንቃቄ እርምጃዎችን እንዲወስድና ጠንከር ያለ የበሽታው ምልክት የሚታይበት ሰው በፍጥነት በአቅራቢያው ወደሚገኝ የጤና ተቋም በመሄድ አስፈላጊውን የህክምና ምክር አና ዕርዳታ ማግኘት አለበት፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በ952 እና 8335 ነጻ የስልክ መስመር መደወል የሚቻል መሆኑን እያስታወስን ሕብረተሰቡ ሊከተላቸው የሚያስፈልጉ የጥንቃቄ እርምጃዎችን አስመልክቶ ዝርዝር መግለጫ እና መረጃዎችን በየጊዜው የምንሰጥ መሆኑን እንገልጻለን።
ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት
Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health, Ethiopia
+3
ትናንት በያዝነው ፕሮግራም መሰረት ዛሬ በተቋማችን የደም ልገሳ ፕሮጋራም አድርገናል። በዚህም 23 Units bag ደም መለገስ ችለናል።
በመሆኑም ደም የለገሳችሁ የተቋማችን እንቁ ባልደረቦቻችን ከልብ እናመሰግናለን!
ክብረት ይስጥልን!
ሰላም ለሁላችን ይሁን ውድ ባልደረቦቻችን!
ነገ ማክሰኞ 05/02/2017 ዓም የደም ልገሳ ፕሮግራም ስላለን ሁላችንም ቁርስ በልተን ተዘጋጅተን በመምጣት የእድሉ ተካፋይ እንሁን።
እናመሰግናለን!
መልካም አዳር!
Repost from N/a
Dear Health Centers Heads,
Here is the past 5 weeks and overall Wellness Pass performance, Over the weeks, our performance has not met expectations, and we anticipated improvements following our recent review meeting. Unfortunately, we are still seeing slow progress. So, please follow your team closely. from here on, we will be posting weekly performances every SUNDAY to make it easier for your follow up.
Thanks in advance!
+4
እንኳን ደስ አለን - Congratulations!
በጤና ሚኒስቴር በተካሄደ EPAQ የ2016 ዓ.ም ትግበራ አፈፃፀም ግምገማ ሀገር አቀፍ መድረክ ተቋማችን ጎሮ ጤና ጣቢያ በበጀት ዓመቱ ባስመዘገበው ከፍተኛ አፈጻጸም የእውቅና ምስክር ወረቀትና ሦስት (3) ኮምፒውተሮች ሽልማት ተቀብለናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ወረዳ 2 ጤና ማስተባበሪያ የእውቅና ምስክር ወረቀትና አንድ (1) ኮምፒውተር ሽልማት ተበርክቶለታል።
Congratulations all!
Goro PHCU Always one Step a Head!
+4
እንኳን ደስ አለን - Congratulations!
በጤና ሚኒስቴር በተካሄደ EHAQ የ2016 ዓ.ም ትግበራ አፈፃፀም ግምገማ ሀገር አቀፍ መድረክ ተቋማችን ጎሮ ጤና ጣቢያ በበጀት ዓመቱ ባስመዘገበው ከፍተኛ አፈጻጸም የእውቅና ምስክር ወረቀትና ሦስት (3) ኮምፒውተሮች ሽልማት ተቀብለናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ወረዳ 2 ጤና ማስተባበሪያ የእውቅና ምስክር ወረቀትና አንድ (1) ኮምፒውተር ሽልማት ተበርክቶለታል።
Congratulations all!
Goro PHCU Always one Step a Head!
+4
እንኳን ደስ አለን - Congratulations!
በጤና ሚኒስቴር በተካሄደ EHAQ የ2016 ዓ.ም ትግበራ አፈፃፀም ግምገማ ሀገር አቀፍ መድረክ ተቋማችን ጎሮ ጤና ጣቢያ በበጀት ዓመቱ ባስመዘገበው ከፍተኛ አፈጻጸም የእውቅና ምስክር ወረቀትና ሦስት (3) ኮምፒውተሮች ሽልማት ተቀብለናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ወረዳ 2 ጤና ማስተባበሪያ የእውቅና ምስክር ወረቀትና አንድ (1) ኮምፒውተር ሽልማት ተበርክቶለታል።
Congratulations all!
Goro PHCU Always one Step a Head!
