cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

Advertising posts
258
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Photo unavailableShow in Telegram
ለእርዚቅ አስፈላጊ ስለሆነ ሒርዝ ላስታውሳችሁ ወደድኩ! በዛሬው #21ኛው የረመዷን ለይል ከፈጅር (ጉህ ከቀደደ በኃላ) ፀሃይ ከመውጣቷ በፊት ባለው ጊዜ መካከል 100 ጊዜ "ياباسط" ብሎ መፃፍ በአሏህ ፍቃድ አመቱን ሙሉ እርዚቅ ያሰፋል ብለዋል ሸይኸና ሸይኽ ዐብደሏህ አል-ሐረሪይ (ረሕማቱሏሂ ዐለይሂ)። እንደዚሁም በረመዷን #27ኛው ለይል ከፈጅር ሶላት በኃላ በሰገዱበት ቦታ ላይ ተቀምጦ 100 ጊዜ "ياباسط" ብሎ ጽፎ መያዝ በአሏህ ፍቃድ እስከ ቀጣዩ አመት ረመዷን ድረስ ለእርዝቅ ይጠቅማል። :¨·.·¨: ❀ `·.ሑሰይን የዐብደሪይ ወዳጅ T.me/husseyn_y_abdery_wedaj
Show all...
💚የወቅቱ የቺቺኒያ ፕሬዚዳንት አስላን ማስካዶፍ እንዲህ ብለው ይጠይቁናል «ራሺያን ስናሸንፍ ስንት ወታደር እንደነበረን ታውቃላችሁ? » እንዲህም ብሎ ቀጠለ « በወቅቱ አጠቃላይ የቺቺኒያ ሙጃሂድ ወታደር ከ4000 አይበልጥም ነበር። 837 ሙጃሂዲን የሚሆኑት ዋና ከተማዋ ግሮዝኒ ውስጥ ነበሩ። በወቅቱ 120,000 የራሺያ ወታደር ግሮዝኒን ከቦ ነበር። አስቡት 837 የቺቺን ሙጃሂዲን ወታደሮች 120,000 የራሺያ ወታደሮችን ሊደመስሱ ችለዋል። 120,000!» ፕሬዝዳንቱም እንዴት ያንን የሚክል ሰራዊት ሊያሸንፉ እንደቻሉ ጠየቁን… «አላህ በቅዱስ ቁርዓኑ እንዲህ ይላል <በአላህ ሱብሃነ ወተዓላ እርዳታ የሚያምን ትንሽ ስብስብ በሺዎች የሚቆጠሩ የማያምኑ ወታደሮችን ያሸንፋሉ> ይላል» «ያን የሚያከል የራሺያ ወታደሮች ላይ በጥቂት ሙጃሂዲን ወታደሮች ስኬታማ የሆነው ለምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? እስልምና ወደ ቺቺኒያ፣ ዳጊስታን፣ ታታሪስታን፣ ካዛኪስታን፣ ዑዝቤክስታን ብሎም መላው ራሺያ የመጣው በሱፍዮች አማካኝነት ነው። በተጨማሪም እነዚህ አካባቢዎች እስልምናን ከትውልድ ወደ ትውልድ የተላለፈውም ከኮሚኒዝም የተጠበቀውም በተሰውፍ ነው» «እስልምና እንዴት እንደተጠበቀ ታውቃላችሁ? በዚክር እና ረሱል (ሰዐወ) ላይ ሰለዋት በማውረድ ነው። እኛ ቺችኖች ቃድሪዎች እና ናቅሻባንዲዎች ነን። ወደ ጦርነት ከመሄዳችን በፊት ክብ ሰርተን ቃሲደቱል ቡርዳህ እና አል―ሞደሪያ እንቀራለን።» «ሁላችንም በጋራ እና ጮክ ብለን እናዜማለን። ድምፃችን ከርቀት አንድ ሆኖ ይሰማል። ከዚያም በረሱል ላይ ሰለዋት ካወረድን በኋላ ዚክር እንላለን። በሰይዲ ላይ ሰለዋት ካወረድንና ዚክር ካደረግን በኋላ ሄደን እንዋጋለን።» ISLAMICUNIFICATION
Show all...
#ከቅዱስ-ቁርአን ጋር በጎ መስተጋብር! #ታላቁ ኢማም(ኢማሙል-አዕዞም)፣ አቡሀኒፋ(ኑዕማን ኢብኑ ሣቢት) ከ699-767 ዓ.ል የኖሩ ሊቅ ናቸው። በስማቸው የተሰየመው እና ዒራቅ ውስጥ የሚገኝ ዩኒቨርስቲ #በቅርቡ ባወጣው መረጃ መሠረት፦ በሕይዎት ዘመናቸው(በ68 ዓመታት)፣ ቅዱስ-ቁርአንን ለ7000 ጊዜ ያኽል አኽትመው አንብበዋል። #ይኽ ስሌት፣ 1,000,000,000 ፈትዋዎችን ሲያዘጋጁ ቁርአንን በወፍ-በረር የቃኙበትን ሂደት አለማካተቱ ደግሞ፣ የንባብ አድማሳቸውን አርቆ ያስመለክታል። በወርሀ-ረመዷን 60 ጊዜ፣ እንዲሁም በአዘቦት ዕለታት #በአንድ ረከዓ የማኽተም ልምዳቸውን መረጃው አካትቷል። ያ ኹሉ የዕውቀት ዥረት፣ የልህቀት ፈነጠቅ፣ #ከቁርአን ጋር ከነበራቸው በጎ መስተጋብር የመነጨ ይመስላል። #አንፀባራቂ የልህቀት አድማሳቸውን በቀላሉ መናኘት ባይቻልም፣ ህሊናን ከነገር፣ ከቂም፣ ከቁርሾ፣ ከአሉባልታ...ለማፅዳት፣ #የደጋጎችን ፈለግ በዓቅም-ፈቀድ መከተል ይሽሻል!!! #በkedr taju #(ምስል፦ ማበሪያ) https://t.me/eslamicworld2
Show all...
The Islamic world 2🌎(የኢስላሙ አለም)

https://t.me/eslamicworld2

https://t.me/eslamicworld2

አብረን የጀመርነውን ትግል አብረን እንጨርሰዋለን መሪዎቻችንን ብቻቸውን አንተዋቸውም በማንኛውም ሠአት ከጎናቸው ነኝ ዲኔ ይመለከተኛል የምትል ነገ እሮብ 02:00 ፁምም አትፁምም ኻሊድ መስጂድ እንገናኝ የመጅሊስና የኡለማ ም/ቤት ጥሪ ነው ቤንስ ለ20 ሰው ሼር አድርጉ🙏
Show all...
በዛሬው እለት ኻሊድ መስጅድ ከመሻይኾች ከሙአዚኖች እና ከወጣት አመራሮች ጋር ገንቢ የሆነ ውይይት ያደረግን ሲሆን ፤ ሁሉም ወጣት ማህበራት ወደ ፊት ለምናደርጋቸው የትግል አቅጣጫዎች ላይ በተጠንቀቅ እንዲቆም እና የረመضاን አጀማመር በተመለከተ ከየ መስጅድ ኢማሞችጋር የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን። ኮ/ቻ ሪጆ ፖሊታን ከተማ አስ/እስ/ጉ/ም/ቤት
Show all...
🕋 ሰበር ረመዳን❤ ✍️ጨረቃ ዛሬ ባለመታየቷ የረመዳን ፆም ከነገ ወዲያ #ሀሙስ ይጀምራል‼️
Show all...
በዛሬዋ ቀን march 21 2013 ላይ ታላቁ የደማስቆ ሊቅ መውላና ሼኽ ሰዒድ ረመዳን አል ቡጢ እመስጂድ ውስጥ ዳዕዋ በማድረግ ላይ ሳሉ ነበር በሶሪያ ፅንፈኛ አማፂያን በተጠመደባቸው ቦንብ ህይወታቸው ያለፈው.. ደማቸው ፈሶ የያዙት ቁርዐን ላይ አሻራውን አሳርፏል... አል ፋቲሀ
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
የጫሌ ሼኽ ገበሬውን "እንዴት ነበር ሀድራው?" ብለው ቢጠይቁት እሱም "ምን እንደሚል ባናቀውም መቼስ ሲወዛወዙ ተወዛውዘናል" አላቸው። እናም ጌታው ሼኽ ሰይድ ኢብራሂም(ጫሌ) ተያ በኋላ ለንደኔ አይነቱ ደንጋራ 👉 "በዐረብ ስንነግረው መዕናው ስንቱን አከረው ባማርኛ እንንገረው ቢገባው እጂግ ስራ"😍 ብለው መድሁን በአጀም አበጁት። ........................... ...💚ብትከጅል በጌታው ሙሀባ መክበሩን 💚ፊት በነዚህ መውደድ እንክፈተው በሩን 💚ከዛ እንድናገኘው ድልብ መደበሩን 💚ፊት እንደሰማነው ወስፍ እና ኸበሩን 💚መላኢኮች በእጣችን ለካ ይገረሙት ❤️💚❤️💚❤️💚❤️💚❤️💚❤️💚❤️ 💚ኧረ ተው አንተየ ክፉ አትጠርጥር 💚ዱንያን ገንዘብ ብለህ እንዳትኸጥር 💚ሲዋን ከሀቂቃው አውጣና አበጥር 💚ቅብቅብ ዝራ ሲሉህ ዳዋ አትመንጥር 💚ሲያምርብን እንሀር-ርም እኒያ እንደሀረሙት 💚❤️💚❤️💚❤️💚❤️💚❤️💚❤️💚 💚ወንድሜ እንማከር ከሆዳችን አሁን 💚ወቀሳ አላነሳም ጉዞ ላይ አላሁን 💚ሂማ እና እስቲዕዳድህ ከኔ ጋራ ይሁን 💚ውስጥህ እንደውስጤ አንተም እንደኔ ሁን 💚በጅህ እንዲሽሩ ሁሉም የታመሙት 😍😍💚 ጁማአ ሸምሰድን መሀመድ ይሄኪታብ ምንደረሰ😋
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
በሀገራችን ኢትዮጵያ ከ200 አመት በላይ ባስቆጠረዉ መወሊድን ሐበሻ ላይ በጀመሩት የጀማ ንጉሱ ሸህ መሀመድ ሻፊ (ሙጃሂዱ) መኡነቱል ፈቂር የተሰኘዉን ኪታብ መጋቢት 10 እሁድ የሀገራችን ታላላቅ ዑለሞች ዱዐቶች እና ማዲሆች በተገኙበት ቦሌ በአለም ሲኒማ ከጠዋቱ 3:00 በደማቅ ሁኔታ ይመረቃል። በእለቱ ፕሮግራም ላይ ከግጥም እና ከተለያዩ ቁምነገር አዘል የጥበብ ስራዎች በተጨማሪ ማዲህ ፉአድ ሸምሱ መድረኩ ላይ አዲስ ስራዉን ይዞ ይቀርባል። ሌላ ታላቅ ሰርፕራይዝም ይኖረናል። በዋናነት በእለቱ የሚመረቀዉ ኪታብ በተለያዩ ቦታዎች በሚገኙ ሐሪማዎች ደረሶች እንዲቀሩበት በማድረግ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣዉን የቀደምት የሐበሻ መሻዒኾቻችን አስተምዕሮት እንዲቀጥል የበኩላችንን ሀላፊነት ለመወጣት ጊዜ እዉቀት ገንዘባችንን ለመሰዋት ቆርጠን ተነስተናል ። እናንተም ከዚህ በፊት በተለያየ መንገድ እኛን ለማገዝ የነየታችሁትን እያስገባችሁ'ና መጽሀፎች እየገዛችሁ መደ ሐሪማዎች እንዲደርሱ የበኩላችሁን እንድትወጡ እላለሁ። Note ፦ በእለቱም ሆነ በቀጣይ በሚሸጡ መፅሐፍቶች ሆነ በሚነየቱ ብሮች ቀጣይ ኢንሻአላህ በየ አካባቢዉ ያሉ መሻኢኾቻችን ፍቃዳቸዉን ጠይቀን ኪታቦቻቸዉን ለማሳተም እና ።ደራሽ እንዲሆን ጠንክረን ለመስራት አስበናል። የፕሮግራሙ መግቢያ 100 ብር።ማንም እንዳይቀር። ❤️ትኬቶች የሚገኙበት ቦታዎች 💚0911460435 ሸጎሌ 💚+251912879958 መርካቶ 💚+251944205544 አጠና ተራ 💚+251920663539 ጀሞ 💚+251922909503 ፒያሳ ለበለጠ መረጃ *0911664544 *0921727340
Show all...
በነቀምት ሙስሊሞች ላይ ከፍተኛ ድብደባ ተፈፀመ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የነቀምት ፈትህ  መስጊድ ኮሚቴ በቀን 30/05/2015  በመዝገብ ቁጥር 14604 ለነቀምት ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ሁከት ይወገድልኝ ብሎ አቤቱታ ያቀረበ ሲሆን የህገ ሂደቱ በቀጠሮ ላይ ያለ ቢሆንም በዛሬው እለት 12/6/2015 በከተማው ፖሊስ የታገዘ የህገወጡ መጅሊስ ቡድን በመስጂዱ ላይ ጥቃት አደረሰ። የመስጊዱ አስተዳዳሪ ሀጅ መሀመድ አደም ነገዎ ታስረው በ20ሺ ብር ዋስ አርብ እለት ከእስር ቢፈቱም በዛሬው እለት ከፍተኛ ድብደባ ተፈፅሞባቸው መንቀሳቀስ በማይችሉበት ሁኔታ ላይ ይገኛሉ። የአካባቢው ፖሊስ ከፅንፈኛው የወሀቢያ ቡድን ጋር በመሆን በመስጂድ ውስጥ በፈፀመው ድብደባ መስጊዱ በደም ጨቅይቶ ሰው እንዳይገባ ታግዶ የመስጂዱ ኢማም በመስጊዱ ውስጥ ታፍነው ይገኛል። በርካታ ሙስሊሞች ከፍተኛ ድብደባ ተፈፅሞባቸው በህክምና ላይ ይገኛሉ። ይህን ሁሉ በደል እና ሰቆቃ በነቀምት ሙስሊሞች ላይ እየተፈፀመ ያለው ፌደራል መጅሊሱን በህገወጥ መንገድ ተቆጣጥሮ የሚገኘው ሀጅ ኢብራሂም ቱፋ በሚሰጠው ቀጥተኛ ትእዛዝ ነው። ህዝበ ሙስሊሙ ይህ ግለሰብ በሙስሊሙ ላይ እያደረሰ ባለው በደል ለፍርድ እንዲቀርብ ማድረግ ይኖርበታል።                                           https://t.me/eslamicworld2 https://t.me/eslamicworld2
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.