BARAKA ብዕር
Open in Telegram
رَبِّ اشْرَحْ لِي صَدْرِي ﴿وَيَسِّرْ لِي أَمْرِي وَاحْلُلْ عُقْدَةً مِّن لِّسَانِي ﴿يَفْقَهُوا قَوْلِي كَلَّا ۖ إِنَّ مَعِيَ رَبِّي سَيَهْدِينِ ቻናሉን ሼር በማድረግ ይተባበሩን ። @baraka_bier
Show more2 702
Subscribers
-324 hours
+1677 days
+10830 days
Posts Archive
2 702
የተወዳጁን🌹 የነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) እና የኸዲጃ (ረ.ዐ)#እውነተኛና መሳጭ #የፍቅር💖 ታሪክ
#ክፍል 5
ታላቁ ሰው ወደ አጎቱ ቤት ተመለሰ። አቡ ጧሊብም ከእህቶቹና ከወንድሞቹ ጋር ቁጭ ብለው አገኙት።
አጎቱ በፈገግታ ተቀበሉትና፦ “ከኸዲጃ ከከባድ ስጦታ ጋር እንደላከችህ እገምታለሁ፣” አለው።
መሀመድም ሰ.ዐ.ወ፦ “አጎቴ ሆይ፣ አንድ ጉዳይ አለኝ፣” አለ።
አቡ ጧሊብም፦ “ምንድነው ጉዳዩ?” አለው።
ወጣቱም፦ “ሂዱና ኸዲጃን ለትዳር እንደምፈልጋት ቤተሰቦቿን ጠይቁልኝ፣” አላቸው።
የሙሀመድ አጎቶች ተያዩ። ከአቡ ጧሊብ በስተቀር ማንም ምንም ለማለት አልፈለገም።
አቡ ጧሊብም፦ “ልጄ ሆይ፣ ኸዲጃ እጅግ የተከበረች፣ የተወደደችና ገንዘብ ያላት ናት። ከአሁን በፊት ሁለት ባሎችን አግብታ በሞት የተነጠቀች፣ ገንዘባቸውን ወርሳ ምትኖር ሴት ናት።
በቅርቡም ታላላቅ ሹማምንቶች ለጋብቻ ጠይቀዋት እንቢ ያለች ናት። አንተ ደግሞ ምንም ንግድ የሌለህ፣ የእሷ ተቀጣሪ ነህ። እንዴት እራሷን አሳልፋ ትሰጥሃለች?” አለው።
“አጎቴ፣ አሁን ያልከው ሁሉ ልክ ነው። ግን ፍላጎቱ ከእኔ የመጣ አይደለም። ኸዲጃ እራሷ ናት ‘አስለምነኝ’ ያለችኝ፣” አለ።
አቡ ጧሊብም ባለማመን፦ “እንዴት?” አሉ።
መሀመድም ሰ.ዐ.ወ፦ “የጋብቻ ጥያቄ አቅርባልኝ። ሽማግሌ እንድልክ ተስማምቼ ነው የመጣሁት፣” አለ።
አቡ ጧሊብም፦ “ተው ልጄ፣ አትሸንገል። የኸዲጃ ንግግር እጅጉን ቦልት ነው፣” አሉ።
አቡ ለሀብም፦ “የወንድሜ ልጅ፣ አንተ ኸዲጃን ማግባት አትችልም። አትመጥንህምና የአረቦች መሳለቂያ አታድርገን፣” አሉ።
ሌላኛው አጎታቸው አባስ፦ “ለምንድን ነው ምትዘላብዱት? በአላህ ይሁንብኝ፣ ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ መካ ውስጥ እጅግ ውብና ጥሩ ስነ-ምግባር ያለው፣ በህዝቡ ዘንድ ‘ሙሀመድ አሚን’ — ታማኙ ሙሀመድ — የሚባል ስያሜ የተሰጠው ነው።
ታዲያ ኸዲጃ ለሱ በምን ነው የምትከብደው? ንግግርን ማጥላላት ምንም የሚጠቅም ነገር አይደለም። ተነሱ፣ እንሂድና የኸዲጃን ወላጅ እንጠይቅለት፣” አሉ።
መሀላቸው ፀጥታ ሰፈነ።
አክስታቸው ሶፊያ ሁኔታውን ለማረጋገጥ ወደ ኸዲጃ ቤት ሄደች።
እንደደረሰችም በሩን በዝግታ አንኳኳች። በሩን የከፈተችላት ኸዲጃ ነበረች።
“አርሂቢ!” ብላ በፈገግታ ወደ ውስጥ እንድትገባ ጋበዘቻት።
ከዛ የሚቀመስ ነገር ለማምጣት ኸዲጃ በተነሳች ጊዜ ሶፊያ እንዲህ አለች፦
“እኔ ልበላ ልጠጣ አልመጣሁም። ወንድሞቼ እየጠበቁኝ ነው። አንቺ ዘንድ የመጣሁት የሰማሁት ወሬ እውነት መሆኑን ላረጋግጥ ነው፣” አለቻት።
ኸዲጃ ረ.ዐ፦ “የመጣሽበት ወሬ በእርግጥ እውነት ነው። ቢሻችሁ ሸሽጉት፣ ወይ ይፋ አድርጉት። እኔው ጠይቄው ነው። እሱ አይደለም የፈለገው። ቢመጣ ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ ጋር ከመጋባት የሚከለክለኝ የለም፣” አለቻት።
ሶፊያም በኸዲጃ ንግግር በመገረም፦ “በአላህ ይሁንብኝ፣ ኸዲጃ፣ እውነት አለሽ። ሙሀመድን የመሰለ ውብ ሰው ‘አስለምነኝ’ ብትይ ምንም ነውር የለውም፣” አለቻት።
ኸዲጃም በሶፊያ ንግግር ተደስታ ውድ ቀሚስን አምጥታ አለበሰቻት። ከደስታዋ ብዛትም እቅፍ አድርጋ ሳመቻት።
ከዚያም ሶፊያ ዜናውን እንድትናገር ወደ ወንድሞቿ ሸኘቻት።
ከእነሱ ዘንድ እንደደረሰችም ፊታቸው በፈገግታ ተሞልቶ ተቀበሏት። ጥሩ ዜና ይዛ መምጣቷን ያወቁትም በውድ ልብስ አሸብርቃ ስለነበር ነው።
ወንድሟ አቡ ጧሊብም፦ “ምን ይዘሽ መጣሽ?” አላት።
እሷም፦ “ኸዲጃ እውነቷን ነው። በሙሀመድ ፍቅር ወድቃለች፣” አለቻቸው።
አ
..... ላ
.............. ለ
.................... ቀ
***ም!!!
➡️ክፍል #6 ይቀጥላል◌◌◌
🔗SHARE 🔗SHARE
┄┄┉┉✽»🌹✿🌹»✽┉┉┄┄
𝙟𝙤𝙞𝙣 & 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚🔗
👉👉 @baraka_bier
👉👉👉 @baraka_bier
𝙟𝙤𝙞𝙣 & 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚🔗
┄┄┉┉✽»🌹✿🌹»✽┉┉┄┄
2 702
ብዙ ነው ያየሁት!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
ከጊዜ ቀድሜ…
በዚህች አጭር ዕድሜ. . .
ብዙ ዐየሁ የማይታይ!
ብዙ አጣሁ የሚታይ
አፍርሶ እየሠራኝ፣ነቅሎ እየገጠመኝ፣
ምድር ከዘራችው፣የለም ያልገጠመኝ!
ብዙ ነው ያየሁት. . .
ሩቅ ነው የመጣሁት. . .
ብቻ በመንገዴ “ደንታ” ነው ያጣሁት!
.
@baraka_bier
2 702
#እታስቡ_እትጨነቁ_
አፍቅሬ ተከዳሁ። ተስፋ አርጌ አጣሁ አትበል። ከሷ ከሱ ከምትጠባበቅ/ቂ ከአላህ ተጠባበቅ/ቂ
ተወኝ፣ሰለቸኝ፣ተጠላሁ፣አትበል። አላህ ብቻ አይጥላችሁ። ከሰው ሳይሆን ከአላህ ብዙ ጠብቁ። ከፈጣራያችሁ እንጅ ከሰው ብዙ ተስፋ አታድርጉ።
አላህ ከሰውም ከሁሉም ብዙብዙ አለው። ስለዚህ ከእሱ ተስፋ አትቁረጡ። ሀሳባችሁ መስመር በሳተ ቁጥር ትጉ። ምኞታችሁ አላምር ብሎ እየራቀ ሲሄድ ልክ እንሰራራ። በተስፋ መቁረጥ መቃብር ላይ ነፍስ ዝሩ። የሞተ የሚባለው ተስፋው የሞተ ነውና አትሙት። አታስቡ አትጨነቁ
@baraka_bier
2 702
🌹 የተወደዱት የነብዩ ﷺ እና የኸዲጃ رضي الله عنها እውነተኛና መሳጭ የፍቅር ታሪክ
ክፍል 4
አጎቴ፣ አንተ እንደፈለክ ማድረግ ትችላለህ። እኔም የአንተን ትእዛዝ ለመፈጸም ዝግጁ ነኝ፣ አለ።
ከሻም መልስ በሁለተኛው ቀን፣ ታላቁ ሙሐመድ ﷺ ገላቸውን ታጥበው፣ አቡ ጣሊብ በገዙላቸው ልብስ ተውበው፣ ወደ ኸዲጃ ቤት ሄዱ።
ኸዲጃም እውነተኛ፣ ታማኝ፣ ፍትሐዊ፣ አዛኝና መልካም ሰሪ የሆነውን ታላቁን ወጣት፣ በውበቱ ላይ አዲስ ልብስ ተጎናጽፎ ስታየው ተደነቀች።
ከዚያም፦
“እንዲህ አምረህ የመጣኸው ከእኔ ዘንድ ነገር ፈልገህ ሳይሆን አይቀርም። ምን ልታዘዝ? ሐጃህ ምንድን ነው?” አለችው።
እሱም፦
“ከአንቺ ዘንድ ያለኝን ገንዘብ ፈልጌ ነው፣” አላት።
ኸዲጃም፦
“ሙሐመድ፣ ይህን ውበትና ገንዘብ ይዘህ ምን ልትሠራበት ነው?” አለችው።
“አጎቴ፣ ሴት አጭልሃለሁ፤ የምትል ለቤቴ ብለውኛልና፣” አላት።
ኸዲጃም፦
“ሚስት ልታገባ አስበህ ከሆነ፣ እኔ እጅግ ቆንጆ የሆነች፣ ገንዘብ ያላት፣ ለዘርህ ቅርብ የሆነች፣ ሹማምንቶች ለጋብቻ ጠይቀዋት እንቢ ያለች፣ በሰዎች ዘንድ የተከበረች፣ አእምሮዋ የተረጋጋና የሞላ አንተን እንጂ ከአንተ ምንም የማትፈልግ ሚስት አዘጋጅቼልሃለሁ፣” አለችና እንዲህ ስትል ቀጠለች፦
“ካንተ ማልደብቀው ሁለት ነውር አላት። አንደኛ፣ አግብታ ታውቃለች። ሁለተኛ፣ በዕድሜ ከአንተ ትበልጣለች፣” አለች።
ሙሐመድ ﷺም፦
“አንቺ ጥሩዋ ሴት ሆይ፣ ማናት? እሷ የት ነው ያለችው?” አላት።
እሷም፦
“የእኔ ምርኳኛ ናት። እዚህ ቅርብ፣ አጠገብህ ታገኛታለህ። ስሟም ኸዲጃ ይባላል፣” አለችው።
ሙሐመድ ﷺ ሁሉም ነገር በተገለጠለት ጊዜ፣ ምንም መልስ ሳይሰጥ ዝም አለ።
ኸዲጃም፦
“የእሽታ መልስህን ስጠኝና ልቤን አሳርፈው። አሁንም ከወጣቱ መልስ ብታጣ፣ አላህ ካለ፣ እኔ ከታጋሾች ሆኜ ታገኘኛለህ። አንተንም በምንም አልወነጅልህም፣” አለችው።
ሙሐመድ ﷺም፦
“ኸዲጃ፣ አንቺ የተከበርሽና ባለ ብዙ ሀብት ባለቤት ነሽ። እኔ ደግሞ የአንቺ ተቀጣሪ ነኝ፤ ከምትሰጪኝ ገንዘብ ሌላ ምንም የለኝም። ገንዘብ የሌለው ፈልጎም ቢሆን፣ ቢጤውን ያገባል፣” አላት።
ኸዲጃም እንዲህ አለችው፦
“ገንዘብን ብናደባልቀው ይበዛል እንጂ አያንስም።”
ወጣቱም በድጋሜ ምንም ሳይመልስላት ዝም አለ።
ኸዲጃም፦
“በግልጽም ሆነ በድብቅ የሚሠሩትን የሚያውቅና የሚያይ በሆነው ጌታዬ ይሁንብኝ፤ በእኔ በኩል ምንም የምሸፍነው ነገር የለም። ሁሉም ነገር እውነት ነው።
ወደ ቤተሰቦችህ ሂድና አጎትህን ለጋብቻ እንዲጠይቁኝ ንገራቸው። ምናልባት አባቴ ብዙ የመሐር ገንዘብ ከጠየቃቸው፣ የጠየቀውን እኔ እሰጥሃለሁ።
እኔ ያንተ ነኝ። እኔው መረጥኩህ። ከአንተ ሌላ ማንንም አልፈልግም። ልቀርብህ ሳስብ አታርቀኝ፣” አለችው።
ልመና በተቀላቀለበት አነጋገር፣ ሙሐመድ ﷺ ተነስቶ ከቤቱ ወጣ።
ኸዲጃ ሙሐመድ ﷺ ከመምጣቱ በፊት፣ ለወዳጇ ለነፊሳ አጫውታት ነበር። ነፊሳም እሱን አሳምና፣ ከምትወደው ሰው ጋር እንደምታጋባት ቃል ገብታላት ነበር።
ወጣቱ ሙሐመድ ﷺ እና ነፊሳ ሲገናኙ፣ ነፊሳ ስለ ታላቂቱ ሴት ኸዲጃ መልካም ባህሪና እንዲሁም እሱን ማግባት እንደምትፈልግ፣ ከገንዘቡም እንደምታስበልጠው አንድ በአንድ ነገረችው።
ጥያቄዋን እንዲቀበልም አሳመነችው።
➡️ ክፍል #5 ይቀጥላል… 🌹
🔗 SHARE • SHARE
┄┄┉┉✽ » 🌹 ✿ 🌹 « ✽┉┉┄┄
JOIN & SHARE 🔗
👉 @baraka_bier
👉 @baraka_bier
┄┄┉┉✽ » 🌹 ✿ 🌹 « ✽┉┉┄┄
2 702
🦋ታገስ
ቀጣዩ የጀላሉዲን አል ሩሚ ምክር የገባኝ አሁን ላይ ነው።
لا تتحدث في الثلاث
عن ذهابك ومذهبك وذهبك
ስለ 3 ነግራቶች ለማንም አትናገር
ስለመጓዝህ(ለመሄድ ስለማሰብህ)
ስለመዝሃብክ (አቂዳህ)
ስለ ወርቅህ(ስለ ሃብትክ)
አንተ ከረሱል የምክር መውጅ የቀዘፍከው ጀላሉዲን አል ሩሚ አሏህ ልሳንህን ይባርክ!
- - ሩቅ ሃገር ለመጓዝ ያስብክ ግዜ ቤታቸው የተቀመጡ የቤት ለማዳዎችን አታማክር - ይልሃል የፋርሱ ነጋሲ። እኚህ ሰዎች በአልጋቸው ሙቀት ተገርመዋል! የእናት እና አባቶቻቸውን ሃቅ የሚወጡት እንደ አራስ ህጻን ከእቅፋቸው ሥር ባለመውጣት ብቻ ይመስላቸዋል።
ለሰዎች ስለመጓዝህ የተናገርክ እንደሆነ ሞኝ መስለህ ትታያቸዋለህ ! ችኩል ነህ ይሉሃል እንግዳም ትሆንባቸዋለክ! ይኋሊት ካየህ ግን ከምርጦቹ ትውልዶች አንዱም ፍራሹ ላይ የተደላደለ የለም ! ከመቶ ሺ በላይ ሶሃባዎች ከመኖሪያቸው ተሰደዋል ! እናቶቻቸውን አስከፍተው ነው ወይንስ አባቶቻቸውን ተቃርነው? ሞኝ ይሁኑ ወይስ ችኩል? ወሏሁል ሙስተዐን !
• ስለ አቂዳህም ለሰዎች አትናገር።አቂዳ የልብ ሥራ ናት ምላስ ጨርሳ ልትገልጸው አትችልም።
አደራህን ሰዎችን ሰው በመሆናቸው እንጂ በአቂዳቸው እንዳትለካ።በያዝከው እስልምና እንጂ ዘመን ባመጣው የዐቂዳ ታርጋ ቅንጣት እንዳትኮራ ፡ እውነትን ሁሌም ፈልጋት ! አገኘጓት ብለህ የተቀመጥክ እንደሆነ ታላቅ ስህተት ላይ ወድቀሃል.
አስተውል እውነትን ከልቡ እየፈለጋት ሳያገኛት የሞተ ከእውነተኞች ጭፍራ ይቀሰቀሳል። እውነትን አውቆ ያልተገበራት ሰውስ? ያልከኝ እንደሆነ እውነትን በሃቂቃ ያወቃት ጀርባውን ሊሰጣት አይቻለውም ! አሏህ ከእዝነቱ ያራቀው ሰው ቢሆን እንጂ እልሃለው። . .....
2 702
▶️የተወዳጁ እና የፍቅር ተምሳሌት የሆኑትን የነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) እና የኸዲጃ #መሳጭ እና #እውነተኛ #የፍቅር ታሪክ◌◌◌
🖌#ክፍል 3⃣❤️
#ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) አጎቱ ጋር መኖር ሲጀምር ፍየል በመጠበቅ ተግባር ተሰማራ፡፡ ግን ብዙም ሳይቆይ አጎትየው የገቢያቸውን መጠን ለማሳደግ ጥረት ማድረግ ጀመሩ፡፡
#አንድ #ቀን ከድጃ ወንዶችን ወደ ምድረ ሻም በመላክ እንደምታሰማራ ስላወቁ ነጋዴው ወደተባለው ሀገር ለመጓዝ በዝግጅት ላይ ሳሉ ሙሀመድን አስጠርተው ስለሁኔታው ሊነግሯቸው ወሰኑ፡፡
"የወንድሜ ልጅ ሆይ እንደምታውቀው አንዳች የሌለኝ ደሀ ነኝ ፤ ግዜው ደግሞ በድርቅ ተመቷል፡፡ ከድጃ ሰው ቀጥራ እንደምታስነግድ ሰምቻለው በርግጥ የምትከፍለው ገንዘብ አነስተኛ በመሆኑ ደስ አያሰኝም፡፡ #እናም ስለዚህ ጉዳይ እሷኑ ባነጋግርልህ " ሲሉ አቡጧሊብ ጥያቄ ለመሀመድ አቀረቡ፡፡ ሙሀመድም እንዲህ አላቸው "አጎቴ ሆይ እንዳሻህ ማድረግ ትችላለህ ሀሳብህ የኔም ሀሳብ ነው መጭው አለም ከዱንያ አለም በላጭ ነው" አሏቸው፡፡
#አቡጧሊብ #ጊዜ ማጥፋት አልፈለጉም ወንድሞቻቸውን አስከትለው ወደ ኸድጃ ቤት አመሩ፡፡ እሷም ከሀር በተሰራ ባማረ ልብስ ተውባ በፈገግታ ተቀበለቻቸው፡፡
#አቡጧሊብም "የተከበርሽው ከድጃ ሆይ እኛ የመጣነው ለጉዳይ ነው ሰዎችን ገንዘብ እየከፈልሽ እንደምታስነግጂ ሰምቻለው፡፡ ለሌሎች በምትከፊይው ላይ ጨምረሽ ተመሳሳይ ስራ እንዲሰራልሽ መሀመድን አትቀጥሪምን? " አሉ
ከድጃም "እንኳንስ ለሚወደድ ለቅርብ ዘመድ ለማይታወቀውም ቢሆን ጥያቄዎ በኔ ዘንድ ተቀባይነት አለው" በማለት አስደሳች መልስ ሰጠች፡፡
#አቡጧሊብ አስደሳቹን ዜና ይዘው ወደ መሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) ተመለሱ፡፡ ብስራቱን ከነገሩት በኋላ "ይህ ፈጣሪ ላንተ የላከው ሲሳይ ነው " አሉ፡፡
#ሩህሩሁ #አጎት መጪው ጊዜ ያረገዘውን ቢረዱ ይህ ለከድጃ ከሰማይ የወረደ ፀጋ ነው ባሉ ነበር፡፡ ሆኖም ከዚህ መልካም ዜና በስተጀርባ የሚመጣውን የላቀ ዕጣ የሚያውቅ አንድም ሰው አልነበረም፡፡
#እድለኛዋ ከድጃ (ረ.ዐ) አቡጧሊብ ያቀረቡትን ጥያቄ በደስታ ተቀበለች ፤ ይህም ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) እና ከድጃ (ረ.ዐ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቁበት አጋጣሚ ፈጠረ፡፡ ጉዳዩ በመካ ነዋሪዎች ዘንድ ተዳረሰ፡፡ በየአጋጣሚው የታላቁን ሰው መልካም ትሩፋት እውነተኛነት ዘረዘሩላቸው፡፡ ከድጃም ይበልጥ ደስ አላት፡፡ #መይሰራ ከተባለው አገልጋይ ጋር ወደ ሻም እንዲሄዱ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን አስታወቀች፡፡ ሙሀመድም የተሰጣቸውን አማና ተቀብለው ለንግድ ከመይሰራ ጋር ወደ ሻም አመሩ፡፡
ከሻም ጉዞ መልስ ከድጃ (ረ.ዐ) #ለሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) "ለአንተ እኔ ዘንድ ጥሩ ደስታና ስጦታ ተቀምጦልሀል ከሁሉም ሰራተኞች የበለጠ እጥፍ ተጨማሪ ገንዘብ ይከፈልሀል" አለችው፡፡ #ሙሀመድም (ሰ.ዐ.ወ) ከጉዞ መልስ አጎቱ ጋር ተመለሰ፡፡ #አቡጣሊብም አባት ለልጅ አቀባበል ከሚያደርገው በላይ በደስታ ተቀበሉት፡፡ ከዚያም እንዲህ አሉት
"#ልጄ #ሆይ ከድጃ ከፈለች?"
ሙሀመድም "ከውሉ በተጨማሪ ትርፍ ገንዘብ ጨምራ እንደምትሰጠኝ ቃል ገባችልኝ " አሉ።
#አቡጣሊብም "ልጄ ሆይ የወላጆችህ አደራ አለብኝ እንደምታዬኝ አርጅቻለሁ የሞትም ምልክቱ እየታየብኝ ነው ስለዚህ አንተን ድሬ ወግ ማዕረግህን ማየት እፈልጋለሁኝ።
.
#ክፍል 👉 4⃣
ይ◌◌◌◌ቀጥላል......
🔗SHARE 𝕛𝕠𝕚𝕟 🔗SHARE
┄┄┉┉✽»🌹✿🌹»✽┉┉┄┄
𝙟𝙤𝙞𝙣 & 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚🔗
👉👉 @baraka_bier
👉👉👉 @baraka_bier
𝙟𝙤𝙞𝙣 & 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚🔗
┄┄┉┉✽»🌹✿🌹»✽┉┉┄┄
2 702
አሰላሙአለይኩም ያጀመዓ ሼር እያደረጋችሁ ግን አደለም ታሪኩ ይቁም እንዴ እ ለእናንተ ወዳችሁ ምትከታተሉትን ለጓደኞቻችሁም ላኩላቸው ሱና ነው ።
2 702
-ናፍቆት'
ወዳለፈው ዘመን የሚጎትት የኋሊት ሀዲድ ነው። በትዝታ ተሳፍረን ትናንትናችንን ልንጎበኝ የምንሄድበት የምልሰት ኑሮ።
የናፍቆት ወላፈን በልጅነታችን ካለፍንባቸው መንገዶች ፣ ከወላጆቻችን አልባሳት ፣ ቤታችን ውስጥ ከቆመችው የዛፍ ጥላ ፣ ከእህት ወንድሞቻችን ድምፅ እየተነሳ ወደ ህሊናችን ይተናል።
ናፍቆት የሰው ልጆች የማያመልጡት ያለፈ ታሪካቸው ዶሴ ላይ የተፃፈ ሰቀቀን ፣ የትካዜ ሀገራቸው መሠደጃ ነው።
Copy
@baraka_bier
2 702
" አቧራ የጠገበን ምንጣፍ በዱላ የምትመታው
አቧራውን ለማራገፍ እንጂ ምንጣፉን ለመጉዳት
አይደለም ። የሰውን ድክመት የምትነግረውም ስህተቱን
እንዲያርም እንጂ ሰውዬም በስራው ተስፋ እንዲቆርጥ
አይደለም ። "
😊❣😊
JOIN👉 @baraka_bier
2 702
የተወዳጁ እና የፍቅር ተምሳሌት የሆኑትን የነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) እና የኸዲጃ #መሳጭ እና #እውነተኛ #የፍቅር ታሪክ◌◌◌
🖌#ክፍል 2⃣❤️
#የተከበረችው ኸድጃ በዝሆኖች አቆጣጠር ከ15 አመት ቀደም ብላ ከአባቷ ኩወይሊድ ኢብኑ አሰድ አብድልዑዛ ከእናቷ ፋጡማ ቢንቱ ዛኢዳ ተወለደች፡፡ #ከድጃ (ረ.ዐ) ስሩ ከጠለቀ ጫፉ ከዘለቀ ከተከበረ ነገድና ቤተሰብ የተገኘች ናት፡፡ #ከህፃንነቷ ጀምሮ የነገሮችን እውነታ የመከታተልና የማወቅ ጉጉቷ ከዕድሜዋ የላቀ ነበር፡፡ ስለ ንግድ አባቷ ከወንድሞቿ ጋር ሲወያዩ በአትኩሮት ትከታተል ነበር፡፡
ለአቅመ ሄዋን ስትደርስ ብዙ የጋብቻ ጥያቄ ይቀርብላት ጀመር፡፡ #እሷ #ግን በስሜት ተገፋፍታ ለምርጫ አልቸኮለችም፡፡ #ጉዳዩን በጥልቀትና በስፋት በመመርመር ለምትወስደው አቋም ሚዛናዊ መለኪያዎችን መፈለግ ተቀዳሚ ተግባሯ ነበር፡፡ በመጨረሻ ግን አቡሀላህ ኢብኑዚራራህን አገባች፡፡ #ከሱም ህንድና ሀላህ የተባሉ ልጆችን አገኘች፡፡ ከድጃ ከአቡሀላህ ጋር ጥቂት አመታት እንደቆየች በሞት ተለያት፡፡ ከዚያ አቲቅ ኢብኑል ኩዘይምን አገባች፡፡ ከሱም አንድ ልጅ ከወለደች በኋላ አቲቅ በሞት ተለያት፡፡ #ሀብትና #ንብረቱን ወርሳ ተቀመጠች፡፡
ከባሏ ሞት በኋላ የተለያዩ ሰዎች ለጋብቻ ቢጠይቋትም ፍቃደኛ አልሆነችም፡፡ የወንድ አይነት እየተግተለተለ በተለያየ አቀራረብ ደጅ ቢጠናትም ስሜት አልሰጣትም፡፡
#አላህ #በረቀቀ ጥበብና ማንም በማይደረስበት ሚስጥሩ የማንነት መለኪያ የትልቅነት መገለጫ ሆነው ከቀረቡት ነገሮች ሁሉ እጅግ ብልጫ ያለውን መልካም ነገርን ሁሉ አጠቃሎ የያዘ ሰው አዘጋጅቶላት እንደነበር አስባውም አታውቅም፡፡
#ከድጃ #ጣኦት አላመለከችም፡፡በጃህሊያ ከጣኦት አምልኮ እንድትቆጠብ ያደረጋት ለአጎቷ ወረቃ ያላት ቀረቤታ ነው፡፡ ወረቃ ኢብኑ ኑፈይል የነሳራዎች መፅሀፍ ከቅድመ አያቶቹ ስለተሰጠው ይህንን መከተል መርጦ ስለነበር ብዙ ዕውቀቶችን ወደተለያዩ አገሮች ሄዶ ተምሮ ብዙ እውቀት ስላገኘ ከድጃ የባዕድ አምልኮ እንዳትከተልና እንድትጠላ አድርጓታል፡፡ #የተረጋጋች ፣በሳል ፣ተፈጥሮዋ የሰከነ በመሆኑ ሰዎች #"ጧሂራ" (ንፅህት) በሚል በልዩ የማዕረግ ስያሜ ይጠሯታል፡፡
#ይህን #ስያሜ ከእስልምና በፊት ያገኘችው ነው፡፡
#አንድ ወቅት ከቁረይሽ ሴቶች ጋር ሆና በጃህሊያ ጊዜ አመታዊ በዓል በሚያከብሩበት የክብር ቦታ ቁጭ ብላ ሳለ አንድ ሰው ሴቶቹ አጠገብ ሲደርስ "እናንተ የመካ ሴቶች በናንተ ከተማ ነቢይ ሊመጣ ነው #ስሙ #አህመድ ይባላል፡፡ ከናንተ የቻለ ያግባው " ሲል ይጮሀል፡፡ #ሴቶቹና ሌሎች ሰዎች ጭምር በድንጋይ እየደበደቡት አባረሩት፡፡ #የተከበረችው #ከድጃ #ስትቀር !
#የከድጃ (ረ.ዐ)ሀብት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጣ፡፡ በውክልና እሷ ዘንድ በኮሚሽን መቀጠር ከቻሉ ሰዎች መካከል ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) አንዱ ነበር፡፡ ወጣቱ ትሁት ሰው አክባሪ የሰውን ገንዘብ ያለ ሀቁ የማይፈልግ ታታሪ ቸር ስራውን ወዳድ በመሆኑ ከድጃ(ረ.ዐ) ጋር #ከተቀጠረ ጀምሮ ከመካ ከተማ ርቆ በመሄድ እየነገደ ገንዘቧን በእጥፍ አሳደገው፡፡ በዚህም ከድጃ (ረ.ዐ) በወጣቱ ኮርታበታለች፡፡ #ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) ከድጃ (ረ.ዐ) ጋር የተቀጠረው እንዲሁ በአጋጣሚ አልነበረም፡፡ የሚያሳድጉት አጎቱ ጥሪት አነስተኛ በመሆኑ እንጂ፡፡
የሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) አባት አብደላህ ገና ሳይወለዱ ነበር የሞቱት፡፡ እናታቸውን ያጡት ደግሞ በ6 አመታቸው ነበር፡፡ ቢሆንም በአያቱ ዘንድ አደገ፡፡ አያቱ ሲሞቱ አጎቱ ተረከቧቸው፡፡
.
🔻#ክፍል 3⃣
.........ይ...........
.......ቀ
.....................ጥ
ላ...........
........ል
🔗SHARE 𝕛𝕠𝕚𝕟 🔗SHARE
┄┄┉┉✽»🌹✿🌹»✽┉┉┄┄
𝙟𝙤𝙞𝙣 & 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚🔗
👉👉 @baraka_bier
👉👉👉 @baraka_bier
𝙟𝙤𝙞𝙣 & 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚🔗
┄┄┉┉✽»🌹✿🌹»✽┉┉┄┄
2 702
| "አንድ ጊዜ ምን ሆነ መሰላችሁ። ሀገራችን ላይ ዝናብ ጠፋና የድርቅ ወሬ እዚህም እዝያም ሆነ።
ሙስሊሙም በመስጅዱ፣ ክርስቲያኑም በመቅደሱ ወደ ፈጣሪ ሊጮህ በነቂስ ወጣ።
አንድ አባወራ ሕፃን ልጁን "ና ወደ መስጅድ እንውጣ። ሙስሊም ክርስቲያኑ ሁሉ ተሰብስበን ዝናብ እንዲሰጠን ወደ አላህ ልንፀልይ ነው።" ይልና የሕፃኑን እጅ ይዞ ከቤት ይወጣል።
ገና ደፉን እንደተራመዱ ሕፃኑ ልጅ "ቆይ፣ ቆይ አባዬ መጣሁ" ይልና እየሮጠ ወደ ቤት ይመለሳል።
ወደ መስጅድ ለመሄድ የተቻኮለው አባት "ምን ፈልጎ ነው?" እያለ በር በሩን ያያል።
ሕፃኑ አፍታም ሳይቆይ እየሮጠ ይመለስና "ዣንጥላ ረስተን ልንሄድ ነበር።" አለው በእጁ የያዘውን ዣንጥላ እያመለከተው።
የዚያ ሕፃን ልጅ ቀልብ ከሁሉም የተሻለ መሆኑን ተመልከቱ እንግዲህ።
አላህን ተሰባስበን ዝናብ ከጠየቅነውማ ዝናቡ በእርግጥም ይዘንባል ብሎ የሚጠለሉበትን ዣንጥላ ይዞ ወጣ። የዚህን ሕፃን ቀልብ ከያዛችሁ የጠየቃችሁትን ታገኛላችሁ።
#ዓለማየሁ_ደመቀ
@baraka_bier
2 702
ተለቀቀ ◎ተለቀቀ◎ ተለቀቀ◎
❤️የተወዳጁን እና የፍቅር ተምሳሌት የሆኑትን የነብዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) እና የኸዲጃ (ረ.ዐ) #መሳጭ እና እውነተኛ #የፍቅር ታሪክ እነሆ ወደ እናንተ መድረሱን ጀመረ።
#ክፍል 1⃣
✨በአሁኑ ዘመን እዉነተኛ ፍቅር ከፊልም፣ ከቃናtv..እና ከአማረኛ ፊልም እያዩ የሚመኙ አሉ ፡፡ ግን እዉነተኛ ፍቅር ገና ማህበሪዊ ሚዲያ ሳይመጣና እንደ አሁኑ ሞደርን ስልጣኔ ሳይመጣ በፊት የተጀመረ ነዉ ..በፊት እዉነተኛ ፍቅር ምን ይመስል ነበር፡፡ እንደ ዘመኑ ፊልም ተጣልቶ መታረቅ ይሆን ?? እስከ ተከታታይ ታሪክ ጀምረናል እስከምንጨርስ አብረዉ ይከታተሉን።
#በቅድመ ኢስላም በጃህሊያ ዘመን ወደ ኢስላም ጥሪ ከመጀመሩ በፊት አስራአምስት አመት ገደማ አንድ ውብና ተክለ ሰውነቱ ያማረ ወጣት ካዕባ አጠገብ ከሚገኘው በኸዲጃ ቢንት ኹወይሊድ (ረዐ) ቤት አጠገብ አለፈ፡፡
#ወጣቱ ሲያዩት ፊቱ እንደ በድር ጨረቃ የፈካ ፤ መልከመልካም ፣ የዐይኖቹ ጥቁረት የበረታ ፣ የሽፋሽፍቶቹ ፀጉር ረዥም ፣ ፀጉሩ በጣም የጠቆረ ፣ አንገቱ መለሎ፣ አይኖቹ በተፈጥሮ የተኳሉ ፣ ቅንድቡ ቀጭን እና ረዥም ፣ ከሩቅ ሲያዩት እጅግ ሲበዛ ቆንጆ ፣ሲቀርቡት ተወዳጅ፣ #ጥርሱ ነጭ እና #አፍንጫው ቀጥ ያለ ነበር፡፡
#በወቅቱ የከድጃ ቤትና የዳረል አሰድ ቢን አብድልዑዛ ፣ ቤት ከካዕባው ጥቂት እርምጃ ነበር የሚርቀው፡፡ አንድ የአይሁድ መነኩሴ በከድጃ ቤት ውስጥ ቁጭ ብሎ ሳለ መልከመልካሙን ወጣት አየው ፣ ከድጃንም ወጣቱ ተጠርቶ እንዲመጣ አዘዛት ፣ ወጣቱም በከድጃ አገልጋይ ተጠርቶ መጣ፡፡
#አይሁዳዊው #መነኩሴ ወጣቱን በትህትና ልብሱን ከትከሻው አካባቢ ገልጦ እንዲያሳየው ጠየቀው ፣ ወጣቱም እንደተጠየቀው አደረገ ፣ አይሁዳዊው ትከሻው አካባቢ ባየው አስደናቂ ነገር ተደሰተ አቅፎም ሳመው፡፡
#ሁኔታውን ስትከታተል የነበረችው ከድጃ ለአይሁዱ "ይህንን ድርጊትህን ቁረይሾች ቢያዩህ አንተን ከመቅጣት ትዕግስት የላቸውም " አለች፡፡
#በርግጥ #የአይሁዱ #ድርጊት ለምን እንደሆነ ከድጃን (ረዐ) የገባት ነገር የለም ፣ ወጣቱን ስታየው ፊቱ የፈካና የሚያምር አንደበተ ርቱዕ ነበር፡፡
#በሌላ ጊዜ አይሁዱ ለከድጃ እንዲህ አላት፡፡
👉"በተውራትና በኢንጂል ኪታቦች ላይ ሰፍሮ እንዳየሁት የአንድ ብርቱ ሰው መምጫ እየተቃረበ ነው፡፡ ይህ ሰው የተወለደው እዚሁ በመካ ነው ፣ እናትና #አባቱ #በልጅነቱ #ይሞታሉ ፣ አጎቱ ያሳድጉታል ወደ መዲናም ይሰደዳል ፣ የሻምን ስልጣን በእጁ ያደርጋል ፣ በመካ ያሉትን ጣኦታት በሙሉ ሰባብሮ በማስወገድ ካዕባን ንፁህ ያደርገዋል፡፡"
#ከድጃ አይሁዱ የተረከላትን በጥሞና አዳመጠች ፣ በንግግሩም ተማረከች ልቧ ጓጓ ወጣቱንም ለማወቅ ፈለገች፡፡
#በሌላ ጊዜ አጎቷ ወረቃን ስለዚው ጉዳይ ጠየቀችው ፤ ወረቃም ወደ ሻምና ሶሪያ በመሄድ የኢንጅልን መፅሀፍ ስላጠናና ስለመረመረ ይመጣል ተብሎ የተተነበየው ታላቅ ሰው ከቁረይሾች እንደሚያገባ በገንዘብ እንደምትረዳውና ከጎኑ እንደምትሆን አረጋገጠላት፡፡
.
አ
..... ላ
..............ለ
....................ቀ
***ም!!!
➡️ክፍል #2 ይቀጥላል◌◌◌
🔗SHARE 🔗SHARE
┄┄┉┉✽»🌹✿🌹»✽┉┉┄┄
𝙟𝙤𝙞𝙣 & 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚🔗
👉👉 @baraka_bier
👉👉👉 @baraka_bier
𝙟𝙤𝙞𝙣 & 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚🔗
┄┄┉┉✽»🌹✿🌹»✽┉┉┄┄
2 702
❤️የተወዳጁን እና የፍቅር ተምሳሌት የሆኑትን የነብዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) እና የኸዲጃ (ረ.ዐ)
መሳጭ እና እውነተኛ
#የፍቅር ታሪክ◌◌◌ ዛሬ ሀሙስ እስከ ማታ 3 ሰአት ድረስ ይለቀቃል።
እንደተለቀቀ እንዲደርሳችሁ ቻናላችንን ይቀላቀሉ
┄┄┉┉✽»🌹✿🌹»✽┉┉┄┄𝙟𝙤𝙞𝙣 & 𝙨𝙝𝙖𝙧
@baraka_bier
2 702
❤️የተወዳጁን እና የፍቅር ተምሳሌት የሆኑትን የነብዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) እና የኸዲጃ (ረ.ዐ)
መሳጭ እና እውነተኛ
#የፍቅር ታሪክ◌◌◌ ዛሬ ሀሙስ እስከ ማታ 3 ሰአት ድረስ ይለቀቃል።
┄┄┉┉✽»🌹✿🌹»✽┉┉┄┄𝙟𝙤𝙞𝙣 & 𝙨𝙝𝙖𝙧
@islamul_habeshi
@islamul_habeshi
2 702
❤️የተወዳጁን እና የፍቅር ተምሳሌት የሆኑትን የነብዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) እና የኸዲጃ (ረ.ዐ)
መሳጭ እና እውነተኛ
#የፍቅር ታሪክ◌◌◌ ዛሬ ሀሙስ እስከ ማታ 3 ሰአት ድረስ ይለቀቃል።
┄┄┉┉✽»🌹✿🌹»✽┉┉┄┄𝙟𝙤𝙞𝙣 & 𝙨𝙝𝙖𝙧
@islamul_habeshi
@islamul_habeshi
