cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ለእኔ ነው።🙏

Advertising posts
258Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1030 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

በሰው ይክሳችኋል! ፨፨፨///////////፨፨፨ ማናችንም የግል ንግግር አለን። ንግግራችንም ከፈጣሪያችን ጋር ነው፤ እውነቱን ቢያውቀውም እውነቱን እንነግረዋለን፤ ህመማችንን ቢረዳም ይበልጥ ይረዳን ዘንድ እናካፍለዋለን፤ የሸክማችን ክብደት የተደበቀበት ባይሆንም ግልፅ አድርገን እናወያየዋለን። ምክንያቱም ከእርሱ ውጪ እውነተኛ ሰላም የሚሰጥ፣ ልባዊ መረጋጋትን የሚያድል የለምና ነው። ማንም ባላለፈበት ከባድ መንገድ አልፋችሁ ይሆናል፣ ማንም ያልደረሰበት በደል ደርሶባችሁ ይሆናል፣ ሊታሰብ የማይችል አጣብቂኝ ውስጥ ወድቃችሁም ይሆናል። ይህን ሁሉ ግን ሰዎች ባያዩ፣ ይህን ሁሉ ግን ሰዎች ባይረዱት አምላካችሁ እግዚአብሔር ግን በሚገባ ይመለከታል፣ በሩህሩህ አይኖቹ ያጤናቸዋል፣ በቸሩ ልቡ ያስባቸዋል። አምላካችሁ አብሯችሁ እንደሆነ ካመናችሁ ያጣችሁትን የምታገኙበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፤ በፈጣሪያችሁ ትከሻ ከተደገፋችሁ የሸሻችሁን የውስጥ ሰላም የምትታደሉበት ወቅት ሩቅ አይሆንም። አዎ! ጀግናዬ..! እግዚአብሔር ህመማችሁን ሲመለከት፣ ድካማችሁ ሲገባው፣ ትጋታችሁ ጥግ መድረሱን ሲያውቅ፣ ቁስላችሁን ሊሽር ሲፈልግ፣ የዓመታት ጠባሳችሁን መሻር ሲሻ ሰው ይሳጣችኋል፤ በሰው ጉዳታችሁን ያክመዋል፤ በሰው ያሳርፋችኋል፤ በሰው ሰላምን ያድላችኋል፤ በመረጠላችሁ ሰው በኩል ዳግም አንፆ ቀና ያደርጋችኋል። ትክክለኛውን የመነሻችሁን ጊዜ ጠብቁ፤ እውነተኛው ሰው ወደህይወታችሁ እስኪገባ ታገሱ፤ የአምላካችሁን ሰዓት በትዕግሥት ተጠባበቁ። በጥድፊያችሁ ምክንያት ተደጋጋሚ ዋጋን ከመክፈል እራሳችሁን ጠብቁ። ከጅማሬያችሁ በላይ ፍፃሜያችሁን፣ ከመነሻችሁም በላይ መውደቂያችሁን ያመቻችላችሁ ዘንድ ፈጣሪን ጠይቁት። አዎ! ስለሚወዳችሁ በሰው ይክሳችኋል፤ ስለሚሳሳላችሁ ሰው ይሰጣችኋል። የሰውን ዋጋ ፍፁም አታሳንሱ፤ የሰውን አብሮነት በጭራሽ እንዳታረክሱ። እግዚአብሔር ስራ ሊሰራባችሁ ሲፈልግ በሰው ያስመርጣችኋል፤ እንባችሁን እስከወዲያኛው ማበስን ሲሻ ሁነኛ የልብ ሰው፣ ጠባቂና የሚሳሳላችሁን ስው ያድላችኋል። ለተሰጧችሁ የሰው በረከቶች ያለማቋረጥ ምስጋናን አቅርቡ። በቁስላችሁ ላይ እንጨት ሊሰዱ የሚችሉ ሰዎች ወደህይወታችሁ መግባት ቢችሉም በፈጣሪ ፍቃድ ግን ቁስላችሁን የሚሽሩ፣ በድካማችሁ ሁሉ የሚያግዟችሁ፣ ሃሳባችሁን ሁሉ የሚካፈሏችሁ ሰውችን ፈጣሪ ስለሰጣችሁ ከልባችሁ አመስግኑት። የአምላክ በረከት፣ የፈጣሪ ስጦታዎች የሆኑላችሁን ሰዎችም ከልብ አክብሩ፣ ውደዱ፣ ተቀበሏቸውም። ውብ ምሽት ይሁንልን! 🌘🌒✨💫 ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋 በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን! 🔺🔻 SUBSCRIBE NOW https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1 ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊 💪
Show all...
ነፍሴን ቀድሳት! ፨፨፨///////፨፨፨ ደጉ አባት ቅዱስ እግዚአብሔር በአንድም በሌላም ይናገረናል። ንግግሩም ከባህሪው ሲቀዳ "በፍቅር ትመላለሱ ዘንድ፣ እኔንም ታስደስቱ ዘንድ የፍቅር ልብ ይኑራችሁ፤ እርስ በእርሳችሁ ተዋደዱ፤ ድጋፍን ፈልጉ፣ ለወገናችሁም ድጋፍ ሁኑ።" የዘወትር አሸናፊዎች በነፍሳቸው ላይ የሰለጠኑ፣ እራሳቸውን የገዙ፣ ማንነታቸውን የዋጁ፣ እግዚአብሔር አምላካቸውን የወደዱና ከልባቸው የተቀበሉ ናቸው። ፍቅርን ከኢየሱስ ክርስቶስ በበለጠ ያስተማረ የለም። አምላክ ሆኖ በፍቅሩ ብዛት የሞተው ለእኛ ለልጆቹ ነው። የእኛ በፍቅር መመላለስ ግን የሚፈልገው ሞት ሳይሆን ንፁ ልብ፣ አዎንታዊ አስተሳሰብና ቅንነት ነው። እግዚአብሔር ፍቅር ነው፤ የፍቅሩ መገለጫም እኛው ድንቅ ልጆቹ፣ የእጆቹ ስራ፣ ግሩም ትሩፋቶቹ ነን። ወዶ፣ ፈቅዶ፣ መርጦ እኛን ፈጠረ፣ ወደዚህ ምድርም አመጣን። ከፈጣሪያችን እግዚአብሔር በቀር ማን ስለእኛ ያውቃል፤ ማንስ እርሱ እያወቀን ዝም ብሎ ፃድቅ ነኝ በይ ሊከሰን ይነሳል። አዎ! ጀግናዬ..! እግዚአብሔር መንገድህ ነው፤ አምላክህ መዳረሻህ ነው፤ ህይወትህ የእርሱ መንግስት ነው፤ ፅድቅህ ፍቃዱ ነው፤ ምርጫው ነው፤ ትዕዛዙ ነው። የምታውቀውን ለመኖር ጥበብ ያሻሃል፤ ትልቁ ጥበብ ደግሞ እግዚአብሔርን መፍራት ነው። ከጠቢቡ ሰለሞን በላይ ጥበብን የሚያውቅ፣ ምንነቱን የተረዳ፣ ምንጩንም የተገነዘበ ሌላ ማን ይኖራል? ማንም። ጥበብን የሚሻ የአምላክ ባለሟል ነው፤ የአምላኩ የእግዚአብሔር ተገዢም፣ ታዛዥም ነው። ልፋ ያለው ይለፋል፤ ድከም ያለው ይደክማል፤ አምላክህን እወቅ ያለው ግን በእውቀቱ ያርፋል፤ በጥበቡ ህይወቱን ይመላል። መርጋት በእግዚአብሔር እጆች ላይ ነው፤ ሰላም ማግኘት በእርሱ እቅፍ ውስጥ ነው፤ መባረክ በቃሉ መውዛት ነው፤ መመረጥ መንገዱን መከተል ነው። አዎ! ካንተ በለይ የምታመልከው አምላክ፣ የታመንክበት ጌታ፣ የምትማፀነው ፈጣሪ መመኪያህ ነው፤ ዙፋንህ ነው፤ ዘወድህ፣ ክብርህ፣ ጌጥህ ነው። ብቻህን አለምን ብታካልል ነፍስህ እረፍት አይኖራትም፤ ምድራዊውን እውቀት ጨርሰህ ብትይዘው ውስጥህ ሃሴት አያደርግም፤ የአለም ጭብጨባና ዝና ቢጎርፍልህ መንፈስህን አያድስም፤ ውስጥህን አያክምም። እረፍትህ፣ ሰላምህ፣ ሃሴትህና እድሳትህ ሁሉ ምንጫቸው እግዚአብሔር አምላክህ ነው፤ መገኛቸው ጌታህ፣ ገዢህና አባትህ ነው። ቅዱሳት ነፍሳት የሚመኩት፣ የሚኮሩት የሚታመኑት በአምላካቸው በእግዚአብሔር ነው ነውና ከዘወትር ፀሎትህ መጀመሪያ፣ ከዘወትር ፀሎትህ መደምደሚያ ይህችን የልባዊ ተማፅኖ ቃል እንዳትረሳ "ነፍሴን ቀድሳት!" ። ብሩክ ቅዱስ ቀን ይሁንልን! 🏞🌞🌅 ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋 በYouTube አማራጭ ይቀላቀሉን! 🔺🔻 SUBSCRIBE NOW https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1 ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊 💪
Show all...
ወደ መንግስቱ ወደ ክብሩም ለጠራችሁ ለእግዚአብሄር እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እየመከርንና እያጸናን እየመሰከርን ላችሁም አባት ለልጆቹ እንደሚሆን ለእያ ንዳንዳችሁ እንደሆንን ታውቃላችሁና።            (1ኛ ተሰ 2፥11-12) በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።                (ኤፌሶን 1፥3) ✍ እኛ ክርስቲያኖች ልካችን ይሄ ነው! በቃ ዘላለም ብቻ ነው የሚለካን ከዛ ውጪ የሆነው ከዛ በታች ነው ማለት እኛን የማይመጥነን ነው! ምን አይነት ክብር እንዳለን ልናስብ ይገባናል። ✍ እኛ ስለ ቦታ አያሳስበንም ስለ ስፍራ አያሳስበንም ቋሚ ስፍራ የምንወርሰው ዘላለማዊ ርስት በክርስቶስ ተሰጥቶናል። ምንም የለንም እያልን ከሌሎች እኛ ያለን ኢየሱስና ዘላለማዊ ህይወት ከሌላቸው ጋር ራሳችንን ማወዳደር ማቆም አለብን ምክንያቱም እነዚህ አለማዊ ሰዎች የሌ ላቸው ነገር ለእኛ በክርስቶስ ተሰጥቶናል። ✍ ለዛ እኮ ነው ጴጥሮስ ካንተ ወዴት እንሄዳለን ያለው ከኢየሱስ ውጪ ያለው ነገር በሙሉ ከንቱ እንደሆነ ገብቶታል ኢየሱስ ጋር ደግሞ የህይወት ቃል ህይ ወትን የሚሰጥ ቃል እንዳለና ይሄ የህይ ወት ቃል ከአለም የሚበልጥ መሆኑን አለማዊ ሰዎች የሌላቸው ነገር ኢየሱስን የሚከተሉ ሰዎች እንደሚያገኙ ስለገባው ነው። ከሰማያዊ ስፍራ ከመንፈሳዊ በረከ ት ውጪ የሆነ ነገር የእኛን የክብራችንን ደረጃ አይመጥንም!! ጌታ የጠራን ለሰማ ያዊ እንጂ ለምድራዊ ክብር አይደለም! ንጉሱ ባለበት እልፍ አእላፍ መላእክት ቅዱሳን ባሉበት ስፍራ ነው ክብራችን የሚገለጠው። ለክብር ተጠርተን የውር ደት ስፍራ እንዳንገኝ! የማያስከፍል መን ፈሳዊ በረከት በኢየሱስ አግኝተን ዘይት ለማግኘት ወረፋ በመያዝና በመሯሯጥ በከንቱ ዘመናችን እንዳያልቅ! ✍ በክርስቶስ ያገኘነውን አለምን የሚያ ስንቀውን ድፍድፍ በረከት ወደጎን ትተን በገዛ ምኞቶቻችንንና ፍላጎቶቻችን ተስበን ተታለን ነገር አለማችን በአለማዊ ነገር ዙሪያ ብቻ ሆኖ ተታለን እንዳንስት እንጠን ቀቅ ከሳትንበትም ወደ እውነቱ እንመለስ።
Show all...