Afri ፈጣን መረጃ
Open in Telegram
እንኳን ደህና መጡ። ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎች በፍጥነት የሚያገኙበት ትክክለኛው የAfri today (Afri ፈጣን መረጃ ) የቴሌግራም ቻናል ነው ። እናመሰግናለን። 📢 ፈጣን ሀገራዊ መረጃዎች 📢 ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 አዝናኝ እና አስተማሪ መረጃዎች 📢 ወቅታዊ ጉዳዮች 📢 ሁሉንም በአንድ የሚያገኙበት ቻናል ነው ።
Show more4 221
Subscribers
-424 hours
-117 days
-3630 days
Posts Archive
4 221
ሰበር‼️ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ሩሲያ የ S-400 የአየር መከላከያ ስርአቶችን ለቱርክ እንዳታስረክብ የማስጠንቀቂያ መልእክት አስተላለፉ።
ይህንንም ተከትሎ ፑቲን በሰጡት ምላሽ ሩሲያ ለማንኛውም አይነት ማስፈራሪያ እጅ አትሰጥም፤ ከማን ጋር ጥረትና ትብብር እንደምናደርግም ማንም ሊወስንልን አይችልም ብለዋል።
Wonde Info
4 221
#ሰበር_መረጃ: ሞሳድ ኤርትራን ማስጠንቀቁ ተሰማ !
በስልታዊው የቀይ ባህር ዳርቻ ላይ የምትገኘው ኤርትራ፣ በሱዳን መደበኛ ጦር (SAF) እና በፈጣን ደጋፊ ኃይሎች (RSF) መካከል እየተካሄደ ያለውን አስከፊ ወታደራዊ ግጭት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በምስራቅ ሱዳን አቅጣጫ ያለውን ተፅዕኖዋን በከፍተኛ ደረጃ ለማስፋፋት እየሰራች መሆኑ ተገለጸ።
ሞሳድ ኮሜንታሪ በኦፊሴላዊ የኤክስ ገጹ እንዳመለከተው፣ ኤርትራ በምስራቅ ሱዳን አቅጣጫ ወታደራዊ ማሰልጠኛዎችን ከማቋቋም አልፋ ከጽንፈኛ ኃይሎች ጋር የቀጥታ ግንኙነት በመፍጠር ቀጠናውን የማወክ ስትራቴጂዋን እየተገበረች መሆኑ ተመልክቷል።
ሞሳድ ኮሜንታሪ ይህን ከማለቱ በፊት ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ኤርትራ የሱዳንን ቀውስ በማባባስ፣ አጋጣሚውን በመጠቀም ተዋጊዎችን በማሰልጠንና በማስታጠቅ ዓይነተኛ ሚና እንደምትጫወት “ዓለም ይወቅልኝ” ስትል ደጋግማ አሁን ድረስ እያስገነዘበች መሆኑ ይታወቃል።
ኤርትራ አሁን ላይ ብረት ያነሱ የኢትዮጵያ አማጺያንን በማሰልጠን፣ ከለላ በመስጠት፣ መሳሪያ በማጓጓዝና በማስታጠቅ የምታደርገውን ተሳትፎ አሳድጋ፣ በገሃድ “ጥምር ጦር” ማደራጀቷ ይታወቃል ሲል አዲስ ሪፖርተር አስነብቧል።
4 221
በድሮን ተደበደብን ሲል ህውሃት መንግስትን ከሰሰ‼
የሕወሃት ባለስልጣናት የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት መቀሌ አቅራቢያ በሚገኝ የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛ ላይ ዛሬ የድሮን ጥቃት ፈጽሟል ሲሉ ከሰሱ።
የሕወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ከላሊ ሃጋዚን ጠቅሶ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት እንደዘገበው፣ ጥቃቱ ከሕወሃትና የፌዴራል መንግስት ውጥረት መጨመር ጋር ተያይዞ በአንድ ሳምንት ውስጥ የተፈጸመ ሁለተኛው የድሮን ጥቃት ነው።
አቶ ከላሊ በጥቃቱ የደረሰ ጉዳት የለም ቢሉም፣ አንድ የአካባቢው ካህን ግን አንድ ታጣቂ መጎዳቱንና ሁለት ሰዎች መቁሰላቸውን ገልጸዋል።
4 221
ማይጨው የሚገኝ ሆስፒታል ለህዝብ መከልከሉ ተገለጸ‼
በማይጨው ከተማ የሚገኘው ለምለም ካርል ጠቅላላ ሆስፒታል ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ለህዝብ የሕክምና አገልግሎት እንዳይሰጥ መደረጉን ከስፍራው የወጡ መረጃዎች አመልክተዋል።በራያ ቆቦ አቅራቢያ በተቀሰቀሰ ተኩስ ጉዳት የደረሰባቸውን ታጣቂዎች ለማከም ሲባል ሆስፒታሉ ለህዝብ እንዲዘጋ መደረጉ ተመልክቷል።
4 221
" ማንኛውንም የጠላት አጥንት እርምጃ ከመጀመሩ በፊት እናደቀዋለን" - ጀነራል አሊሬዛ ሼክ
የኢራኑ ምክትል ጦር አፈጻጸም አስተባባሪ የሆኑት ብርጋዴር ጄነራል አሊሬዛ ሼክ "ማንኛውም የጠላት አቅም እርምጃ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት፣ ከመሠረቱ ይከሽፋል" ብለዋል።
በተጨማሪም ኢራን በመከላከያ እና በወታደራዊ አቅሟ ላይ በመመስረት ማንኛውንም ወታደራዊ ስጋት ለመቋቋም ዝግጁ መሆኗን አክለዋል።
4 221
በብሉ ናይል ግዛት ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ አዲስ ውጊያ መቀስቀሱ ተሰማ‼
📌 ከአንድ ወር በፊት የሱዳን መደበኛ ጦር ስትራቴጂካዊቷን የኩርሙክ ከተማን መቆጣጠሩ ይታወቃል፡፡ በወቅቱ ጦሩ ከተማዋን ሲቆጣጠር የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ (RSF) ታጣቂዎች ወደኋላ አፈግፍገው ነበር፡፡
📌 ሆኖም ዛሬ በወጣ መረጃ፤ በሸረሪናው ውጊያ ተሳትፏል በሚል የተወነጀለው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ በሱዳን ጦር ላይ አዲስ የመልሶ ማጥቃት ከፍቷል፡፡ ይህንንም ተከትሎ በአሁኑ ሰዓት በአካባቢው ከባድ ውጊያ እየተደረገ ይገኛል፡፡
📌 በተጨማሪም በዚህ ቀጠና የሕወሓት የጦር አሃዶች ከአልቡርሃን (የሱዳን ጦር) ጎን ሆነው እንደሚዋጉ ጠቅሶ አንድአፍታ አጋርቷል።
4 221
+1
ኢትዮጵያ የዓለም ኃያላንን ቀልብ እየሳበች ነው‼️ 🇪🇹✈️
የቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ አሜሪካንና ቻይናን ለፉክክር አስገባ‼️
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዘርፍ እያሳየ ያለው ፈጣን እድገትና የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ እና በዓለም ገበያ ያለው እየጨመረ የመጣ ተፈላጊነት፣ የዓለም ኃያላን ሀገራትን ቀልብ እየሳበ ነው።
ከአዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር ገደማ ርቀት ላይ ሊገነባ የታቀደው 12.5 ቢሊዮን ዶላር የቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአንድ ግዙፍ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክት ባለፈ የኢትዮጵያን እያደገ የመጣ ስትራቴጂያዊ ጠቀሜታ የሚያሳይ ፕሮጀክት ሆኗል።
ሳውዝ ቻይና ሞርኒንግ ፖስት እንደዘገበው፣ የቻይና መንግሥታዊ ኩባንያዎች በፕሮጀክቱ የጨረታ ሂደት ጠንካራ ተሳትፎ እያደረጉ ሲሆን፣ በሌላ በኩል አሜሪካም እንደ ቦይንግ እና ጄነራል ኤሌክትሪክ (GE) ያሉ ግዙፍ ኩባንያዎቿ በፕሮጀክቱ እንዲሳተፉ ከፍተኛ ፍላጎት እያሳየች መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የሁለቱ ኃያላን ሀገራት ፍላጎት፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን፣ የንግድና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን እያጠናከረች መምጣቷን የሚያሳይ ነው።
4 221
በራያ አላማጣ የድሮን ጥቃት ተፈጸመ‼
በራያ አላማጣ መረዋ በተባለ ት/ቤት ዛሬ ነሐሴ 4 ቀን ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት የድሮን ጥቃት መፈጸሙ ታውቋል።
📌 የህውሃት ታጣቂዎች ትናንት ምሽት ለየክፍላቸው የጦር መሳሪያ ክፍፍል አድርገው ዛሬ ከመረዋ ት/ቤት ጭነው ለመውሰድ በዝግጅት ላይ እንዳሉ ጥቃቱ መፈፀሙ ተነግሯል።
በታጣቂዎቹ ላይ ጉዳት መድረሱ እና ወደ አላማጣ ሆስፒታል ተሽከርካሪዎች ሲመላለሱ ነበር ተብሏል።በአካባቢው ከፍተኛ የጦርነት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የሚያመለክቱ ተደጋጋሚ መረጃዎች እየወጡነው።
ምስሉ AI ነው።
4 221
⚡ Discover ALEXATOR
Original electronic music created to inspire, motivate and energize.
🌐 alexator.com
Listen & download for free.
📲 t.me/alexator_music
Follow for new music & updates.
▶️ NEW MUSIC VIDEO
ALEXATOR — GENESIS (001)
https://youtu.be/OR2yplPn1AU
4 221
ኢራን የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን ለመክፈት ከባድ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀመጠች‼
የኢራን ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤት አሜሪካ እገዳዋን ሳታነሳ፣ ጦሯን ሳታወጣ፣ የጦርነት ካሳ ሳትከፍል እና የታገዱ ሀብቶችን ሳታስለቅቅ የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ እንደማይከፈት አስታወቀ።
የ60 ቀናት የሽግግር ጊዜ ለማጠናቀቅ አንድ ሳምንት በሰጠበት ወቅት የቀረቡት እነዚህ ጥያቄዎች ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ወደ ወታደራዊ እርምጃ ሊገፋፉ እንደሚችሉ ተንታኞች ገልጸዋል።
የአሜሪካው ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ በበኩላቸው ዋነኛው ትኩረት በባህረ ሰላጤው የተዘረጉ ፈንጂዎችን ማጽዳት መሆኑን ጠቁመው፣ ኢራን ለውጥ ካላደረገች ዋሽንግተን ጫናዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል አስጠንቅቀዋል።
4 221
የፌዴራል መንግሥቱን የጦር ካምፕ ተቆጣጠሩ‼
በሶማሊያ የከፊል ራስ-ገዝ አስተዳደር በሆነችው ፑንትላንድ እና በፌዴራል መንግሥቱ መካከል ያለው ውጥረት ባነሰረበት በዚህ ወቅት፣ የፑንትላንድ ኃይሎች በጋልካዮ በሚገኘው የፌዴራል ጦር ላይ ጥቃት በመሰንዘር በቦሳሶ የሚገኘውን የደህንነት ኃይል (PSF) የጦር ካምፕ መቆጣጠራቸውን አስታወቁ።
የፑንትላንድ ፕሬዚዳንት ሳይድ አብዱላሂ ደኒ በጋሮዌ በሰጡት መግለጫ፣ እርምጃው በክልሉ መንግሥት ላይ ተቃውሞ በሚያነሱ አካላት ላይ መልእክት ለማስተላለፍ የተወሰደ የታቀደ የደህንነት እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። በከባድ መሳሪያዎች የታገዘው ይህ ግጭት የሰው ህይወት ጉዳት ያደረሰ ሲሆን የሲቪሎችን መፈናቀልም አስከትሏል።
4 221
የህንድ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆኑ‼
ኤር ኢንዲየቀድሞውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማሪያምን የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና ማኔጂንግ ዳይሬክተር አድርጎ መሾሙን አስታወቀ።
በፍቃዳቸው ኃላፊነታቸውን የለቀቁትን ካምፕቤል ዊልሰንን የሚተኩት አቶ ተወልደ፣ ከመጪው መስከረም መጨረሻ ጀምሮ ሥራቸውን የሚጀምሩ ሲሆን የአየር መንገዱን የፋይናንስ እና የአሠራር ፈተናዎች የመወጣት ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።
4 221
+2
"ጦርነት እንዲጀመር አልፈልግም፤ ከተጀመረ ግን አሰብ ደርሶ የሚመለስ የኢትዮጵያ ወታደር የለም‼️
አሰብ ብቻም ሳይሆን የኤርትራ ሀገራዊነት ጥያቄ ዉስጥ ይገባል።
ጄኔራል ሳሞራ ዩኑስ
4 221
+2
ሰሜን ኮሪያ ጦርነቱን በሚሳኤል ተቀላቀለች‼
ሩሲያ እና ሰሜን ኮሪያ በምስጢር ሲያዘጋጁት የነበረው አደገኛ ውሳኔ በመጨረሻ ወደ ተግባር ተቀይሯል።
ዛሬ ሌሊት የተተኮሰው ይህ አዲስ እና እጅግ አጥፊ ሚሳይል የብዙዎችን ህይወት በቅጽበት የቀጠፈ ሲሆን፣ የምዕራባውያንን የአየር መከላከያ ስርአት ሙሉ በሙሉ ግራ አጋብቷል።
4 221
ሰበር ዜና በሩሲያ የድሮን ጥቃት የዩክሬን ወታደራዊ የጥገና ማዕከል እና የነዳጅ አቅርቦቶች ተመቱ !
በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል ያለው ግጭት በከፍተኛ ሁኔታ በቀጠለበት በዚህ ሰዓት፣ የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖች በዩክሬን ስልታዊ መሠረተ ልማቶች ላይ ያተኮረ የተቀናጀ ጥቃት ፈጽመዋል።
በደረሰን ዘገባ መሠረት፣ በጥቃቱ የመጀመሪያ ኢላማ የሆነው የዩክሬን ጦር ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን እና የጦር መሳሪያዎችን ይጠግንበት የነበረ ዋና የጥገና ማዕከል ሲሆን፣ ተቋሙ በጥቃቱ ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ ሆኗል።
በተጨማሪም ጥቃቱ በሦስት አበይት ክልሎች ማለትም በሱሚ፣ በካርኪቭ እና በዲኔፕሮፔትሮቭስክ በሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች እና የማከማቻ ዲፖዎች ላይ ያተኮረ ነበር።
ይህ በሦስቱም ክልሎች ላይ የተፈጸመው የተቀናጀ የድሮን ጥቃት፣ የዩክሬን ጦር ግንባር የሎጂስቲክስና የነዳጅ አቅርቦት መስመር ላይ ከፍተኛ ስልታዊ ጫና እንደሚፈጥር ተገምቷል።
4 221
በዓባይ ወንዝ ላይ በሚገነቡ ሁለት የሃይድሮኤሌክትሪክ ግድቦች እንዲሁም በባሮ አኮቦ ወንዝ ላይ ለሚገነባ አንድ የተቀናጀ የኤሌክትሪክ ማመንጫና የመስኖ ግድብ ፕሮጀክት (Multipurpose Dam) ግንባታ ለመሳተፍ የፍላጎት ማሳወቂያ ደብዳቤ (letter of intent) ካስገቡ የታወቁ 17 ኮንትራክተሮች መካከል የተመረጡ 7 ግዙፍ ተቋማት የፋይናንስና ቴክኒካል አቅምን ጨምሮ ዝርዝር ማስረጃ እንዲያቀርቡ ጥሪ እንደቀረበላቸው መረጃ ደርሶናል።
🇪🇹
ኢትዮጵያ የአፍሪካ የለውጥ ተምሳሌት ትሆናለች !!
4 221
"የግብፅ ስጋት የሆነው የኮይሻ ግድብ ወደ መጠጠናቀቅ እየተቃረበ ነው።
የግብፅ ሴራ ያላስቆመው የኢትዮጵያ የቀጠናው የበላይነትና የልማት ጉዞ በብርቱ እየቀጠለ ነው።"
ኢትዮጵያ በራሷ አቅም፣ በልጆቿ ቁርጠኝነት እና በሕዝቧ ድጋፍ የጀመረችውን የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ተጠናቆ 2ኛው ግዙፍ ግድብ #ኮይሻ ወደ ፍጻሜው እያቀረበ ትገኛለች።
ኮይሻ ግድብ የመብራት ምንጭ ብቻ ሳይሆን የሀገሪቱ የቴክኖሎጂ እድገት፣ የምህንድስና ብቃት እና የልማት ራዕይ ምልክት ሆኗል።
ዛሬም በተለያዩ ፈተናዎች መካከልም ኢትዮጵያ የልማት ጉዞዋን ሳታቋርጥ ቀጥላለች።
የህዳሴ ግድብ መጠጠናቀቅ ለሚሊዮኖች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነትን ያሳደገ ሲሆን 2ኛው ኮይሻ ግድብ፤ ለኢንዱስትሪ እድገት መሰረት ይጥላል፤ በቀጠናውም የኃይል ትስስርን ያጠናክራል።
"ግድቦች የኮንክሪት ክምር ብቻ አይደሉም፤ የአንድ ሕዝብ ሕልም፣ ትጋት እና የወደፊት ተስፋ ናቸው።"
ኮይሻ ግድብ የኢትዮጵያ የልማት ጉዞ በፅናት እንደሚቀጥል የሚያሳይ ሕያው ምስክር ነው።
ዛሬ የሚታየው ኮንክሪት ነገ የብርሃን፣ የሥራ እድል እና የኢኮኖሚ እድገት መሰረት ይሆናል። 🇪🇹
ግብፅ ለሁሉም ጠብታ ውሀ ተሰልቶ እንድትከፍለን ይደረግ
የኢትዮጵያ ውሀ ንብረትነቱ የኢትዮጵያ ብቻ ነው::
4 221
+1
የአፍሪካ ቁጥር አንዱ ባለሀብት አሊኮ ዳንጎቴ 33% ሀብቱን ለዘካ ለመስጠት ወስኗል።
ናይጀሪያዊው አሊኮ ሙሀመድ ዳንጎቴ ከአፍሪካ ቁጥር አንድ ባለሀብት ሲሆን በአለማችን ላይ ካሉ ጥቁሮች ሁሉ ቁጥር አንዱ ባለሀብት ነው። 36 ቢሊዮን ዶላር ያለው ዳንጎቴ ከአለምም በሀብት መጠኑ 62ኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ የናጠጠ ባለሀብት ነው።
ሀገራችንን ጨምሮ በበርካታ የአፍሪካ ሀገራትም ቀዳሚ ኢንቨስተር ነው።
ታዲያ የአሊኮ ሙሀመድ ዳንጎቴ ልጅና የዳንጎቴ ኩባንያ ዋና ሀላፊ የሆነቺው ፋጡማ አሊ ሙሀመድ ዳንጎቴ ከብሉምበርግ ጋር ባደረገቺው ቆይታ አባታችን 33% ሀብቱን ለዲሀዎችና ለተረጂዎች ለማዋል ወስኗል ብላለች። ፋጡማ በሰጠቺው ቃለመጠይቅም አባቴ ይሄን የሚያደርገው በኢስላማዊው የዘካ መርህ ነው ብላለች።
ፋጡማ ስለ አባቷ ውሳኔ ስታወራ አባቴ እኔን እህቴን እና እናቱን በዚህ ጉዳይ አስፈርሞናል ሁላችንም የአባቴን ሀሳብ ተስማምተን አንድ ሶስተኛውን ለመስጠት ወስነናል ብላለች።አባቷ ከዚህ በፊትም 25% ሀብቱን ለግብረሰናይ ተግባር እንደለገሰ አስታውቃለች።
ግዙፉን የዳንጎቴ ኩባንያው በዋና ስራ አስፈፃሚነት የምትመራው ልጁ ፋጡማ ዳንጎቴ ነች።
4 221
+2
አሜሪካ ባለ 6ኛ ትውልድ አደገኛ የጦር ጄቷን "F-47" ልታመርት ነው!
የአሜሪካ አየር ኃይል የዓየር ላይ የበላይነቱን ለማስጠበቅ ያለመውን ባለ 6ኛ ትውልድ የጦር ጄት F-47 የማልማት ሥራ በይፋ መጀመሩ ተበሰረ።
በኔክስት ጄኔሬሽን ኤር ዶሚናንስ (NGAD) ፕሮግራም ሥር የሚገነባው ይህ የጦር ጄት፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ወታደራዊ የቴክኖሎጂ የበላይነትን ሙሉ በሙሉ ይይዛል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ እጅግ ዘመናዊ ጄት የላቀ የመሰወር (Stealth) ቴክኖሎጂ፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የሚታገዙ የውጊያ ሥርዓቶች እና በረጅም ርቀት የማጥቃት ብቃት ያለው ነው ተብሏል።
4 221
በሚሳይል ኢንዱስትሪ ውስጥ የኢራን አስደናቂ ስኬት!
ኢራን Paveh የተሰኘ አዲስ ሚሳይል የሙከራ ሂደት እያጠናቀቀች እንደሆነ ተነግሯል።
ከቴህራን ጋር ቅርበት ያላቸው የመረጃ ምንጮች መሰረት ይህ ሚሳይል ባህሪያቱና በሚያደርሰው ከፍተኛ ጉዳት ምክንያት የኢራንን የሚሳኤል አቅምና የደምሳሽነት ብቃትን እጅግ ከፍ ወዳለ ደረጃ የሚያሳድግና ውጤታማነቱ በጦር አውድ እስኪሞከር አጓጊነትን የፈጠረና ለሃገሪቱ ጠላቶች የመርዶ ያህል አስደንጋጭ ሊሆን የሚችል ነው ተብሏል።
በአሜሪካም ስጋት መፈጠሩን ይነገራል።
የተጠቀሱት የPaveh ሚሳይል ባህሪያት፦
የመድረሻ ርቀት፦ 1,650 ኪሎሜትር
ፍጥነት፦ Mach 8 (በሰዓት 10,000 ኪሎሜትር ገደማ)
300 ኪሎግራም የሚመዝን የጦር ራስ (warhead) መሸከም ይችላል።
ከመሬት 50 ጫማ ብቻ ከፍታ በመብረር መጓዝ ይችላል።
ሚሳኢሉ
# በማንኛውም ራዳር አይገኝም ተብሏል።
# በGPS እና በመመሪያ ሥርዓቶች ይመራል።
# የበረራ አቅጣጫውን በራሱ መቀየር ይችላል።
ይህ ሚሳይል እንደ አውሮፕላን ቡድን (squadron) ይሠራል።
16 ሚሳይሎች በአንድ ጊዜ ወደ አንድ ዒላማ ይጓዛሉ። ከእነሱ አንዱ የመሪ ሚና ይጫወታል። የጠላት ሚሳይል ለማጥፋት ቢመጣ፣ ከመሪው ሚሳይል ሌላ ሚሳይል ወደ ፊት እንዲሄድ የሚያስችል የቴክኖሎጂ ንድፍ ተሰርቷል። የጠላት ሚሳይል ያንን ሚሳይል በማጥፋት ሲጠመድ፣ ቀሪዎቹ ሚሳይሎች ዒላማቸውን በትክክል ለመምታት ዕድል ያገኛሉ።
ይህን የቴክኖሎጂ ችሎታ ለመከላከል በዓለም ላይ የሚችል ሀገር እንደሌለ እና ይህ የኢራን ስኬት ጠላቶቿን እጅግ እንዳሳሰበ ይነገራል።
ለማንኛውም የነገን ለማየት ያብቃን
