366
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
April '24
April '24
+7
in 0 channels
March '24
+19
in 0 channels
Get PRO
February '24
+37
in 0 channels
Get PRO
January '24
+57
in 0 channels
Get PRO
December '23
+57
in 0 channels
Get PRO
November '23
+21
in 0 channels
Get PRO
October '23
+274
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 24 April | 0 | |||
| 23 April | 0 | |||
| 22 April | 0 | |||
| 21 April | 0 | |||
| 20 April | 0 | |||
| 19 April | +1 | |||
| 18 April | 0 | |||
| 17 April | +1 | |||
| 16 April | 0 | |||
| 15 April | +1 | |||
| 14 April | +1 | |||
| 13 April | 0 | |||
| 12 April | 0 | |||
| 11 April | 0 | |||
| 10 April | 0 | |||
| 09 April | 0 | |||
| 08 April | +2 | |||
| 07 April | 0 | |||
| 06 April | +1 | |||
| 05 April | 0 | |||
| 04 April | 0 | |||
| 03 April | 0 | |||
| 02 April | 0 | |||
| 01 April | 0 |
Channel Posts
አልሐምዱሊላሂ! አፍራህ ደህና ናት። አያታለሁ ዛሬም!
________
“እንዴት ነህ አሚ…?” ሰጠራው እንደዛ ነበር።
“አልሃምዱሊላሂ… !! ደህና ነህ አቡቹ…? ማሻ አላህ! ! አምሮብሃል! !” አለኝ ትከሻዬን በቀኙ ቸብ ቸብ እያደረገ። እኔ ስላማረብኝ ብቻ አቤት ፊቱ ላይ የነበረው ደስታ! !እኔም እንደዛው ሳልሆን አልቀረሁም የእኔ ግን ስላገኘሁት ነበር። ምሳ እየበላን የባጥ የቆጡን አዎራን።
አልአሚን ትምህርቱን ከአስረኛ ክፍል አቋርጧል። እናቱን ለማስታመም ነበር ያቋረጠው። እናቱ አልተረፉም። ከዛ በኃላ መቀጠል አልፈለገም። እዛው ሸርፍ ተራ የድለላ ስራ እየሰራ፣ ረዳትነትም እየሞከረ ቀልጦ ቀረ። ያ ፈጣንና አስገራሚ አእምሮ የነበረው አልአሚን በቃ ይኼው ሆነ ዕጣ ፈንታው…።
እየፈራሁ የማይቀረውን ጥያቄ አስከተልኩ፤
“እኔ የምልህ እ… አፍራህስ አለች?”
ዝምምምምምምም አለ አልአሚን። እናም ቅሬታ የተቀላቀለ ፈገግታውን እያሳየኝ “አልሃምዱሊላሂ ሁለት ቆንጆ ልጆች ወልዳለች። እንዴት ያማምራሉ መሰለህ! ”አለኝ። ግራ ገባኝ፣ ግራ መጋባቴን አይቶ ካለንበት ፎቅ ላይ አሻግሮ ጫፍ የሚታይ ፎቅ በእጁ በያዛት የጫት እንጨት እየጠቆመኝ : “ … የነሱ ነው… አንድ ሃብታም አግብታ ይሄን ፎቅ ሠርተው እኖሩ ነው። ከስር ያለው ትልቅ ሱቅ የሷ ነው፣ ሁልጊዜ አያታለሁ፣ ወላሂ… አምሮባታል… !” አለኝ።
ከነቅሬታ ፈገግታ አቀረቀረ። ከረዥም ዝምታ በኃላ የምግብ ጠረጴዛው ላስቲክ ላይ እንባው ጠብ ሲል አየሁት። አቅፌ ወደ ራሴ አስጠጋሁት ፣ ከልቤ አዝኜ ነበር። እናም በእቅፌ እያለ ድምፁን ቀንሶ እንዲህ አለ፣ “አልሐምዱሊላሂ! አፍራህ ደህና ናት። አያታለሁ ዛሬም።”
ከዙበይዳ
(ገፅ፡ 14)
በአሌክስ አብርሃም
| 2 | No text... | 108 |
| 3 | ገጣሚና ሠዓሊ ገብረ ክርስቶስ ደስታ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ሥነ ጥበብ ታሪክ ውስጥ ስሙ ጎልቶ ከሚጠቀሱ የስነ ጥበብ ሰዎች ዘንድ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ እውቅና ታላቅ ሰው ነው፡፡
‹‹ጎልጎታ›› የገብረ ክርስቶስ ዘመን አይሽሬ (Classical) የሆነች በብዙዎች ነፍስ፣ አጥንትና ጅማት ድረስ ዘልቃ፣ የፍቅርን ብርቱ፣ ኃይልና ጽናት የምትገልጽ ሥራው እንደሆነች በርካታ አድናቂዎቹ ይመሰክራሉ፡፡ በአንድ ወቅት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ጥናት መጽሔት (Ethiopian Studies Journal) ላይ የገ/ክርስቶስ የጥበብ ልጁና የሙያው ባልደረባ የሆነው አቶ እሸቱ ጥሩነህ ስለ ገብሬ ታሪክና ስለ ‹‹ጎልጎታ›› ድንቅዬ የጥበበብ ሥራው ባቀረበው የጥናት ጽሑፉ እንዲህ ነበር ያለው፡-
… ይህ የገ/ክርስቶስ ደስታ የሥነ ሥቅለት ስዕላዊ ድርሰት የፍቅርን፣ የመሥዋዕትነትን፣ የቤዛነትን፣ የሕያውነትና የዘላለማዊነትን፣ እንዲሁም የነፃነትንና ሰላምን ምንነት ባጫሩ በሕብረ ቀለማት የቃኘበትና የተቀኘበት ነው፡፡ መስቀሉ እውነታዊ ነው፡፡ የተሰቀለው ክርስቶስ ግን ተምሳሌታዊ ነው፡፡ ሥዕሉ እስከተሠራበት እስከዚያን ጊዜ ድረስ ብዙ ሠዓሊዎች አካሉን ወይም ስጋውን አልፎም እውነታዊ ምስሉን ከነስቃዩ ይስላሉ እንጂ፣ እንደ ገብረ ክርስቶስ ክቡር ደሙን፣ ንጹሕ መሥዋዕትነቱን በቀይ ሕብረ ቀለም ብቻ ተምሳሌት አድርገውና ወሰነው የሠሩ የሉም … ፡፡
ይህን በሚመለከት ይላል አቶ እሸቱ ጥሩነህ፣ ‹‹የገብረ ክርስቶስ ደስታ፣ አጭር ትውስታና ጨረፍታዊ ዕይታ›› በሚል ርዕስ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ባቀረበው በዚሁ ጥናቱ፣ ይህን በሚመለከት የጀርመን አገር ጓደኛው የነበረው ዶ/ር እጓለ ገብረ ዮሐንስ እንዲህ በማለት ጽፏል ይለናል፡-
ሰዓሊ ተብሎ የጎልጎታን ተራራ ያልወጣ፣ የቀራኒዮን ትልቁን ትራጀዲ ያላየ የለም፤ ግን የገብረ ክርስቶስ ሥነ-ስቅለት ለብቻው ነው፡፡ ቀለም ተናጋሪው ነው፣ የሚታየው ንጹሕ ደም ብቻ ነው፡፡ ግራና ቀኝ የነበሩት (የተሰቀሉት) እነ ፋይታዊ ቦታ የላቸውም ተዘንግተዋል፡፡ ወይም ሠዓሊው ሊያያቸው አልፈለገም፣ ይገርማል፡፡ ጥበብ ከንጹሕነት ከጽርየት ከርቀት ብቻ እንጂ ከሌላ ጋር ግንኙነት የሌላት መሆኑን ለመረዳት ይቻላል፡፡
ዛሬም ድረስ የገ/ክርስቶስ የፍቅር፣ የናፍቆት፣ የነፍሱ ስቃይና ጣር የሆነችው ‹‹ጎልጎታ›› የፍቅር ሕያው መዝገብ፣ የጥበብ ቁንጮ ሥራ ሆና በዚህ ክብሯ፣ ማዕረጓና ሕያውነቷ ዘልቃለች፡፡ ፍቅርን በመሥዋዕትነት፣ ፍቅርን በእውነት፣ ፍቅርን በደም እየተረከች፣ በደም እየሞሸረች፣ በእሾኽ አክሊል፣ በደም እያነገሠች፣ በጦርና በችንካር በደም እያስዋበች፣ በደም እየተረከች… ፡፡
ይህ የገ/ክርስቶስ ዘመን አይሽሬ የሆነ የጥበብ ሥራው ለበርካታ ዓመታት በስደት ከቆየበት ከወደ አውሮፓ መጥቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በጀርመን መንግሥት እርዳታ በስሙ በተቋቋመው የስነ ጥበብ መዘክር ውስጥ ይገኛል፡፡
* * *
ምንጭ ፦ https://www.zehabesha.com/amharic/archives/2702 | 171 |
| 4 | No text... | 127 |
| 5 | #አማካይ_ጦርነት_የሚባል_ነገር_የለም!
ከሌሎች 49 ሰዎች ጋር ሆነህ በመኪና እየሄድክ ነው እንበል፡፡ ቀጣዩ ፌርማታ ላይ መኪናው ሲቆም የአሜሪካ የመጨረሻው ከባድ ሰው ገባ፡፡
ጥያቄ፡-
የተሳፋሪዎቹ አማካይ ክብደት ምን ያህል ይጨምራል? 4%?፣ 5%? እንደዚያ አካባቢ ነው የሚሆነው፡፡
ትንሽ እንደሄዳችሁ ደግሞ መኪናው ቆመና ቢልጌት ወደ መኪናችሁ ገባ እንበል፡፡ አሁን ጉዳያችን ክብደት አይደለም፡፡
ጥያቄ፡-
ቢልጌት ከገባ በኋላ የተሳፋሪዎቹ የሃብት መጠን አማካይ በስንት ይጨምራል? 4%? 5%? በፍፁም፤ ከዚያ እጅግ ይርቃል፡፡
እስኪ ሁለተኛውን ጥያቄ ቶሎ እንመልከተው፡፡
ቢልጌት ከመግባቱ በፊት የነበራችሁት 50 ተሳታፊዎች የሃብት መጠን አማካይ 54,000 ዶላር ነው እንበል፡፡ ይህ አማካይ ነው፡፡ በዚህ ላይ ቢልጌት ተጨመረበት፡፡ የቢልጌት ሃብት 59 ቢሊዮን ዶላር አካባቢ ነው፡፡ በ50ዎቹ ተሳፋሪዎች ላይ ይህ ሃብት ተጨምሮ ሲሰላ የሙሉ ተሳፋሪዎቹ አማካይ የሃብት መጠን ወደ 1.15 ቢሊዮን ዶላር ይተኮሳል፡፡ ይህም ከ2 ሚሊዮን በመቶ በላይ ጨመረ ማለት ነው፡፡ እዚህ ታሪክ ውስጥ ማየት የሚቻለው አንድ ሰው የ‹አማካይ›ን ትርጉም እንዴት እንደሚያዛባው እና ትርጉም አልባ እንደሚያደርገው ነው፡፡
#ስለምታስበው-አስብ መጽሐፍ | 236 |
| 6 | ሁሉም ሰው በማያልቅ ህመም የተሸነፈ ነው። በልቤ ልያዘው እኔ ጋር ይቅር ብሎ እንጂ ሀዘን የሰዎች የልብ ቋንቋ ከሆነ ሰነባብቷል። ጨለምተኛ ላለመሆን ብንሞክርም የሚቁረቁር እውነታ በልባችን አለ ።
አንዳንዱ በፍቅር ፣ በኑሮ ፣ በድግግሞሽ ዝሏል ፤ ሁሉም ሚያለቅስበትን ትከሻ ፈላጊ ነው ። ሀሳቦች ተስፋን ሚያሸሹ ፣ ወሬው የሚያርድ ሆንዋል። በሁሉም ማዕዘን የስሜት አቅላችን ቦታው ተዛብቷል ። ቢሆንም ለህመም ከመዘመር ይልቅ ለተስፋ ማሸርገድ ትልቅ ጥቅም አለው። ስሜትን ሚያነብ አእምሮ ይዘን በህመማችን መቆየት የድባቴ ጭፍራ ከመሆን ውጪ ምን ሊረባን ? ድባባችንን፣ ሙዳችንን መቀየር እየቻልን ?.... የሆነው ሆኖ ንግግር ያማረ ነገር ነው ። ንግግር ፍትሃት ነው ፣ ተነጋገሩ ፤ ተወያዩ ፣ እንዴት ነህ ፥ ምነው ፊትህ ዳመነ ? ተባባሉ ለሰው ግድ ይኑራችሁ ። ህመማችሁን በሰው አክሙ ፣ አምላካችሁን አውሩ። ችግር ሁሉ መፍትሄ አያሻውም ችሎ መኖር የህይወት አንድ ሃቂቃ ነው።
ያጋጠማችሁ ነገር የናንተ ውስን እውነታ አይደለም፤ ስለዚህ ቢያማችሁም፣ ቢከፋችሁም ከምንም ነገር ህልውናችሁ ይበልጣል ፣ ያልተጭበረበረ፣ ያልተፎገረ ተስፋ ፈልጉ ፣ ደስታን ከሚጨርላችሁ ክስተቶች አትጉደሉ ፤ በሌላችሁ ነገርም ቢሆን ተስፋን አትጡ ፣ በመኖራችሁ እረፍት ሁኑ። ተፈጥሮን ሁኑ። ዝምታችሁ ይናገር ....እስትንፋሳችሁ ጥሩ ድባብ ውስጥ ይከተት ፤ መንፈሳችሁ ያረጋጋ ፤ ሳቃችሁ ለቅሶዋችሁን ያሳይ ፤ ፍቅርን ሰው ላይ አጋቡ ፣ ትህትና ልብሳችሁ ይሁን ፣ ቅንነት እንደ ስማችሁ ይታተምባችሁ ፥ ያመናችሁትን ከልብ እመኑ ፤ ቃላችሁ የሰው ቀን ሚያፈካ ይሁን ፤ አቋማችሁ ቅንነት ፣ መርሃችሁ ትህትና ፣ ርዕየተ ዓለማችሁ ተስፋ ፣ መታወቅያችሁ ፍቅር ይሁን። ህይወትን በመፍራት ሳይሆን በመገምገም ኑሯት ፤ ቅጽበት ውስጥ ደስታን ፈልጉ .....
የምታደርጉትን ነገር በምልዓት አድረጉ ፣ ስታነቡ ፣ ሙዚቃ ስትሰሙ ፣ በመጠሞን ፣ በመመሰጥ አድርጉት። ሁሉ ነገር ላይ ጥሩ ትዝታ እስኪኖራችሁ ድረስ የምታደረጉትን አትልቀቁት ፣ ...ከእውቀት..ሰው ፣ ከፍራንክ.. ወዳጅ እንደሚበልጥ መገንዘብ ኑሮን መቅደም ነው። Any ways ተስፋ የህመም ማጣፊያ ነው። የምትጠልቀው ጀንበር ተስፋን ልታሳየን ነው የምትጠልቀው ፤ የታመመ ሰው መዳን ባይኖር ሞት ምርጫው አልነበርን ? አያችሁ መዳን አለ። ልብ በሉ መኖር ያምራል። ህመማችንን ቆይታ ያከስመዋል። በመኖር ውስጥ ተስፋ አለ። መኖር ደጉ ማለት ውብ የህይወት መርህ ነው።
........ መኖር ደጉ ..........
——————————————————————
እና ቡና ቆንጆ ነው ። ......ሌላ አጽናፈ ዓለም ውስጥ ያስገባል ፣ ሽታውን ፣ ጢሱን ፣ ጥፍጥናውን ሁሉን ያለመከልከል አጣጥሙ። እየጠጣችሁ ።
'' አቦል ጀባ ቀሃ ጀባ
የማይበጀን ገደል ይግባ '' እንዲል | 209 |
| 7 | ሁሉም ሰው በማያልቅ ህመም የተሸነፈ ነው። በልቤ ልያዘው እኔ ጋር ይቅር ብሎ እንጂ ሀዘን የሰዎች የልብ ቋንቋ ከሆነ ሰነባብቷል። ጨለምተኛ ላለመሆን ብንሞክርም የሚቁረቁር እውነታ በልባችን አለ ።
አንዳንዱ በፍቅር ፣ በኑሮ ፣ በድግግሞሽ ዝሏል ፤ ሁሉም ሚያለቅስበትን ትከሻ ፈላጊ ነው ። ሀሳቦች ተስፋን ሚያሸሹ ፣ ወሬው የሚያርድ ሆንዋል። በሁሉም ማዕዘን የስሜት አቅላችን ቦታው ተዛብቷል ። ቢሆንም ለህመም ከመዘመር ይልቅ ለተስፋ ማሸርገድ ትልቅ ጥቅም አለው። ስሜትን ሚያነብ አእምሮ ይዘን በህመማችን መቆየት የድባቴ ጭፍራ ከመሆን ውጪ ምን ሊረባን ? ድባባችንን፣ ሙዳችንን መቀየር እየቻልን ?.... የሆነው ሆኖ ንግግር ያማረ ነገር ነው ። ንግግር ፍትሃት ነው ፣ ተነጋገሩ ፤ ተወያዩ ፣ እንዴት ነህ ፥ ምነው ፊትህ ዳመነ ? ተባባሉ ለሰው ግድ ይኑራችሁ ። ህመማችሁን በሰው አክሙ ፣ አምላካችሁን አውሩ። ችግር ሁሉ መፍትሄ አያሻውም ችሎ መኖር የህይወት አንድ ሃቂቃ ነው።
ያጋጠማችሁ ነገር የናንተ ውስን እውነታ አይደለም፤ ስለዚህ ቢያማችሁም፣ ቢከፋችሁም ከምንም ነገር ህልውናችሁ ይበልጣል ፣ ያልተጭበረበረ፣ ያልተፎገረ ተስፋ ፈልጉ ፣ ደስታን ከሚጨርላችሁ ክስተቶች አትጉደሉ ፤ በሌላችሁ ነገርም ቢሆን ተስፋን አትጡ ፣ በመኖራችሁ እረፍት ሁኑ። ተፈጥሮን ሁኑ። ዝምታችሁ ይናገር ....እስትንፋሳችሁ ጥሩ ድባብ ውስጥ ይከተት ፤ መንፈሳችሁ ያረጋጋ ፤ ሳቃችሁ ለቅሶዋችሁን ያሳይ ፤ ፍቅርን ሰው ላይ አጋቡ ፣ ትህትና ልብሳችሁ ይሁን ፣ ቅንነት እንደ ስማችሁ ይታተምባችሁ ፥ ያመናችሁትን ከልብ እመኑ ፤ ቃላችሁ የሰው ቀን ሚያፈካ ይሁን ፤ አቋማችሁ ቅንነት ፣ መርሃችሁ ትህትና ፣ ርዕየተ ዓለማችሁ ተስፋ ፣ መታወቅያችሁ ፍቅር ይሁን። ህይወትን በመፍራት ሳይሆን በመገምገም ኑሯት ፤ ቅጽበት ውስጥ ደስታን ፈልጉ .....
የምታደርጉትን ነገር በምልዓት አድረጉ ፣ ስታነቡ ፣ ሙዚቃ ስትሰሙ ፣ በመጠሞን ፣ በመመሰጥ አድርጉት። ሁሉ ነገር ላይ ጥሩ ትዝታ እስኪኖራችሁ ድረስ የምታደረጉትን አትልቀቁት ፣ ...ከእውቀት..ሰው ፣ ከፍራንክ.. ወዳጅ እንደሚበልጥ መገንዘብ ኑሮን መቅደም ነው። Any ways ተስፋ የህመም ማጣፊያ ነው። የምትጠልቀው ጀንበር ተስፋን ልታሳየን ነው የምትጠልቀው ፤ የታመመ ሰው መዳን ባይኖር ሞት ምርጫው አልነበርን ? አያችሁ መዳን አለ። ልብ በሉ መኖር ያምራል። ህመማችንን ቆይታ ያከስመዋል። በመኖር ውስጥ ተስፋ አለ። መኖር ደጉ ማለት ውብ የህይወት መርህ ነው።
........ መኖር ደጉ ..........
——————————————————————
እና ቡና ቆንጆ ነው ። ......ሌላ አጽናፈ ዓለም ውስጥ ያስገባል ፣ ሽታውን ፣ ጢሱን ፣ ጥፍጥናውን ሁሉን ያለመከልከል አጣጥሙ። እየጠጣችሁ ።
'' አቦል ጀባ ቀሃ ጀባ
የማይበጀን ገደል ይግባ '' እንዲል | 1 |
| 8 | No text... | 164 |
| 9 | ጄሊ ፊሽ (Jelly Fish) ዝልግልግና ጃንጥላ መሰል፣ አልያም አውሮፓያን ለበረራ የሚጠቀሙበት ግዙፍ ፊኛ የሚመስል የዓሣ ዝርያ ነው። የጀርባ አጥንት የለውም። ልክ እንደ ጃንጥላ ተዘርግቶ እንደ ፊኛ ተነፍቶ መንቀሳቀስ ሲፈልግ፣ ጭብጥ ዘርጋ፣ ጭብጥ ዘርጋ እያለ መቅዘፍ ይችላል። እንቃስቃሴውን ሲያስቆም ቁልቁል ወደ ባህሩ ከርስ ይሰጥማል። አያሌ ቅጥልጣይ አካል ስላለው በእነሱ በሚፈጥረው እንቅስቃሴ ዝግ ብሎም መንሳፈፍ ይችላል።
ማንኛውም ፍጥረት አይነካውም ፤ ከነካው በመርዛማ መንደፊያው ነድፎ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ይገላግለዋል። ተነዳፊው ልክ በመርዘኛው ኮብራ እባብ የተነደፈ ያህል በምድር ላይ በሕይወት መቆየት የሚችለው ሦስት ደቂቃ ብቻ ነው።
ጄሊ ፊሽ ብርቱካናማ፣ ነጭ፣ ደማቅ ሰማያዊ ቀለማት ህብር ፈጥረው ስለሚኖሩት አያሌ የባህር ውስጥ ፍጥረታት ቀለሙ አማሏቸው ባለማወቅ ይነኩትና ለህልፈት ይዳረጋሉ። ጄሊ ፊሹም በነዳፊ አካሉ ስቦ ወደ ከርሱ ይወረውርና ዋጥ ስልቅጥ ያደርጋቸዋል። በአዕምሮ ብቃት ይበል የተባለለት ዶልፊን እንኳ በፈጣን ዋና ላይ ሆኖ ድንገት ጄሊ ፊሽ እጅ ላይ ይወድቃል። አልያም አደገኛው ሻርክ እንዲሁ ይሰግራል። የጄሊ ፊሽን አደገኛነት አስቀድመው የሚያውቁ የባህር ፍጡራን ብቻ በርቀት በመሸሽ ራሳቸውን ይከላከላሉ። ከእነዚህ መካከል ሕይወታቸው ከባህር ጋር የተቆራኘው መርከበኞች በዋና ወቅት ባህር ላይ ጄሊ ፊሽን ሲንሳፈፍ ካዩት አቅጣጫቸውን ቀይረው ከአደጋው በመሸሽ ራሳቸውን ይከላከላሉ። ዓሣዎች ከአፈጣጠራቸው ወደፊት እንጂ ወደኋላ መዋኘት ስለማይችሉ ለብዙ ጊዜያት የጄሊ ፊሽ ሲሳይ ይሆናሉ። ብዙ ጊዜ ከርቀት አይተውት ወደ ጎን በመጠምዘዝ ከአደጋው ራሳቸው ይጠብቃሉ።
ጄሊ ፊሽ በባህሩ ዓለም ታፍሮ እና ተከብሮ ቢኖርም፣ ሁሌም አንድ ታሪካዊ ስህተት ይሰራል። ይኸውም ቀንድ አውጣን ሲያገኘው ልክ እንደሌሎቹ ፍጥረታት እንዲበላው የተፈጠረ እንስሳ መስሎት ይውጠዋል። ይህ ታላቅ ስህተት ጄሊ ፊሽን ነብሱን ያስከፍለዋል። ቀንድ አውጣ የሠራ አካላቱ ሙሉ በሙሉ በአጥንት መሳይ ቅርፊት የተሸፈነ በመሆኑ የጄሊ ፊሽ መርዝ ቀንድ አውጣውን አያገኘውም። ስለዚህ ቀንድ አውጣ ጄሊ ፊሽን ሆድቃ ውስጥ ኑሮውን እንደወትሮው እያዘገመ እየተጓዘ ይጀምራል። የጄሊ ፊሹ ሆድቃ በጣም ሰፊ ስለሆነ ለቀንድ አውጣው ታላቅ አዳራሽ ያህል ነው። አየሩም እንደልብ ነው። ቀንድ አውጣ ምግብ ሲያሻው ከጄሊ ፊሹ ሆድቃ ቦጨቅ ያደርግና ይበላል። ኑሮው የምቾት ሆኖ አንድም አደጋ የሚጥል፣ አጥንት እንደ አገዳ የሚቆረጥም ጠላት ሳያጋጥመው የጄሊ ፊሹን አካል፣ ቀንድ አውጣው በራሱ ጥበብ መርዛማነቱ አርክሶት ምግብ በማድረግ ለረጅም ጊዜ እየበላው ይከራርምበታል። ጄሊ ፊሽም የተጠናወተው ነቀርሳ ምን እንደሆነ ሳያውቅ ተቆንጥሮ፣ ተቆንጥሮ ያልቃል። ያ አገር የሚሸፍን፣ ያ ባህር የሚያለብስ ግዙፍ አካል የተቆራኘውን ሕመም ሳያውቀው ሁሌም «ወይኔ!» እንዳለና እንደተከዘ ተበልቶ ያልቃል። ቀንድ አውጣውም በድል አድራጊነት እንደገና ወደ ባህር ይመጣና ሌላ የሚበላው ጄሊ ፊሽ ፍለጋ ባህሩ ውስጥ ያዘግማል።
ይህ ቀርፋፋ፣ ይህ ዐይነ ገብ ያልሆነ፣ ኩርማን ፍጡር ኃያሉን ሽባ የሚያደርግበትን ምስጢር ለማንም አይተነፍስም። የቀንድ አውጣዎች ታላቅ ምስጢር እንደሆነ ለዘለዓለሙ ይቀጥላል።
* * *
መልህቅ
…
(ገፅ፡ 80 - 81)
…
ዘነበ ወላ | 195 |
| 10 | No text... | 141 |
| 11 | ጄሊ ፊሽ (Jelly Fish) ዝልግልግና ጃንጥላ መሰል፣ አልያም አውሮፓያን ለበረራ የሚጠቀሙበት ግዙፍ ፊኛ የሚመስል የዓሣ ዝርያ ነው። የጀርባ አጥንት የለውም። ልክ እንደ ጃንጥላ ተዘርግቶ እንደ ፊኛ ተነፍቶ መንቀሳቀስ ሲፈልግ፣ ጭብጥ ዘርጋ፣ ጭብጥ ዘርጋ እያለ መቅዘፍ ይችላል። እንቃስቃሴውን ሲያስቆም ቁልቁል ወደ ባህሩ ከርስ ይሰጥማል። አያሌ ቅጥልጣይ አካል ስላለው በእነሱ በሚፈጥረው እንቅስቃሴ ዝግ ብሎም መንሳፈፍ ይችላል።
ማንኛውም ፍጥረት አይነካውም ፤ ከነካው በመርዛማ መንደፊያው ነድፎ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ይገላግለዋል። ተነዳፊው ልክ በመርዘኛው ኮብራ እባብ የተነደፈ ያህል በምድር ላይ በሕይወት መቆየት የሚችለው ሦስት ደቂቃ ብቻ ነው።
ጄሊ ፊሽ ብርቱካናማ፣ ነጭ፣ ደማቅ ሰማያዊ ቀለማት ህብር ፈጥረው ስለሚኖሩት አያሌ የባህር ውስጥ ፍጥረታት ቀለሙ አማሏቸው ባለማወቅ ይነኩትና ለህልፈት ይዳረጋሉ። ጄሊ ፊሹም በነዳፊ አካሉ ስቦ ወደ ከርሱ ይወረውርና ዋጥ ስልቅጥ ያደርጋቸዋል። በአዕምሮ ብቃት ይበል የተባለለት ዶልፊን እንኳ በፈጣን ዋና ላይ ሆኖ ድንገት ጄሊ ፊሽ እጅ ላይ ይወድቃል። አልያም አደገኛው ሻርክ እንዲሁ ይሰግራል። የጄሊ ፊሽን አደገኛነት አስቀድመው የሚያውቁ የባህር ፍጡራን ብቻ በርቀት በመሸሽ ራሳቸውን ይከላከላሉ። ከእነዚህ መካከል ሕይወታቸው ከባህር ጋር የተቆራኘው መርከበኞች በዋና ወቅት ባህር ላይ ጄሊ ፊሽን ሲንሳፈፍ ካዩት አቅጣጫቸውን ቀይረው ከአደጋው በመሸሽ ራሳቸውን ይከላከላሉ። ዓሣዎች ከአፈጣጠራቸው ወደፊት እንጂ ወደኋላ መዋኘት ስለማይችሉ ለብዙ ጊዜያት የጄሊ ፊሽ ሲሳይ ይሆናሉ። ብዙ ጊዜ ከርቀት አይተውት ወደ ጎን በመጠምዘዝ ከአደጋው ራሳቸው ይጠብቃሉ።
ጄሊ ፊሽ በባህሩ ዓለም ታፍሮ እና ተከብሮ ቢኖርም፣ ሁሌም አንድ ታሪካዊ ስህተት ይሰራል። ይኸውም ቀንድ አውጣን ሲያገኘው ልክ እንደሌሎቹ ፍጥረታት እንዲበላው የተፈጠረ እንስሳ መስሎት ይውጠዋል። ይህ ታላቅ ስህተት ጄሊ ፊሽን ነብሱን ያስከፍለዋል። ቀንድ አውጣ የሠራ አካላቱ ሙሉ በሙሉ በአጥንት መሳይ ቅርፊት የተሸፈነ በመሆኑ የጄሊ ፊሽ መርዝ ቀንድ አውጣውን አያገኘውም። ስለዚህ ቀንድ አውጣ ጄሊ ፊሽን ሆድቃ ውስጥ ኑሮውን እንደወትሮው እያዘገመ እየተጓዘ ይጀምራል። የጄሊ ፊሹ ሆድቃ በጣም ሰፊ ስለሆነ ለቀንድ አውጣው ታላቅ አዳራሽ ያህል ነው። አየሩም እንደልብ ነው። ቀንድ አውጣ ምግብ ሲያሻው ከጄሊ ፊሹ ሆድቃ ቦጨቅ ያደርግና ይበላል። ኑሮው የምቾት ሆኖ አንድም አደጋ የሚጥል፣ አጥንት እንደ አገዳ የሚቆረጥም ጠላት ሳያጋጥመው የጄሊ ፊሹን አካል፣ ቀንድ አውጣው በራሱ ጥበብ መርዛማነቱ አርክሶት ምግብ በማድረግ ለረጅም ጊዜ እየበላው ይከራርምበታል። ጄሊ ፊሽም የተጠናወተው ነቀርሳ ምን እንደሆነ ሳያውቅ ተቆንጥሮ፣ ተቆንጥሮ ያልቃል። ያ አገር የሚሸፍን፣ ያ ባህር የሚያለብስ ግዙፍ አካል የተቆራኘውን ሕመም ሳያውቀው ሁሌም «ወይኔ!» እንዳለና እንደተከዘ ተበልቶ ያልቃል። ቀንድ አውጣውም በድል አድራጊነት እንደገና ወደ ባህር ይመጣና ሌላ የሚበላው ጄሊ ፊሽ ፍለጋ ባህሩ ውስጥ ያዘግማል።
ይህ ቀርፋፋ፣ ይህ ዐይነ ገብ ያልሆነ፣ ኩርማን ፍጡር ኃያሉን ሽባ የሚያደርግበትን ምስጢር ለማንም አይተነፍስም። የቀንድ አውጣዎች ታላቅ ምስጢር እንደሆነ ለዘለዓለሙ ይቀጥላል።
* * *
መልህቅ
…
(ገፅ፡ 80 - 81)
…
ዘነበ ወላ | 1 |
| 12 | No text... | 1 |
| 13 | ጓደኛዬ ቤት ሁሌ የምሄደው ታናሽ እህቱን ለማየት ነበር ። ታናሽ እህቱ ዘቢብ ትባላለች ። አጠያየሟ ፣ ድርብ ጥርሷ ፣ ሳቋ ፣ የፀጉሯ ብዛት፣ ድምጿ ፣ ፈገግታዋ ስለሚናፍቀኝ ቤታቸው እሄዳለሁ ።
የታላቅ ወንድሟ ጓደኛ ስለሆንኩ እንደወንድ እያየችኝ አትሽኮረመምም እንደታላቅ ወንድሟ ነው የምትሰማኝ ።
እሷ ካለች ቤታቸው ጭር አይልም ። እጫወታለሁ፣ አመሻለሁ ፣ ከቤታቸው ውጣ ውጣ አይለኝም ፤ ከሷ ሌላ የማየው ሰው አልነበረም ።
ታላቅ ወንድሟ ሲቆጣት በስሱ አግዝላታለሁ ።
ድንገት ግን ከጓደኛዬም በላይ፣ ከዘቢብም በላይ ጋሽ ንጉሴ ቀልቤን ገዙኝ ። ጋሽ ንጉሴ አባታቸው ናቸው።
ምናቸውም ደስ አይለኝም ነበር ። ኮስተር ይላሉ፣ ግንባራቸው አይፈታም ከሙሉ ቀን ጋር ብቻ ነው የሚጫወቱት። ሙሉቀን የቤቱ የመጀመሪያ ልጅ ነው ። 'Down Syndrome' አለበት
(የአእምሮ እድገት ውስንነት )
እቤት ሲገቡ "ሙሌስ?" ይላሉ ። በእጃቸው ይዘው የሚመጡትን በቆሎ ፣ ቆሎ ፣ ዳቦ ጠቅላላ ላንተ ነው ይሉታል። ሁሉንም እንደዋዛ ጨብጠው "ሙሌ" ብለው ያቅፉታል ።
ሙሌን ከጓደኛዬ በላይ፣ ከዘቢብ በላይ፣ ከቤቱ መጨረሻ ልጅ ከሚኪ በላይ ፣ ይወዱታል። ጓደኛቸው ነው ። ብዙ ግዜ አመሻሽ ላይ ሸራተን ሆቴል ጋር ባለው ቁልቁለት እና ዳገት መውረጃ እና መውጫውን በዝግታ እየተላፉ ፣ እየታገሉ ፣ እጅ ለእጅ ተያይዘው ሲንሸራሸሩ አይቻቸው አውቃለሁ ።
ከልጆቻቸው ሁሉ ሙሌን እንደሚወዱት አወቅኩኝ። የጋሽ ንጉሴ እና የሙሌ ሁኔታ ቀልቤን ገዛኝ ፤ ሁሉንም ረሳኋቸው ።
ጓደኛዬን "ጋሽ ንጉሴ ሙሌን ይወዱታል ኣ?" ስለው ፤
"ሰምተኽው አታውቅም እንዴ ? ሙሌ ይሙት እያለ ነው እኮ የሚምለው ። ሙሌ ካመመው እኮ ስራ ራሱ አይሄድም። የኔ ዘንካታ ፣ የኔ የዋህ ሲለው ነው የሚውለው ።
ያበዘዋል ባክህ !
ሲፀልይ ከኔ በፊት ያድርገው እያለ እኮ ነው ። " አለኝ።
ጋሽ ንጉሴ ሙሌ አድጎ እንደማይጦራቸው ፣
ስማቸውን እንደማያስጠራላቸው ፣ ውለታቸውን እንደማይተነትን ያውቃሉ። ግን ሙሌን በበለጠ ይወዱታል ።
እውነተኛ ፍቅር ምላሽ ሳይጠብቁ ውለታ እንደማያገኙ እያወቁ መውደድ ነው አይደል?
ጋሽ ንጉሴን አማቴ ካላደረኳቸው ሞቻለሁ !!
© Adhanom Mitiku | 174 |
| 14 | አንተ የደን ባለሙያ ነህ። በዚህ መስክ ደግሞ ትልቁን ዲግሪ ልታገኝ እየተዘጋጀህ ነው። ሙያህ የተመሰረተው በዛፎች ላይ ነው። እድሜ ዘመንህን የምትጠራበት ሙያ ያሰጡህ የዛፎች በዚህ ምድር ላይ መኖር ነው። የሙያህ መሠረቶች ናቸው። እነርሱ ላንተና ለእኔ ብርቅዬ ፍጥረት ናቸው። ስለ እነርሱ ከማወቅህ በፊት ልትወደቸው ግድ ነው ፤ ቀጥሎ ሥነ - ፍጥረተቸውን ለማወቅ ትጥራለህ። በመውደድ ለማወቅ ስትጥር ደግሞ የእውቀቱን ሂደቱንም ትወደዋለህ። አሁን የምንቆፍረው የምንወዳቸውን ዛፎች ተጋድሏቸውን ለማወቅ ነው።
አየህ! አንተ በዶማና አካፋ ለመቆፈር ያደከመህን መሬት እነርሱ ህዋሳቸውን ገብረው ሰርስረው፣ ሰንጥቀው ያለፉት ነው። በዚህ ድካማቸው የተፈጥሮ ሚዛንን ይጠብቃሉ፣ በጎርፍ የአፈር መካላትን፣ የመሬት ሙቀትንና የአየር ብክለክትን ይከላከላሉ። ተፈጥሮ በሠጠቻቸው ፀጋ ለምድሪቱ በረከትና ልብስ፣ ጌጥና ውበት ናቸው። እኔ እና አንተ ደግሞ በሰው ልጆች ዓለም እነርሱን ወክለን ስለ እነርሱ ጥቅም ግርማ የምንናገር ባለሙያዎች ነን። እናም መሬት የምንቆፍረው በላብራቶሪ የምንርመጠመጠው የእነርሱ ሙሉ ወኪል ለመሆን ነው። አንተ ትናንተ የደከምከውን ድካም ያ ታደጊ ችግኝ ለሁለት ዓመታት ደክሞታል። ይህን ድካሞቸውን ስትርዳ ያለአግባብ ሲጨፈጨፉ ህመሙ ወደ እናንተ ማጋባት ነው እንጂ እናንተን በቁፋሮ ለማድከም አይደለም።
~
ችቦ - ዓለማዬሁ ዋሴ | 170 |
| 15 | No text... | 141 |
| 16 | "ምን ይናፍቅሀል ?..."
"የድሮ ቀናቶች...."
"የትኞቹ...?"
"ሳቃችን ከቤታችን ጣሪያ በላይ የነበረበት...አንዳችን ምግብ አልበላም ካልን አንዳችን የምንደበርበት...ብቻ ብዙ ብዙ...በብርድ ሰበብ የተቃቀፍንበት...ተቃቅፈን የተላቀስንበት..."
"እሺ ሌላስ...."....እነዚህ ሳይካትሪስት ተብዬዎች ማስለፍለፍ አይሰለቻቸውም... ምን ሌላስ አለው...
"እሷ ...እና የእሷ የሆነ ነገር ሁሉ ይናፍቀኛል...በቃ ፥ ወናነት እየተሠማኝ ነው ብታይ ይከብዳል"...
"ሌላ ቢኖርልኝ ብለህ የምትመኝው ሰው አለ ?...."
"ነገርኩህ እኮ..."
"እሺ ነገ በተለመደው ሰአት እንገናኝ...መድሃኒትህን መውሰድ እንዳትረሳ..."....ብሎኝ በያዘው ወረቀት መሞነጫጨር ጀመረ።
"በቃ ለዚሁ ነው ይሄ ሁሉ...?"
"አይ ሌሎች ታካሚዎች ውጪ ስላሉና ያንተ ሰአት ስላለቀ ነው...ነገ ካቆምንበት እንቀጥላለን...መድሀኒትህን ውሰድ...."..
"መድሀኒቴ እሷ ናት..ስለ እሷ ጠይቀኝ...ማቋረጥ የማልፈልገው መድሀቴ እሷ ናት...ስለ እሷ ልንገርህ እ...."
"እሺ አንዴ....".....አለኝና ተንቀሳቃሽ ስልኩን አወጣ...ወደ ሆነበት ቁጥር መታና ከጆሮው ለትሞ ማውራት ጀመረ።
"ሄለው ኤፊ በር ላይ ያሉትን ታካሚዎች ለከሰአት ቀጠሮ ስጣቸው....".....ደስ አለኝ...ሌሎቹን ሲያባርር ያተኮረብኝ መሰለኝ....
"መቀጠል እንችላለን.... ".....
"ልጀምር..."...ተንገበገብኩ።
"አዎ..."
"ከምን እንደምጀምር ግራ ገባኝ...."
"ከፈለክበት ጀምር"....አለኝ ፈገግ ብሎ...
"በቃ እሷ ብቻ ናት...በቃ ".....
"እየሰማኹህ ነው...."....አፈጠጠብኝ።
"በቃኝ ይሄን ያህል ካልኩህ ይበቃል"....እንደዛ ስለ እሷ ለማውራት እንዳልቋመጥኩ ገና ከመጀመሬ ውስጤ ተላወሰብኝ...ተበጠበጥኩኝ....እጄ መንቀጥቀጥ ጀመረ...ግንባሬ ላይ ላቤ ችፍፍ አለ....
አኳኃኔን አይቶ መድሀኒት ማዘዣው ላይ የማይነበብ ፅሁፉን ፃፈ....
"መድሀኒት ቤት ሂድ...የበፊቱ መድሀኒት ላይ የሚጨመር ነው ይሄ...የበፊቱ መድሀኒት ከመውሰድህ ከአንድ ሰአት በፊት ይሄን አንድ አንድ ፍሬ ውሰድ....ነገ እንገናኝ።"
"ዶክተር..."
"አቤት...."
"መድሀኒቴ እሷ ነች አልኩህ እኮ...እሷን እዘዝልኝ !....."
" እባክህ ..... "
"ባንድ ሰከንድ ነው የምድነው እመነኝ...."
" እባክህ አንተም እመነኝ ... ሊያ ሞታለች ..... "
" አልሞተችም....ልብ ብለህ እየኝ....እኔ ነኝ የሞትኩት..! " | 231 |
| 17 | No text... | 171 |
| 18 | ልኬቴ ላደርጋት ፡ ሴት ሲባል ፡ ስለ እንስትነት ሲወራ እሷን ማሰብ ይዳዳኝ ጀምሯል ። ሰው ናት ፡ ሴት መኾኗ አይገመቴነቷን ጨምሮላት ያሰብኩትን ቀድማኝ ማድረግ ከጀመረች ከርማለች (እኔ የታወቀኝ አሁን ኾነ እንጂ ) ....
ከ ፫ ዐመት በፊት ስንለያይ ደግመን ልንገናኝ ቀርቶ በውልብታ እንኳ የምታስበኝ አልመሠለኝም ነበር ፤ ባላወኩት የምትለኝ ፤ የእግር እሳቷ .......
ስለ ወንድ ክፋት ሲወራ ፡ ተሞክሮ የምሆናት ነበር የሚመስለኝ ።
እሷ ግን ሰው ናት ፡ ሁሉን ረስታ
እኔን ሳትረሳ እራሴን የምወቅስበት ምክንያቴ ኾነች መሠል ...
ይከነክነኝ ጀምሯል | 196 |
| 19 | ቀጥ ብለህ ቁም!
(አሌክስ አብርሃም)
ጎተራ ኮንዶሚኒየም ስኖር ወጣት ባልና ሚስት ጎረቤቶች ነበሩኝ! በጣም የሚፋቀሩ ! እና ሌሊት ሌሊት አንዳንድ ተቀባይነት የሌላቸው ድምፆች ያለዕቅድ ግድግዳውን አልፈው ይረብሹኝ ነበር! ሌላ ሌላው ነገር ሳይሆን በተለይ ሚስቱ የባሏን ስም በቁልምጫ ስትጠራው "ምናለ ይሄን ለቁልምጫ የማይመች ስም ቢያስቀይረው" እያልኩ በሌሊቱ አስባለሁ! ወይም የብዕር ስም እንደሚባለው የእንትን ...ስም ቢጠቀሙ! ከነገሩ ይልቅ የስሙ ቁልምጫ ነበር በሀፍረት ጆሮየን የሚያግለው! (ለአንባቢወቸ የስነ ልቦናና የስነ ተዋልዶ ስሜት ስል ስሙን እዘለዋለሁ)
አንድ ቀን ድንገት ቤቱን ለቀው ሄዱ! ለአንድ ሳምንት ከደበረኝ በኋላ😀 ሌሎች ባልና ሚስቶች ተከራዮች ገቡ! በተለይ ሚስትየዋ የፆሎት ሰው ነች! ባሏ ስራ ሲሄድ ቤቷን ዘግታ ይሄን አጋንንት ስትለበልበው ነው የምትውለው...ከጎተራ ልቀቅ ...ከሳሪስ ልቀቅ ...ከቦሌ ልቀቅ...ከቡልቡላ ....ስገስፅ ነው የምትውለው! ለወሬ ነጋሪ አንድ አጋንንት አዲሳባ አታስቀርም! ድምጿ ራሱ ጎርናና እና አስፈሪ ከመሆኑ ብዛት እኔ ራሱ ልለቅ ይቃጣኝ ነበር! ፀባችን ከስጋና ደም አይደለም ስትል ሻንጣየን አስቀምጨ ተረጋጋሁ!
እና አንድ ሌሊት ያ ድምፅ አነቃኝ ! መጀመሪያ ሹክሹክታ ነበር በኋላ ግን ድምጿ ጨመረ " በአንተ ላይ በተሰጠኝ ስልጣን አዝሃለሁ... ቀጥ ብለህ ቁም ! የተፈጠርክበትን አላማ ትፈፅም ዘንድ ቀጥ ብለህ ቁም ! ስራህን እስክታከናውን ፀንተህ ቁም! የሚያልፈሰፍስህ መንፈስ አሁን ተመታ! ..."
"አሜን" ይላል ባሏ በሚያሳዝን ድምፅ! ምንድነው ይሄ ቁም የሚባል ነገር ? ብየ እኔም በቀስታ ፀለይኩ "ጌታ ሆይ ምንም ድምፅ የማያሳልፍ ግድግዳ ባለው ቤት ባርከኝ! ልጅህን ክፉ የሚያሳስበውን መንፈስ ከጎተራ ...ወሎ ሰፈር ...ከቦሌ... ከቡልቡላ ...ንቀለው! ከሶስት ወር በኋላ ፆሎቴ ሰመረ እኔን ከጎተራ ነቀለኝ! | 195 |
| 20 | "ዛሬን ነገን የምንገነባበት ጊዜ ነው። ነገ ደግሞ ተስፋ ነው። ትናንት ደግሞ ታሪክ እንጂ ተስፋ አይሆንም። ይህ ሲባል ግን ዛሬ ለምንሰራው ስራ ትናንትም ሆነ ነገ ምንም ዓይነት ጠቃሜታ የላቸውም ማለት አይደለም። ሁሉም የየራሳቸው አስተዋፅኦ አላቸው።
ትናንት ለዛሬ የሚኖረው አስተዋፅኦ ልክ እንደ ትምህርት ቤት ነው። ከትናንት የምንወስዳቸው በርካታ ተሞክሮዎች አሉ። ትናንት የመጣንበት መንገድ ለዛሬ ተሞክሮ ነው። ጠንካራ እና በጎ ጎኖችን የምንወስድበት፣ ድክመቶችን ለይተን ለማረም የምንሰራበት ትልቅ የምርምር ማዕከል ነው።
ነገርግን ትናንትና የምንወስድበት መንገድ የተለያየ ነው። አንዳንዶች ትናንትን በታሪክነቱ ይማሩበታል። ከዚያ በመነሳትም ለነገ ምን መሆን እንዳለበት ያመሳክሩበታል፤ ነገን ሲያቅዱም በግብአትነት ይጠቀሙበታል። ከፊሎቹ ደግሞ ይህንንኑ ትናንት ይቆጩበታል፤ በዚህም ጊዜያቸውን ያባክኑበታል።
በሌላ በኩል ነገ አዲስ የህይወት ምዕራፍ ነው። ስለነገ ዛሬ መተንባይ እንጂ መተግበር አንችልም። እናም ነገን ስናነሳ እንዲህ እሆናለሁ፣ እንዲህ አደርጋለሁ፤ በዚህ መስመር እጓዛለሁ ከማለት ውጭ ተግባራዊ ልናደርግቸ አይችልም። ነገን የተሻለ ለማድረግ ያለን ጊዜ አሁን ነው። የዛሬ እቅዳችንም ሆነ ተግባራችን ዋነኛ ዓላማ ከዛሬው ይልቅ ለነገ ትልቅ ተስፋን የሰነቀ ስለመሆኑ ልናስብ ይገባል።.
ሸጋ ሰንበት ፤ መልካም ውሎ ........... | 272 |
