en
Feedback
Yekatit 12 Hospital for Community

Yekatit 12 Hospital for Community

Open in Telegram
210
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
photo content

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ህዳር 18 / 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) በሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ ስሰጥ የነበሩ ሁለት ትትልቅ ስልጠናዎ ተጠናቀቁ። የመጀመሪያው ከ15/04/2016
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ህዳር 18 / 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) በሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ ስሰጥ የነበሩ ሁለት ትትልቅ ስልጠናዎ ተጠናቀቁ። የመጀመሪያው ከ15/04/2016 - 16/04/2016 ለየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮልጅ ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው የድንገተኛ አደጋዎች መከላከል ላይ ያቶከረ ስልጠና አመርቂ እንደነበር ተጠቁሟል ። ስልጠናው የተሰጠው ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ እንዲሁም ድንገተኛ አደጋዎች መካከል ኮሚሽን በመጡ ባለሙያዎች ነው። ስልጠናው የቆየው ለሁለት ቀናት ሲሆን በርካታ የተቋሙ ሰራተኞች ተሳትፈውበታል። ስልጠናውም በፁሁፍና በተግባር የታገዘ ሲሆን በተለይ በተቋማችን ውስጥ የአደጋ ጊዜ መውጫ ፣ የእሳት ማጥፊያ በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን አድርጓል። አደጋ በየትኛው ጊዜ እንደሚመጣ አይታወቅም ያሉት ሰልጣኞቹ ሁሉም ሰው ራሱን በተለያየ መልኩ ራሱን ማዘጋደት ይኖርበታል ተብለዋል። ሁለተኛው ስልጠና በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የፅዳት አገልግሎት የምግ ቤት እና የላውንደሪ አገልግሎት ለሚሰጡ ባለሙያዎች በአይነቱ ጥሩ የሆነ ስልጠና መውሰዳቸውን ታውቋል። ስልጠናው አበበች ጎበና እናቶችና ህፃናት የህክምና ማዕከልን ያካተተ ሲሆን በርካታ ሰልጣኞች ተሳትፈውበታል ስልጠናው የተሰጠው በሶስት ዙር ለሶስት ተከታታይ ቀናት ሲሆን ከ50 በላይ ለሚሆኑ የተቋሚ አገልጋዮች ተደራሽ ለማድረግ ተችሏል። ስልጠናው ያተኮረው በሽታ መከላከል ፣ የምግብ አያያዝ የአልባሳት አያያዝና የደንበኛ አገልገሎት አያያዝን በተመለከተ ሰፊ ዳሰሳ ተደርጋል። ስልጠናው አጠቃላይ infection prevention ላይ ያቶከረ ሲሆን በተለይ በተቋሙ ለሚሰጡ ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎቶች ትልቅ እገዛ ያደርጋል ተብሏል። "ሰላም አይለየን"

photo content
+8

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ህዳር 17 / 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በርካታ የመማሪያ መፅሐፍቶች በስጦታ መልክ ተበረከተለት። ሜዲካል ኮሌዱ
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ህዳር 17 / 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በርካታ የመማሪያ መፅሐፍቶች በስጦታ መልክ ተበረከተለት። ሜዲካል ኮሌዱ ከህክምና አሰጣጡ ጎን ለጎን የሰለጠኑ የጤና ባለሙያዎችን በማፍራት ረገድም ቢሆን  ግንባር ቀደም ተቋም እንደሆነ ይታወቃል። በምህፃረ ቃሉ "GRS" በመባል የሚታወቀው የስደተኞች አገልግሎት ድርጅት ወደ 300 ( ሶስት መቶ ) የሚጠጉ የተለያዩ የመማሪያ መፅሃፍቶችን ለሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ  በስጦታ መልክ አበርክቷል። በምህፃረ ቃሉ "GRS" በመባል የሚታወቀው የስደተኞች አገልግሎት ድርጅት እነዚህን 300 የመማሪያ መፅሃፍቶችን ለተቋሙ ሲያበረክት ከተቋሙ ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ እንደሚያጠናክርም ተጠቁሟል። የሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ ዋነ ናኘሮቮስት ዶ/ር ኤልያስ ተዋበ እንዲሁም የሆስፒታሉ ሜዲካል ኮሌጁ የአካዳሚክና ምርምር ም/ኘሮቮስት ዶ/ር መረርቱ ተመስገን በመፅሃፉ ርክክብ ስነስርዓት ላይ በመገኘት መፃሃፍቶችን ተረክበዋል።

photo content
+3

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሳስ 16/ 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) "አዲስ ጉዞ ድርጅት" ለየካቲት 12 ሆስታል ሜዲካል ኮሌጅ ዘመናዊ የፊዚዮ ቴራፒ መገልገያ እቃዎች እና ዊል
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሳስ 16/ 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) "አዲስ ጉዞ ድርጅት" ለየካቲት 12 ሆስታል ሜዲካል ኮሌጅ ዘመናዊ የፊዚዮ ቴራፒ መገልገያ እቃዎች እና ዊልቸር በስጦታ መልክ አበርክተዋል። የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ እንደሚታወቀው በሃገር አቀፍ ደረጃ ለማህበረሰቡ ግዙፍ የጤና አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ትልቅ ተቋም ነው በመሆኑም የተለያዩ ድርጅቶችም በተለያየ መልኩ አብረውት እየሰሩ ይገኛሉ። አዲስ የጉዞ ድርጅትም አንዱ ከተቋሙ ጋር መልካም ግንኙነት ያለው ድርጅት ሲሆን ብዛታቸው 3 ዘመናዊ የፊዚዮ ቴራፒ ማሽን በስጦታ እና 5 ህመምተኛ ማመላለሻ ዊልቸር በማደስ ለሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ በስጦታ መልክ አበርክቷል። አዲስ ጉዞ ድርጅት ከዚህ በፊትም ለሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ በርካታ የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችን በስጦታ መልክ ማበርከቱ ይታወሳል።  ሶልያና ደጀኔ የሜዲካል B አስተኝቶ ህክምና አስተባባሪ የሆኑት እነዚህን የህክምና መገልገያ እቃዎች መምጣት ትልቁን አስተዋፆ ያደረጉ ሲሆን አዲስ ጉዞ ድርጅት ከዚህ ቀደምም በርካታ የህክምና መገልገያ እቃዎችን አበርክተውልናል ብለዋል። አያይዘውም ድርጅቱን ላበረከቱት ስጦታ በሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ ስም አመስግነዋል።                     "ሰላም አይለየን"

photo content
+8

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሳስ 7/ 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) በካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ላሉ በጥበቃ አገልግሎት ለሚያገለግሉ ባልደረቦቻችን ለሁለት ቀን ሲሰጥ የ
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሳስ 7/ 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) በካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ላሉ በጥበቃ አገልግሎት ለሚያገለግሉ ባልደረቦቻችን ለሁለት ቀን ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል። በስልጠናው ላይ  የተለያዩ ግንዛቤዎችን አግኝተናል ያሉት ሰለሰጣኞች ስራችንን በአግባቡ እንድንሰራ የተለ መነሳሳትን ፈጥሮልና ብለዋል። በሆስፒታ ሜዲካል ኮሌጁ ለሁለት ቀናት ሲሰጥ  የነበረው ስለሰጠና እጅግ ጠቃሚ እንደነበር ተሳታፊዎቹ ገልፀዋል አያይዘውም ይህ ስልጠና በተቋሙ ውስጥ ስንሰራ የእኔነት ስሜት እንዲሰማን አድርጓል ብለዋል። ስልጠናው በሽታን እንዴት ቀድመን መከላከል  እንደሚቻል ፣ የመጀመሪያ እርዳታ አሰጣጥ የስነምግባር መርሆዎችና ደንቦች ፣ የተገልጋይ እርካታን አካቷል። በስልጠናው የመዝጊያ ኘሮግራም ላይ የተገኑት የሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጂ የአስተዳደርና ልማት ም/ኘሮቮስት የሆኑት አቶ አለሙ ክብረት እንደገለፁት እንደዚህ አይነት ጠቃሚ ስልጠናዎች በፅዳት ሰራተኞችና ሌሎች ሴክተሮች ላይ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመዋል።                "ሰላም አይለየን"

photo content
+8

photo content
+9

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሳስ 06 / 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ጥበቃዎች በዛሬው ዕለት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጣቸው። የግን
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሳስ 06 / 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ  ጥበቃዎች በዛሬው ዕለት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጣቸው። የግንዛቤ ማስጨበጫ ኘሮግራሙ ለሁለት ቀን የሚቀጥል ሲሆን የጥበቃ አገልግሎት የሚሰጡ የተቋሙ ባልደረቦች ለሁት ተከፍለው ሁሉም የሚሳተፉበት ይሆናል ተብላል። ስልጠናው የሚያካትተው የግንዛቤ ትምህርት ፣ የደንበኛ አያያዝ ፣ የስነምግባር መርሆዎች እና ከግቢው ማህበረሰብ ጋር እንዴት ተስማምቶ መስራት እንደሚገባ ያጠቃልላል። የህክምና አገልግሎት ለማህበረሰቡ ሲሰጥ የሁሉም ሃላፊነትን የሚጠይቅ በመሆኑ የጥበቃም አስተዋጽኦ እጅግ የጎላ ነው ተብሏል። በስልጠናው ላይ የተገኙት ዶ/ር ኤልያስ ተዋበ የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ዋና ኘሮቮስት እንደገለፁት የጥበቃ አስተዋጽኦ ለተቋማችን እጅግ የጎላ ነው ብለዋል  አያይዘውም በተለይ ደንበኞችን ስናስተናግድ በአክብሮት እንዲሆን ሲሉ ገልፀው ከእናንተ ጋር በመስራታችንም ደግሞ ታላቅ ክብር ይሰማናል በማለት ገልፀዋል። የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የአስተዳደርና ልማት ም/ኘሮቮስት የሆኑት አቶ አለሙ ክብረት በስልጠናው ላይ በመገኘት ለተቋሙ ጥበቃ አባላት ጥልቅ የሆነ ስልጠና ተሰጥተዋል። ም/ኘሮቮስቱ በስልጠናው ላይ አፅኖት ሰጥተው ከተናገሩት መካከል ደንበኛ ክቡር ነው እዚህ ተቋም የሚመጣ ማንኛው ደንበኛ እኩል በሆነ መልኩ በክብር ሊስተናገዱ  ይገባቸዋል ብለዋል። በተቋሙ የሚመጡ ታካሚዎች ድነው የሚወጡት በሃኪና ነርስ ጥረት ብቻ ሳይሆን በዕናንተም አስተዋጽኦ ጭምር በመሆኑ ሁላችንም ደንበኞቻችንን በእኩልና በስነምግባር ልናስተናግዳቸው ይገባል በማለት ተናግረዋል።                   "ሰላም አይለየን"

photo content
+9

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሳስ 04 / 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የኤች አይቪ የተጋላጭነት ልየታ እና ምርመራ ( HRST AND TES
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሳስ 04 / 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ  የኤች አይቪ የተጋላጭነት ልየታ እና ምርመራ ( HRST AND TESTING ) ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ። ለሶስት ተከታታይ ዙር በተሰጠው አይቪ የተጋላጭነት ልየታ እና ምርመራ ስልጠና 100 (አንድ መቶ) ለሚደረሱ የተቋማችን ሰራተኞች ስልጠናው ተሰጥቷል። ስልጠናው በተለይ የበለጠ ለኤች አይቪ ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍል ውስጥ በመግባት ተጋላጮችን የመመርመርና የመለየት ስራ ለመስራት እጅጉን እንደሚጠቅም ተጠቁሟል። የዚህ ስልጠና ዋና አላማ ለኤች አይቪ ተጋላጭ የሆኑ የማህቀረሰብ ክፍል  ለይቶ በመመርመር  ፖሰፒቭ የሆኑ ሰዎችን የማግኘት እድልን  መጨመር ( Increasing Case detection) ነው።

photo content
+1

photo content
+3

photo content
+9

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሣሥ 4/ 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የስነ አዕምሮ ዲፓርትመንት "ሰላም የህፃናት መንደር ማዕከል" በመገኘት
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሣሥ 4/ 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን) የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የስነ አዕምሮ ዲፓርትመንት "ሰላም የህፃናት መንደር ማዕከል" በመገኘት የጤና ድጋፍ በተቋማችን የስነ-አዕምሮ ህክምና በተለየ መልኩ ለማህበረሰቡ እየተሰጠ ይገኛል ዲፓርትመንቱ ከተመላላሽ ህክምና እስከ አስተኝቶ ህክምና በስፋት እየሰጠ ይገኛል። የስነ አዕምሮ ዲፓርትመንት በየአመቱ ለማህበረሰቡ የሚጠቅሙ በጎ ተግባራት ስራዎችን  ያከናውናል። በዛሬው ዕለት የተቋማችን የስነ አዕምሮ ዲፓርትመንት "ሰላም የህፃናት  መንደር ማዕከል" በመገኘት የተለያዩ  የጤና ድጋፎችን አድርጎ ተመልሷል። ከተደረጉ ድጋፎች መካከል የተለያዩ የስነ አዕምሮ የልየታ እና ህክምና እንዲሁም ጠቃሚ የሆነ የግንዛቤ ማስጨበጫ የጤና ትምህርት ተደርጓል። በነበረው የጤና ድጋፍ "ሰላም የህፃናት ማረፍያ ማዕከል" ሃላፊዎች ስለተደረገላቸው ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ብዙ ጊዜ ታካሚ ወደ ሃኪም ቤት ይሄዳል እንጂ ሃኪም ወደ ታማሚ አይመጣም ያሉት የማዕከሉ ሃላፊዎች ለየካቲት 12 ሆስፒታል ያላቸው አክብሮት ገልፀዋል። በመጨረሻም እንደዚህ አይነት በጎ የማህበረሰብ አገልግሎት መስጠት ለህሊና እረፍና ለመንፈስ እርካታን ይሰጣልና ሁሉም ሰው የሁልጊዜ ተግባሩ ሊያደርገው ይገባል ተብሏል። ይህን ነፃ የጤና አገልግሎት ለሰጡ ለካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የስነ አዕምሮ ዲፓርትመንት የከበረ ምስጋና ይገባል።                   " ሰላም አይለየን"

photo content
+9

photo content
+1

photo content
+9