en
Feedback
ሜላት ተስፋዬ (Melat Tesfaye)

ሜላት ተስፋዬ (Melat Tesfaye)

Open in Telegram

This is an official channel of Melat Tesfaye

Show more
1 297
Subscribers
-124 hours
-197 days
-6230 days
Posts Archive
አትቸኩል! አንዳንዴ ፀጥ ማለት፤ አጎንብሶ ማሳለፍ መልካም ነው፤ ነገ የሚቆጭህን ነገር ከማድረግህ በፊት ትንሽ ጊዜ ውሰድና አስብ፣ ፀልይ። ፈጣሪ ስራውን የሚሰራው በግልፅ አይደለም በስውር ነው። የዘገየ ይመስልሃል ግን የሚቀድመው የለም! ስለዚህ ቸኩለህ አትወስን ብዙ ነገር ታበላሻለህ!

ወሳኝ ፀሎት! ፈጣሪ ሆይ 'መቀየር የማልችላቸውን ነገሮች እንድቀበል እርዳኝ፤ መቀየር የምችላቸውን እንድቀይር ድፍረቱን ስጠኝ ከሁሉ በፊት ግን ሁለቱን መለየት እንድችል ማስተዋሉን ስጠኝ።' እርካታ የሞላው ህይወት ለመኖር ወሳኝ ፀሎት ነው። የሚያረካ ምሽት ተመኘሁ🙏

✅✅ በህይወቴ የሚቆጨኝ ትናንት ከማይሆኑ ሰዎች ጋር ያሳለፍኩት ህይወት ነው። ✅✅ በህይወቴ የሚፀፅተኝ ከኔ ያልተሻሉ ሰዎች ሲንቁኝ ያነባሁት እንባ ነው። ✅✅ በህይወቴ የተደሰትኩበት ትናንትን አልፌ ዛሬ ላይ ያለሁበት ዕለት ነው። 🚺🚹 ስለዚህ ከታገሱት ሁሉም ያልፋል ስለ ነገም አንተ ታውቃለህ ነገ ማለት ተስፋ ነውና በፈጣሪህ #ብቻ ተስፋ አድርግ

የፍቅር ህይወትህን ለማሳካት አንተስ ምን አድርገሀል? ብዙ ሰው እኔኮ ማግባት እፈልጋለው ፤ የፍቅር ጓደኛ ይዤ ጥሩ የፍቅር ግንኙነት መመስረት እፈልጋለው ግን ደግሞ የኔ የተባለዉን ሰው እስከአሁን አላገኘውትም እንደው እኮ ደህና ሰው ጠፋ እንጂ እኔስ እንዴት ጥሩ ባል እንደምሆን ታዩኝ ነበር ይላል ወንድሜ እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ ላንተ የተባለችው ሴት ቀለሟ ምን አይነት ነው ቁመቷስ ምን ያህላል? በምንድነው የምትለያትስ? ደህና ሰው ሆና ያላገኘሀትስ ሴት አንተ ለሷ እንዴት አይነት ሰው ሆነህላታል? እህቴስ ከሱ አላገኘውም ከምትይው በላይ አንቺስ ለሱ የሚገባውን ምን አድርገሽለታል? አንተ በህይወትህ ሙሉ ለተሰጠህ በእጅህ ላለዉ ሰው ልታደርግ የሚገባውን ሙሉ ለሙሉ በቻልከው መጠን ካደረግህ አብሮህ ያለው ባይረዳህ ሙከራህ ሁሉ ባይሳካ እንኳን እመነኝ ከምታስበው በላይ የተሳካ ህይወት እየተዘጋጀልህ ነው የተሰጠህን አክብረሀልና ይገባሀል ያድርግልህ! መልካም ቀን!

ፈልገህ አልተፈጠርክም ማሰብ፣ ማቀድ ሰውኛ ባህሪ ነው። መፈፀም የአምላክህ ነው። አየህ ስኬት እቅድ አሁን የምታስበው በጥቂቱ ነው። እቅድህ የፈጣሪ ፍቃድ ካገኘ አሁን ከምታስበው በላይ እንደሚሆን አትጠራጠር። እናም ወንድሜ ማሰብህን እና ማቀድህን አታቁም አንድ ቀን ከስኬት በላይ ሆኖ ታገኘዋለህ። መልካም አዳር!

ድምፅህን አጥፍተህ ተለወጥ! የራስህን ዋጋ ስታውቀው ዋጋቸውን ያልተረዱ ሰዎች ያሳዝኑሀል፤ አንተ ከልብህ መለወጥ ስትጀምር ሌሎች እንደፈዘዙ ታያለህ፤ መሮጥ ስትጀምር ብዙዎች ቆመው እንደቀሩ ትታዘባለህ። ብትነግራቸው ግን አይሰሙህም፤ ሰዎች ብዙ ርቀት ላልተጓዘ ጆሮ አይሰጡም፤ ለዛ ነው ድምፅህን አጥፈተህ እስከጥግ መለወጥ ያለብህ። መጀመሪያ አንተ ሳትቀየር ሌሎች እንዲቀየሩ አጠብቅ! ለምትወዳቸው የምትደርሰው አንተ ቆራጥ ሆነህ ያመንክበትን ስታሳካ ነው፤ ያኔ ስኬትህ ጮክ ብሎ ይናገራል! የተዓምር ሀሙስ ተመኘሁ🙏

በራስህ እመን! ለራስ አነስተኛ ግምት አትስጥ! ፈጣሪ ለታላቅ አላማ ነው ወደዚህ ምድር ያመጣህ። በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ሆነህ ነገ ከፍታው ላይ እንደምትወጣ ማሰብ እና ማመን ከዛ የምትችለውን ሁሉ ጥረት ማድረግ አለብህ! ሰዎች ባንተ ከማመናቸው በፊት አንተ በራስህ እመን፤ ወዳጄ አሁን ያለህበት ሁኔታ ነገ የምትደርስበትን ትልቅ ቦታ አይወስንም!

ትልቁን ምክንያትክን አዘጋጅ ገና በጠዋት ከእንቅልፍክ ከመነሳትክ ድክም ብሎክ ተኝቼ አይደለም እንዴ ያደርኩት የሚያስብል አጋጣሚ ኖሮክ ያውቃል? እናቶቻችን አባቶቻችንና አያቶቻችን ከኛ ምንም ያክል በእድሜ ከፍ ቢሉም ግን ባላቸው ጉልበትና ብርታት ሁላችንም በጣም እንገረማለን ከየት አመጡት? ሁሉም ቢጠየቁ የሚሰጡት ምላሽ የሚሆነው ትልቅ ምክንያት ስላለኝ ነው የሚል ነው! አንተ አዎ አንተ ልጃቸው ነህ ትልቁ ምክንያታቸው ላንተ ሲሉ ግዴታ መበርታት አለባቸው ስለዚህ አንተም ምክንያት ይኑርክ ትልቅ ምክንያት አዘጋጅ ያኔ በፍፁም መድከም አይፈቀድልክም መልካም ዕለተ ሰንበት 🙏

ሀላፊነቱን ውሰድ! ለውጥ እና መሻሻል የሌለው ህይወት ከመሬት በታች ካረፉ ሰዎች በምንም አይለየንም። ሙት ብቻ ነው የማይለወጠው! እየተነፈስክ ከሆነ ኑሮህ ላይ ብዙ ነገር መቀየርና ተዓምር ሰርተህ ማለፍ አለብህ። ለትልቅ አላማ ተፈጥረህ ትንሽ ህይወት መኖር ላንተ አይመጥንም! ዕድለኛ ካልሆንኩ አያልፍልኝም ማለቱን አቁም! ለውጥ መጀመር የሚፈልግ ሁሉ ስለ ራሱ ህይወት ሀላፊነት ይውሰድ! ከተለወጥኩ በራሴ ጥንካሬ ነው፤ ቆሜ ከቀረውም በራሴ ጥፋት ነው በልና መቀየር የምትችላቸው ነገሮች ላይ ትኩረትህንና ጉልበትህን አሳርፍ። ወዳጄ አንተ ብቻ ቆርጠህ ወደ ተግባር ግባ እንጂ የማይቀየር ነገር የለም! መልካሙን ሁሉ ተመኘንላችሁ🙏

✅ #ከእንቅልፍህ ስትነቃ ተመስገን በል በዛው የቀሩ ስት አሉና ✅ #ከአልጋቹህ ስትነሱ ተመስገን በል ስንት የአልጋ ቁራኛ አለና ✅ #ስትስቁ ተመስገን በል በችግር አንገቱን የደፋ አለና ✅ #ስትራመዱ ተመስገን በሉ መራመድ ያቃታቸው አሉና ✅ #ወዳጄ ሆይ ስትወጣም ስትገባም ተመስገን በል እደወጣህ ባለ መቅረትህ ፈጣሪን አመስግን 🌀 #ቅያሪ ልብስ ካለህ ተመስገን በል ስንት እራቁቱን የሚሄድ አለና 🌀 #ስታወራ ተመስገን በል ስንት ማውራት የማይችሉ አለና 🌀 ስትሰማ ተመስገን በል ስት መልካሙን ነገር ለመስማት የሰው ድምጥ የናፈቃቸው አሉና 🌀 የሞቀ ቤት ውስጥ ላይ በመሆንህ ተመስገን በል ፈጣሪን አመስግን ቤት አተው ጎዳና ላይ ወድቀው የሚያድሩ አሉና 🚹🚺 አይከፍልም ተመስገን ተመስገን እንበል የፈጣሪ ምህረቱ ለዘላለም ነውና!!!