en
Feedback
አባ ደዋም 𝑠𝑤𝑒𝑒𝑡 ℎ𝑜𝑚𝑒🥰

አባ ደዋም 𝑠𝑤𝑒𝑒𝑡 ℎ𝑜𝑚𝑒🥰

Open in Telegram

የሰሀባ እና የደጋጎች ታሪክ የአብሬት እንዲሁም የቃዲሪይ ሲልሲላ የወአዝ ምክሮችን ፣ ከአካቢሮች የሰማናቸውን ቀሰሶች ፣ እንዲሁም ከመሻኢኾቻችን ኪታቦች አንዳንድ ጠቃሚ ነገሮችን የምንማማርበት ቻናል ነው Telegram 👇 Join ያድርጉ t.me/Abadewamee -አደራ በጥሩ ኒያ ተከታተሉን √ 𝐉𝐨𝐢𝐧 @Abadewamee 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄 @Abadewamee

Show more
506
Subscribers
No data24 hours
+47 days
-130 days
Posts Archive
ሽቀላ ነው ሰለዋት በሉ! በነቢዩﷺ አንድ ሰለዋት ማውረድ ከትርፍ በላይ ነው።

ረቢዑን የጭቅጭቅ ወር አታድርጉት! አማና የምላችሁ አትከራከሩ #መውሊድ_የፈለገ_ያክብር_ያልፈገ_አያክብር። ዋናው የነቢዩﷺ ሀያት ወደ ህይወታችሁ ለማምጣት ሞክሩ እና ሲራቸውን ቅሩ! [ኡስታዝ አዲል አህመድ]

#1501ኛው ረቢዐል አወል 12ኛው ለይል ከአስር ሰአት በሁዋላ በፈጅር መቃረቢያው ላይ ትልቁ ሰውﷺ ተወለዱ። እንኳን ለነብዩ ﷺ #መውሊድ አደረሳችሁ:: 💚🎉♥️

[አባባ በመድሀቸው አህመዴ ከሚለው መንዙማቸው ላይ በነቢዩﷺ #መወለድን ሲገልጹት እንዲህ ይላሉ፦ واهتز كل اكوان الله عاشقا ونزهة وتراجفت به الملإكة بالغرام والوج
[አባባ በመድሀቸው አህመዴ ከሚለው መንዙማቸው ላይ በነቢዩﷺ #መወለድን ሲገልጹት እንዲህ ይላሉ፦ واهتز كل اكوان الله عاشقا ونزهة وتراجفت به الملإكة بالغرام والوجد وفتح الجنان والعطر يتباهر لمولد طه العربى المجتبى الأمجد ለነብያችንﷺ ዊላዳ ካኢናቱ ሁሉ በደስታ ተወዛወዘ ፣ መላኢካው ሁሉ በኢሽቅ ተንቀጠቀጠ ፣ ሁሉም የጀነት በሮች እጅግ ግሩም በሆነ መአዛ ታጅበው ተከፈቱ:: የነብያችንንﷺ መወለድ አላህ እራሱ ነው ቀድሞ ያከበረው:: https://t.me/Abadewamee

በረቢዕ ሴት ልጅ የተወለደችለት ውቢቱ "ሸይማእ" ይበላት "ሸይማእ" በሃሊመቱ በኩል የሰይዳችን የጥቢ እህታቸው ናት...አንቺቱ እንዴት ያለ እድያ አገኘሽ? በሓሊመት ፈንታ ታጫውታቸውና ታስተኛቸው ነበር ﷺ በዚህ ግጥም እያዜመች፥ هذا أخ لي ولم تلده أمي وليس من نسل أبي وأمي فأنمه اللهم فيما تنمي. እናቴ ሃሊመት ያልወለደችው ወንድሜ ነው ስትል የጥቢ እህታቸው መሆኗ እያስደሳት ነው። የሃዋዚን ጠሃይ በበረታበት እኩለ ቀን ስታጫውታቸው እሜት ሃሊማ "ወደ ቤት ግቡ እንጂ" ስትላት "እናቴ ወንድሜን ጸሃይ አይነካውም ዳመናዋ ልታስጠልለው ትከተለዋለች " ብላ ትመልስላት ነበር ﷺ ** የሰይዳችን ﷺ የወተት እናቶች 8-10 ይደርሳሉ' ሁሉም የሂዳያን ብርሃን ተወፍቀው እንጂ አልሞቱም። #አብሬትዬም_አባባ قدس سره .ሰሂቁል አንዋሪ ወል ሚስኪ ወል አንበር) የሚለው መድህቸው ላይ አጥቢዎቻቸው የጀነት ሙሽሮች ናቸው እንዳሉት፥ ومرضعاته عرائس الجنة هي الحليمة قبلها الثويبة አቦሉን በረካ ያገኘቺው እመት ሱወይባህ ናት፥ለሳምንት ወይም 10 ቀናት በዊላዳው መግቢያ ትኩስ ወተቷን የአሚነት ትክ ሁና ለጧሃ ይሁን ብላለች። የአቡ ለሐብ ልጃገረድ ነበረች ለመውሊዳቸው ስታበስረው ነጻ ያወጣትና በሷ ሰበብ ኢስነይን ቀን ቅጣት እንደሚቀልለት ሰይዱና አባስ ባዩት ህልም ቢሻራ ታየ.......እንኳን አማኙ ያላመነው እንኳን የስዎን ሰው ነጻ ሲያወጣ ለህመሙ ፋታ እሚያገኝባቸው ነብይﷺ ** ከዚያማ ሃሊመቱ-ሰዕዲያህ የልጅነትዎን በረከት እጅጉን ብቻዋን ልታፍሰው ልትዝቀው አሏህ ፈቀደላት' ከቀየዋ ስትመልሰው ያረጀች ድኩም ግመላቸው የጧሃን ገላ መሸከም ብርታት ሆኗት እንደቡራቅ በነሻጣ አስጋለባት። ሃሊመቱም የደረቀው ወተቷ ረቢዕ አፍለቀለቀው ፥ ጎጆዋን እስከ ጋጣዋ የሙሐመድ በረካ ኮልኩሎ አሳቀው፥ ስሟን እስከባል ጎረቤቷ በእቅፍዎ በርከት አላቀው ፥ መካ ስትመልሰው የሜዳው ሳር ሳይቀር የሙስጦፋን ኮቴ አሸቀው......ከእናቱ መልሳው ኖረች ስትናፍቀው የግራዋን ጡት ለጥቢ ወንድማቸው ብለው ነክተው አያውቁም' የሰፈር ሰዎች ሲታመሙ ወይም ግመልና ፍየሎቻቸው ሲጎዱ ወደ ሃሊመት ጎጆ ተስበው እየመጡ "የዚያን ሙቀደስ ልጅሽን እጅ አስነኪን "ብለው ለመድሃኒትዎ ይማጠናሉ......."ከሱለይማን ሙልኩ ምጡ የደመቀው" ብለው የለም #የወረባቦው። ** ቡሰይሪይ በሃምዚያቸው የጥቢውን ወራት ሙዕጂዛቱ ጀማመረው ብለዋል وبدت في رضاعه معجزات ليس فيها عن العيون خفاء ከበረከቱል #ሐበሽይ በኋላ 3 አቲካዎች ለሐቢባችን ﷺ የወተት እናት ሆነዋል። "أنا بن العواتك የአቲካዎች ልጅ ነኝ" እሚለውን ሓዲስም ኡለማዎች እኚህን ጥቆማ ነው ብለዋል....እሚዐጅበው 3ቱም አቲካዎች ነቢን በማቀፍ እመቤት ቢባሉም ጥንፍፍ ያሉ ቢክራዎች ነበሩ ይባላል፥ወተታቸው የፈለቀው በጦይባው መውደድ እንጂ እናት ሁነው አልነበረም ﷺ♥️ ኑሩ ረቢዕ.....ሰላም ይድረሶት ሆዴ! https://t.me/Abadewamee

#ሰሉ_አለ_ነቢ ♥️ አላሁመ ሰሊ ወሰሊም አላ ሰይድና ሙሀመድ 💯 🤍

ሰሊ በሉ ሰላም ትሆኑ ዘንድ!🥰

ሸፊዒ ﷺ ♥️ የግርማ ሞገስ ብሎም የእዝነት ባለሟል ናቸው። መንገድ አመላካቻችን፣ ኢማማችን ናቸው። ቁርዓንን ያገኘነው በእርሳቸው ነው። እሳቸው መንገድ ባያመላክቱን፣ ተውሒድ'ን ባያስተምሩን፣ ሐላልና ሐራሙን ለይተው ባያስተምሩን፣ በብርሓናቸው #ከጨለማው_ባያስወጡን ኖሮ የዘቀጥን ህዝቦች እንሆን ነበር። 💯%💯 አልሃምዱሊላሂል ወዱዲል አሃዲ ኧለዚ ሸረፈ ለይለተል #መውሊዲ

➦ ዘመን እንደሆነ በአንድ ሓል አይኖርም:: ተራ በተራ ይለዋወጣል:: ከጅምሩ አንስቶ ሁሉም ነገር እየተቀያየረ መጥቷል:: ምድር እንደሆነ እንግዳ ነገር ለምዷል:: አዳዲስ እንግዳ እየተቀየረበት ይኖራ
➦ ዘመን እንደሆነ በአንድ ሓል አይኖርም:: ተራ በተራ ይለዋወጣል:: ከጅምሩ አንስቶ ሁሉም ነገር እየተቀያየረ መጥቷል:: ምድር እንደሆነ እንግዳ ነገር ለምዷል:: አዳዲስ እንግዳ እየተቀየረበት ይኖራል:: ❝ ከጌቱዋ ወአዝ የተወሰደ ❞ ➦ በቅርብ አመታት ብቻ ስንቱን ወደ አኼራ ሸኘን? ትናንትና የነበሩ አባት እናቶቻችንን ወዳጅ ዘመዶቻችንን ስንቶቻችን ሸኘን? (አላህ በረሕመቱ ይሸፍንልን) ➦ ከመቶ አመት በፊት የነበረው ትውልድ ሁሉ አልፎ አሁን ሌላ አዲስ ትውልድ አዲስ እንግዳ ተተክቷል:: አሁን ያለነው እኛም አልፈን ሌላ እንግዳ አዲስ ትውልድ ይፈጠራል:: ዱኒያ ጠፊ አላፊ ነው:: #ለነገው_ቤታችን_ለአኺራ_የእውነት_እንዘጋጅ ፣ አላህን ከምር እንፍራው ፣ የምር ተውበት እናድርግ ፣ ከነብስያ ሸህዋት ከሸይጣን ከይድ እራሳችንን እንጠብቅ ፣ ሁሌም እውነተኛ ሁሌም ከእውነት የሚቆም ሰው እንሁን:: አላህ ይወፍቀና. ♥️ https://t.me/Abadewamee

ድንበር ያልተበጀለት ቅርበት አላቸው። መስመር ያልተቀለመለት ኬላ አላቸው። ግን እዛ መቃም ደርሰው፣ ዓቅልን በሚያስት ደስታ ውስጥ ሆነው እንኳን ለአፍታ አልዘነጉንም። በሰላምታቸው መሃል “አሰላሙ ዓለይና” ብለው ከሀድራው ደበለቁን። ደግሞ “ወዓላ ዒባዲላሂ ሷሊሂን” አሉና ሙቀረቦቹን ለዩ። የወዳጃቸውን ምክርም ተቀብለው ይከብዳቸዋል የተባለውን ሊያግራሩልን ላይ ታች ደፋ ቀና፣ መለስ ቀለስ አሉ። መቼም ሲፋቸው አግያሩን መጥረግ፣ ጥኑውን ማግራት ነው። ከዛ ሹመት መልስም እጃቸውን አንስተው ለኛው ሲያለቅሱ ያድራሉ። #እኛም_ኹዝቢዬዲ_እያልን_እንማልዳለን። እንባጉታለን። እንዲህ ያለ ውድ ሰነድ፣ የማይበጠስ ገመድ፣ የማይላላ ሰንሰለት ከርሳቸው ለኛ ሊዘረጋልን #ተወለዱ፡፡ 💥 «አላሁመ ሶሊ ዓላ መን ወሰለ ኢላ ማ ለም የሲል ኢለይሂ ነብዩን ሙርሰል ወላ መለኩን ሙቀረብ-የተሾመ ነብይ፣ የተቃረበ መልአክ እንኳ ያልደረሰበት የቅርበት ማዕረግ ላይ በደረሱት የላይ ገንዳው ዘማችህ ላይ ሰለዋት አውርድ።» 💚💚💚 አላሁመ ሰሊ ወሰሊም አላ ነብይና ሙሀመድ ﷺ ♥️ @Abadewamee @Abadewamee

የዓለሙ ንጉሥ ሙሐመድ ኢማሙ!💚 የቃበ ቀውሰይን ሚስጥር (የቅርበት ጥግ) መካ ተወልዶ አርሽ ላይ የነገሰው፣ አህመድ ሲራጁ ባለ ሚዕራጁ! አርሽ ተጊጦ፣ ጀሊል ደግሶ፣ በሰማይ ቀበሌ የጌትዬው ኑር ተነ
የዓለሙ ንጉሥ ሙሐመድ ኢማሙ!💚 የቃበ ቀውሰይን ሚስጥር (የቅርበት ጥግ) መካ ተወልዶ አርሽ ላይ የነገሰው፣ አህመድ ሲራጁ ባለ ሚዕራጁ! አርሽ ተጊጦ፣ ጀሊል ደግሶ፣ በሰማይ ቀበሌ የጌትዬው ኑር ተነስንሶ፣ መለክ የተባለ ባ’ጭር ታጥቆ፣ ቡራቅ ያንን ዛት ለማፈናጠጥ ተቁነጥንጦ፣ አርዋሁ ሁላ ተደልቆ፣ የነብዬ ቀልብ በሂክማ እጣን ታጥኖ፣ ከውኑ ለልቅናቸው ሸብ ‘ረብ ባለበት የኢስራእና ሚዕራጅ ሌሊት ሲድረቱል ሙንተሃ ሲደርሱ አጃቢያቸው ሩሑል አሚን ሰይድ ጂብሪል ዓ.ሰ ቆሙ። የጂብሪል ወዳጅ ያ’ላህ ባለሟል ሰይዲ ጀማሉል ጀማል! ይሄኔ ነብዬ ﷺ ወዳጃቸውን የማይዘነጉ፣ የያዛቸውን እጅ የማይለቁ ናቸውና «እዚህ ቦታ ላይ ትተኸኝ ትሄዳለህን?» ብለው ጠዬቁት። ጂብሪልም፡- «አንድ ጣት ያህል ወደፊት ብራመድ በጌታዬ የጀላል ኑር እቃጠላለሁ፤ እከስማለሁ፣ ይህንን ቦታ ከአንተ ሌላ ማንም ሊያልፈው አልተፈቀደም። አንተ ተራመድ አልፈህ ግባ፣ እለፍ ተቀደም» አላቸው። ዘመን እና ቦታ በማይቆጠርበት፣ አቅጣጫ በማይዋሰንበት፣ መላእክት እንኳ ሊያዩት በማይችሉት የመለኮት ቅርበት «ቃበ ቀውሰይኒ አው አድና» (የሁለት ቀስት ያህል ወይም ከዚያ በላይ የቀረበ) ቦታ ላይ ብቻቸውን ቆሙ። መወደዱንማ ኑህም ተወደደመወደዱንማ ኢሳም ተወደደ ያለ ነቢ የለም በአርሽ የሰገደ! 💚💚💚اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَـــلِّمْ عَلَىٰ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ ﷺ💯💕💞💕

💚የረቢእ ስጦታ🖤 🤍 የተንቢ አባኖ ♥️ መቼም አላህ (ሱ.ወ) በዚህ ልዩ ወር የሰጠንን ስጦታ ቆጥረን አንጨርሰውም የስጦታው ሁሉ ስጦታ ካኢናቱን ሁሉ ለእርሳቸው ሲል ያስገኘላቸው ታላቁ ነብይ مُ
💚የረቢእ ስጦታ🖤 🤍 የተንቢ አባኖ ♥️ መቼም አላህ (ሱ.ወ) በዚህ ልዩ ወር የሰጠንን ስጦታ ቆጥረን አንጨርሰውም የስጦታው ሁሉ ስጦታ ካኢናቱን ሁሉ ለእርሳቸው ሲል ያስገኘላቸው ታላቁ ነብይ  مُحَمَّد ﷺ  የተወለዱበት ወር ነው     የፊታችን አሁን ያለንበት ወር ደግሞ እጅግ ትልቅ ቀን ነው የአለማቱ ኑር  የካኢናቱ ሁሉ አለቃ የሆኑት ነብያችን ሀቢባችን مُحَمَّد ﷺ የተወለዱበት ወር ከመሆኑ ባሻገር ብዙሀኑ #የጉራጌ_ህብረተሰብ_ከመብረቅ_አምልኮ_ወጥቶ_ወደ_ዲነል_ኢስላም_ለመምጣት_ሰበብ_የሆኑት, ከጉራጌም አልፈው ለመላው #ሀበሻ_ብርሃን_የሆኑት, ሲራራቸውን ከኸለቃቸው ኻሊቃቸው ውጪ ማንም ያላወቀው የቃድርያን ጦሪቃ ፍንትው አድርገው ያዛኸሩ ተከትብው የተያዙ 286 ኪታቦችን ለዑማው ያበረከቱ (ከነሱም ውስጥ የተውሂድ ኪታብ, ቁርአን ተፍሲር, የአመት ሙሉ ኹጥባ,  መጅሙእ የሰለዋት መድብል, የሠይድ ባኡ ሳኒ መናቂብ, እጅግ ብዙ የዱኣ ተወሱላት ኪታቦች, ቁጥር ስፍር የሌላቸው የመንዙማ ኪታቦች ይገኙበታል) ቸር ለጋሹ ታላቁ፦ #የአብሬት_ሸይህ ሸምሰ'ዲነል አብሬትይ (አበል ራሙዝ ) ቀደሰሏሁ ሲረሁ የተወለዱበት ቀን ነው::              የተወለዱት በረቢእ 3 ኸሚስ ቀን ሲሆን እሳቸውም አብሬት ከነበሩበት ወቅት ጀምሮ ሙሪዶቻቸው ረቢእ በገባ የመጀመሪያው ኸሚስ አባባ የተወለዱበትን ቀንን በማስታወስ ቀኑን መውሊድ በማውጣት ያሳልፋሉ::    🙏እንኳን ለዚህ ታላቅ ቀን አደረሳቹ♥️ https://t.me/Abadewamee

የሶሓባዎች መተሳስብና ፍቅር አቡ ጀህም ኢብኑ ሑዘይፋ የሚከተለውን ገልጸዋል፦ “በየርሙክ ጦርነት በውጊያ ማዕከል ላይ የነበረውን አጐቴን መፈለግ ጀመርኩ፡፡ ለርሱም ጥቂት ውሃ ይዤለታለሁ፡፡ ለመሞት ሲያጣጥር ደረስኩበት፡፡ ያለኝን ጥቂት ውሃ ለመስጠት ተጠጋሁት፡፡ ከጐኑ ግን በከፍተኛ ሁኔታ የቆሰለ ተዋጊ ያቃስታል፡፡ ፊቱን አዞረብኝ፡፡ ለርሱ አጠጣው ዘንድም አመለከተኝ፡፡ ውሃውን ይዤ ወደግለሰቡ ሄድኩ። ሂሻም ኢብን አቢል-ዓስ ነበር፡፡ ገና ሳልጠጋው ሌላ ድምጽ ራቅ ካለ ቦታ ተሰማ፡፡ ሂሻም ወደዚያው እንድሄድ አመለከተኝ፡፡ ሄድኩ፡፡ ግን አርፏል፡፡ ወደ ሂሻም ተመለስኩ እርሱም ተሰውቷል፡፡ ወደ አጐቴ ሄድኩ እርሱም ጓደኞቹን ተከትሏል፡፡'' አላህ አክበር! በሐዲስ ድርሳናት በርካታ ታሪኮች ተጠቅሰዋል፡፡ ሶሓባዎች በሞት አፋፍ ላይ ባሉበት ወቅት እንኳ ከራሳቸው ይልቅ የወንድሞቻቸውን ደህንነት የሚያሰቀድሙ ነበሩ፡፡ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمْ وَرَضُوا عَنْهُ
አላህ በእነርሱ ወዷል፤ እነርሱም በእርሱ ወደዋል
❤️‍🩹 𝐉𝐨𝐢𝐧 @Abadewamee 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄 @Abadewamee

ዑመር (ረ.ዐ) አቡበክርን we all is, ለመቅደም ያደረጉት ጥረት ታሪኩን ራሳቸው ዑመር ረ.ዐ→ ያወሱልናል፡- ‹‹ከዕለታት አንድ ቀን የአላህ መልዕክተኛ ﷺ☆ #ለፊሰቢሊላህ” መዋጮ ጠየቁ፡፡ በወቅቱ ገንዘብ ነበረኝ፡፡ እናም (ለነፍሴ) እንዲህ አልኩ፡፡ “አቡበክር (ረ.ዐ) በተደጋጋሚ #በአላህ_መንገድ_ላይ ገንዘብ በማውጣት በልጦኛል፡፡ ዛሬ ግን በአላህ ፈቃድ ልበልጠው ይገባል፡፡ ምክንያቱም በቂ ገንዘብ አለኝ፡፡” በዚሁ ሐሳብ ተሞልቼ ወደ ቤቴ ሄድኩ፡፡ ያለኝን ንብረት ለሁለት ከፈልኩ፡፡ ግማሹን ለቤተሰቤ ስተው ቀሪውን ይዤ ወደ መልዕክተኛውﷺ ሄድኩ፡፡ የአላህ መልዕክተኛምﷺ :-“ዑመር ሆይ አሉኝ! ለቤተሰብህ የተውከው ነገር አለን?” በማለት ጠየቁኝ፡፡ ዑመርም “አዎ! የአላህ መልዕክተኛﷺ አልኩ፡፡ “ምን ያህል?” አሉኝ፡፡ ግማሽ ያህሉን ትቻለሁ፡፡” አልኳቸው፡፡ ወዲያውም አቡበክር ገንዘባቸውን ተሸክመው መጡ፡፡ ያላቸውን ንብረት ይዘው እንደመጡ ተረዳሁ። "አቡበክር ሆይ! ለቤተሰብህ ምን ተውክላቸው" በማለት ነቢዩ'ﷺ ጠየቁት፡፡ “አላህንና መልዕክተኛውን ትቼላቸዋለሁ።” አሉ - ታላቁ አቡበክር፡፡ ረ.ዐ›› ዑመር ከዚያ ዕለት ወዲህ ማረጋገጣቸውን ገልጸዋል፡፡ #አቡበክርን_ለመብለጥ_እንደማይችሉ። አላህ አላህ! በርግጥ በበጐ ሥራ መሽቀዳደም የሚፈቀድ ብቻ ሳይሆን የሚበረታታም ነው፡፡ አላህ በቁርአን እንዲህ ብሏል፡- فَاسْتَبِقُوا الْخَيْرَاتِ ) ‹‹በጎ ሥራዎችንም (ለመሥራት) ተሽቀዳደሙ፤›› (አል - ማኢዳህ + 48) 𝐉𝐨𝐢𝐧 @Abadewamee 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄 @Abadewamee

እከሌ የእከሌ ልጅ ባንቱ ላይ ሰለዋት አውርዷል ተብሎ ስምህ የዓለማቱ እዝነት፣ ነቢይ ﷺ ፊት መነሳቱ ምንኛ ያማረ ነው…. 🥰 🤍اللهم صلِ و سلم  على سيدنا محمد ﷺ @Abadewamee @Abadewamee

#ሰሉ_አለ_ነቢ 💚💚💚اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَـــلِّمْ عَلَىٰ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ ﷺ💕

ድንቅ ምላሽ፦ አንድ ቀን ለሰይድና ዑመር ኢብን አል'ኸጣብን (ረ.ዐ) አንድ ሰው ይመጣና፦ «ዕድሜዋ በጣም የገፋ እናት አለችኝ ሁሌም ተሸክሜያት እዞራለሁኝ ማንኛዉንም ጉዳይዋን ሁሉ የምትፈጽመዉ ጀርባዬ ላይ ሆና ነዉ፡፡ እንዲህ በማድረጌ እሷ ከኔ ላይ ያላትን ሀቅ ሁሉ የተወጣሁ አይመስልዎትም? ሲል ጠየቀ፡፡ ዑመር ረ.ዐ. «ፈፅሞ ሀቋን አልተወጣህም እሷ ያኔ ስንት ድካም አግኝቷት ስታሳድግህ ያንተን ዕድገት እየተመኘች እሷ ሳትበላ አንተን እያበላች፣ (ልጄ ያድግ ይሆን) እያለች እየተጨነቀች ነዉ ያሳደገችህ፡፡ አንተ ግን ይህን ዉለታ ለመካስ ስትጥር (ከዚች አሮጊት መቼ ነው በሞት የምገላገለው ይሆን?) እያልክ ነዉ» አሉት፡፡ ያአላህ! 😢 𝐉𝐨𝐢𝐧 @Abadewamee 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄 @Abadewamee

"ከሶላትህ ከተዳከምክ ቁርአንን ችላ ካልክና ከዚክር ከተዘናጋህ በኋላ የሐዘንና ጭንቀት  ወታደሮች ቢወሩህና ቢያሹህ ነፍስህን እንጂ  ማንንም እንዳትወቅስ።

ሰዎች ያሰቡልኝን አይነት አወዳደቅ ያልወደኩት #አላህን_ስለተደገፍኩ ነው❤️‍🩹

የሞት ቀናችን ዛሬ ይሁን ነገ ፣አሁን ይሁን ወደፊት #ከኛ_የሚጠበቀው_ተረጋግቶ መኖር ነው 😊