ዝጉ መንገድ ሚዲያ
Open in Telegram
''ዝጉ መንገድ ሚዲያ '' የዚህ ቻናል ዓላም ተከታዮቹን በመንፈሳዊ ሕይወታቸው፤ በግል ስብዕናቸው፤ በቢዝነስ ሕይወታቸው እና በሙያዊ ሕይወታቸው ላይ የሚያስፈልጋቸውን እውቀትና ክህሎት እንዲሁም ጥበብ ለማጎልበት የሚሠራ ድንቅ ቻናል ነው። የ ''ዝጉ መንገድ ሚዲያ''አስተማሪ ቪዲዮችን ለምትፈልጉ ከታች ያለውን ሊንክ ተጫኑ!!! https://youtu.be/OIhbFJUy0Nw?si=6hhr3VOes5XEnZO
Show more261
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
261
#ሰውን ለመርዳት ጥሩ ነገር ማሰብ ብቻ በቂ ነው።
ሰዎችን የምንረዳባቸው መንገዶች እጅግ ብዙ አማራጮች አሉን።
ከእናንተ መካከል አንድ አይነ ሥውር ሰው ወደ ጉድጓድ ገብቶ ሊወድቅ ሲል እጁን ዘርግቶ የማይደግፈው ማን ነው? ታድያ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በልቡናቸው ታውረው ወደ ሲዖል ጉድጓድ ለዘለዓለም ሲወድቁ እንደ ምን እጃችንን የበለጠ አይዘረጋም?ወገኖቼ!በነፍስም በሥጋም የታመመ ሰውን ስታዩ "ይህ የእኔ ሥራ አይደለም: የቀሳውስትና የመነኮሳት ሥራ እንጂ፡፡ ምክንያቱም ሚስት አለችኝ: ልጆችንም አሳድጋለሁ" አትበሉ፡፡
እስኪ ምሳሌ መስዬ ልጠይቃችሁ እናንተም መልሱልኝ፡፡ አንድ ትልቅ በወርቅ የተሞላ ሳጥን ወድቆ ብታዩ "ይህ እኔን አይመለከተኝም፡ ሌሎች መጥተው ያንሡት እንጂ" ትላላችሁን? ግራ ቀኛችሁን አይታችሁ በፍጥነት የምታነሡት አይደለምን?
ይህ ወደ ዘለዓለም ጉድጓድ እየወደቀ ያለው ወንድማችሁም ከዚያ ወርቅ በላይ ውድ የእግዚአብሔር ሀብት ነውና አንሡት እንጂ የበለጠ እንዲወድቅ አትግፋት፡፡ እግዚአብሔር ይህን በተመለከተ በአፈ ያዕቆብ እንዲህ ብሏልና፡- "ወንድሞቻችን ሆይ! ከእናንተ ወገን ከጽድቅ ወጥቶ የበደለ ቢኖር መክሮ አስተምሮ ከበደሉ የመለሰው ቢኖር ራሱን አንድም ወንድሙን ከሞት እንዳዳነ ይወቅ፡፡ የራሱን አንድም የወንድሙን ብዙ ኃጢአቱን እንዳስተሠረየ ይወቅ፡፡ አንድም የወንድሙን ነፍስ እንዳዳነ ይወቅ"(ያዕ.5:19-20)፡፡
@deacon mezmur niguse
261
የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት በ5 ዓቢይ ክፍል ይከፈላሉ።
ክፍል1
1. የወንጌል ክፍል
ወንጌል ማለት ኢቫንጌሊዩን ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን መልካም ዜና፣ የምስራች፣ ብስራት፣
ስብከት ማለት ነው። ወንጌላት አራት ሲሆን እነዚህም፦
1.1. የማቴዎስ ወንጌል
የስሙ ትርጉም = ማቴዎስ ማለት በሮማይስጥ ሀብተ አምላክ ማለት ነው። እንዲሁም የአምላክ
ስጦታ፣ ከቀራጭነት የተመረጠ ማለት ነው።
ጸሐፊዉ፦ ራሱ ቅዱስ ማቴዎስ ነው። ማቴ 1፡1
የተጻፈበት ዘመን፦ 42 ዓ.ም
የተጻፈበት ቦታ፦ ፍልስጤም ነው።
የተጻፈበት ቋንቋ፦ በዕብራይስጥ ነው።
የተጻፈበት ምክነያት፦
አይሁድ ለጠየቁት ጥያቄ መልስ
ጌታችን የአብርሃምና የዳዊት ዘር መሆኑን ለመግለጽ
ጌታችን አምላከ ነብያት መሆኑን ለመግለጽ
የነብያት ትንቢት በጌታችን መፈጸሙን ለማሳየት ነው።
የተጻፈላቸው ሰዎች፦ አይሁድ ዕብራዊያን ናቸው።
የማቴዎስ ወንጌል 28 ምዕራፎች 1068 ቁጥሮች ሲኖሩት በ6 ዓበይት ክፍሎች ይከፈላል።
1.2. የማርቆስ ወንጌል
የስሙ ትርጉም = ማርቆስ ማለት ካሕን፣ ልዑክ፣ ታላቅ፣ መዶሻ ማለት ነው።
ጸሐፊዉ= ራሱ ቅዱስ ማርቆስ ነው። ማር 1፡1
የተጻፈበት ዘመን = 44 ዓ.ም
የተጻፈበት ቦታ = በሮም ነው።
የተጻፈበት ቋንቋ = በሮማይስጥ ነው።
የተጻፈበት ምክነያት = ሮማዉያን በዘመናቸው ገናና እኛ ብቻ ነን በማለት ይናገሩ ነበርና የጌታችንን
ኃያል፣ ገናና ተአምራቱን ለመግለጽ ነው።
አገረ ስብከቱ = በግብጽ እስክንድርያ በሮምና ሊብያ ናቸው።
የተጻፈላቸው ሰዎች = ለሮማዉያን ነው።
የቅዱስ ማርቆስ ወንጌል 16 ምዕራፎች 678 ቁጥሮች ሲኖሩት በ6 ዓበይት ክፍሎች ይከፈላል።
1.3. የሉቃስ ወንጌል
የስሙ ትርጉም = ሉቃስ የሚለዉ ቃል ሊካኖስ ከሚለው የላቲን ቃል የተገኘ ሲሆን መብራት ማለት ነው።
ጸሐፊዉ= ራሱ ቅዱስ ሉቃስ ነው። ሉቃስ 1፡1
የተጻፈበት ዘመን = ከ54-57 ዓ.ም
የተጻፈበት ቦታ = በግሪክ መቄዶንያ ነው።
የተጻፈበት ቋንቋ = በግሪክ ጽርዕ ነው።
የተጻፈበት ምክነያት = ቴዎፍሎስ የተባለ የሮም መኮንን በቃል የተማረዉን የክርስቶስን ነገር
እርግጡን/በጥልቀት በሚገባ/ እንዲያዉቅ ለማድረግ ነው።
የተጻፈላቸው ሰዎች = ቴዎፍሎስ ለተባለ የሮም መኮንን ነው።
የቅዱስ ሉቃስ ወንጌል 24 ምዕራፎች 1151 ቁጥሮች ሲኖሩት በ8 ዓበይት ክፍሎች ይከፈላል።
1.4. የዮሐንስ ወንጌል
የስሙ ትርጉም = ዮሐንስ ማለት ፍስሐ ወሐሴት ጸጋ እግዚ አብሔር ማለት ነው። እንዲሁም ፍቁረ እግዚእ
/ጌታ ይወደው የነበረ/፣ ወልደ ነጎድጓድ፣ ቦኤኔርጌስ የነጎድጓድ ልጆች ማር 3፡17፣ ታዖሎጎስ/ ቴዎሎጎስ/
ነባቤ መለኮት ስለ መለኮት የሚናገር፣ አቡቀለምሲስ ባለ ራዕይ፣ ቁጽረ ገጽ/ ፊቱ በሀዘን የተቋጠረ/ ይባላል።
ጸሐፊዉ= ራሱ ቅዱስ ዮሐንስ ነው። ዮሐ. 21፡20-24
የተጻፈበት ዘመን = በ90 ዓ.ም
የተጻፈበት ቦታ = በኤፌሶን በኤጅያን ደሴት ነው።
የተጻፈበት ቋንቋ = በዮናኒ/ በጽርዕ ቁንቋ ነው።
የተጻፈበት ምክነያት = ሰው ሁሉ የክርስቶስን የባሕርይ አምልካነት አምኖ እንዲድን፣ ይመጣል የተባለው
መሲህ ክርስቶስ መሆኑን ለመግለ፣ ክርስቶስ የእግዚ አብሔር የባሕርይ ልጅ እግዚ አብሔር መሆኑን
ለመግለጽ ነው።
አገረ ስብከቱ = ከቅዱስ ጲጥሮስ ጋር በኢየሩሳሌምና አከባቢዋ፣ በአንጾኪያና አከባቢዋ፣ በሎዶቂያ፣
በእሲያ፣ በኤፌሶን ሰብኳል።
የተጻፈላቸው ሰዎች = ለኤፌሶን ምዕመናን ነው።
የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል 21 ምዕራፎች 880 ቁጥሮች ሲኖሩት በ7 ዓበይት ክፍሎች ይከፈላል።
261
ጓደኛ እንዴት ልምረጥ?
ይህ ጥያቄ ከአንድ እህታችን የተጠየቀ ጥያቄ ነው። ነገር ግን የሁላችን ጥያቄ ነው ብየ አስባለሁ። ጓደኛየ አህዛብ ነው ፤ ጓደኛየ መናፍቅ ነው እኔ ኦርቶዶክስ ነኝ እንዴት እናድርግ የሚሉም ጥያቄዎች አብረው ተነስተዋል።
እስኪ እናንተስ ምን ትላላችሁ????
261
ውሳኔ እና ሕይወት
ውሳኔ ማለት እግዚአብሔር የሰጠንን ነፃ ፈቃድን ተጠቅሞ አንድን ነገር መምረጥ ማለት ነው።
ውሳኔ ለሕይወት በጣም ወሳኝ እና መሰረት ነው።
ውጤቱ ጥሩ ከሆነ በጣም አስፈላጊ ነው።
የምንወስናቸው ከትንንሽ ውሳኔዎች ጀምሮ በሕይወታችን ላይ ተጽዕኖ አላቸው ።
ለውሳኔ አስፈላጊ የሆኑ ክህሎቶች አሉ እነሱም፦ ቁርጠኝነት፣ ያለ አድሎ መሆን አለበት/ማለትም ከስሜት እርቀን በእግዚአብሔር መንገድ መጓዝ /፣ማስተዋል/ማገናዘብ/፣ነገሮችን ሚዛን ላይ አድርጎ ማየት ወይም ውጤቱ የሚያመጣውን ነገር በማሰብ፣ ኃላፊነት መሰማት፣ አርቆ ማየት የወደፊቱን፣🙏ጸሎት🙏እንዲሁም በዋነኝነት ፈቃደ እግዚአብሔርን መጠየቅ፣ መንፈሳዊ መሆን፣ አባቶችን መጠየቅ፣ ውይይት፣ መታገስ ያስፈልጋል።
ውሳኔ አሳላፊ ወይም ድርሻ ያላቸው አካላት ፦ መንፈስ ቅዱስ የሚያሳየን፣ ህሊና/ስንወስን የሚሰማን ስሜት/፣ አእምሮ ፣ ጠባይ/ዝንባሌ፣ የምንኖርበት ማህበረሰብ እና ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናቸው።
የውሳኔ መመዘኛዎች
• ከሀይማኖት አንፃር
• ከእግዚአብሔር ፈቃድ አንፃር
• ከቅዱሳት መጽሐፍት አንጻር
• ጥቅሙንና ጉዳቱ ከሚያስከትለው አንፃር
• ከአድሎ የነፃ መሆኑን ማረጋገጥ
• ከማህበረሰቡ አንፃር
ውሳኔያች የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን የምናውቀው እንዴት ነው?
1,ውሳኔያችን የህሊና እረፍት ሲሰጠን፣
2,ከቅዱሳት መጽሐፍት ጋር የማይቃረን ከሆነ
3,አካሄዳችን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን በመመርመር
ውሳኔ በክርስቲያኖች ዘንድ መምሰል ያለበት በማስተዋል፣ በጥንቃቄ ፣ ዘላለማዊነት በማሰብ ፣በማንበብ እና በመጠየቅ መሆን አለበት።
ጸሐፊ ሰላም ተሰማ
https://t.me/dn_mez
261
ህይወት ስትከብድህ ,የሚያጨናንቁህ ነገሮች ሲበዙብህ, የምትለፍላቸው ሁሉ ነገሮች አልሳካ ሲሉህና ,አለም ፊቷን ስታዞርብህ እራስህን እንድትወድ የሚያደርጉህ 3 ነገሮች ይኸውልህ
1.ታጋሽ ሁን
2.ሰጪ ሁን
3.ለማንም የዋህ ሁን
በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ብትሆን እነዚህን 3 ነገሮች ካሉህ በፍፁም እራስህን አትጠላም
261
⚡️Acorns ቦትን በስልኮት በመጠቀም ብቻ በወር
100,000ሺ ብር በላይ ተከፋይ ይሁኑ 💸
🎁የ Acorns ቦት ጋር ልክ እንደገቡ የ 1000ብር ስጦታ ያገኛሉ በተጨማሪም 1 ሰዉ ወደ ቦቱ ሲጋብዙ በየቀኑ የ 50ብር ቋሚ ክፍያ ያገኛሉ
🔗ይህ የእርሶ የመጋበዣ link ነው ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ 👇👇
https://t.me/FreeEearnMoneyPay_Bot?start=r00143406750