Afri ፈጣን መረጃ
Open in Telegram
እንኳን ደህና መጡ። ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎች በፍጥነት የሚያገኙበት ትክክለኛው የAfri today (Afri ፈጣን መረጃ ) የቴሌግራም ቻናል ነው ። እናመሰግናለን። 📢 ፈጣን ሀገራዊ መረጃዎች 📢 ዓለም ዓቀፍ መረጃዎች 📢 አዝናኝ እና አስተማሪ መረጃዎች 📢 ወቅታዊ ጉዳዮች 📢 ሁሉንም በአንድ የሚያገኙበት ቻናል ነው ።
Show more4 223
Subscribers
-424 hours
-67 days
-3830 days
Posts Archive
4 223
16 አዳዲስ ግዙፍ መርከቦች በ83.1 ቢሊዮን ብር ሊገዙ ነው‼
የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ለማቀላጠፍ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ውስጥ 83.1 ቢሊዮን ብር በመመደብ 16 አዳዲስ መርከቦችን ለመግዛት ማቀዱን አስታወቀ።
📌የአሁኑ 6 መርከቦች የግዥ ሂደት ቀድሞ የተጀመረ ሲሆን፣ አዳዲሶቹ መርከቦች እያንዳንዳቸው ከ50 ሺህ እስከ 63 ሺህ ቶን የመጫን አቅም ያላቸው (የአሁኖቹን በእጥፍ የሚበልጡ) ግዙፋን ናቸው።
📌 ሀገሪቱ አሁን ካሏት 10 መርከቦች ጋር ሲደመር የባህር ትራንስፖርት አቅሟን በከፍተኛ ደረጃ ያሳድገዋል።
4 223
የመጨረሻው ንግግር _ ''ቀይ ባህር ለእኔ ዘላለማዊ ቤቴ እንዲሆን ወስኛለሁ! ደስተኛ እና እድለኛ ጀነራል ነኝ።''
''የምፅዋው ዳግማዊ ቴዎድሮስ''..ሲሉ ይጠሯቸዋል! ...''የትኛውም ሀገር ያለ በር እና መስኮት አይሰራም ! '' የሚለው የዘወትር ንግግራቸው ከምፅዋ እና ከባህር በር ጋር በተያያዘ የሚሰማቸው ስሜት እንደሆነም ይነገርላቸዋል _ ሀገር ወዳዱ ጀግና ብርጋዴር ጀኔራል ተሾመ!
የብርጋዴር ጀኔራል ተሾመ ተሰማ የመጨረሻዋ መልዕክት-ከምፅዋ
"ሻዕብያ ያለ የሌለ ሃይሉን ተጠቅሞ ምጽዋን ለመያዝ ቆርጦ መነሳቱ ጥርጥር የለውም። እኔ የሚጠበቅብኝን አደራ ተወጥቻለሁ። ከጥር 30 ጀምሮ እስከ የካቲት 9/1982 የሞት ሽረት ትግል አድርጌያለሁ። ከዚህ በኋላ የራሴን ህይወት በክብር ማጥፋትና ለኢትዮጵያ ጀግኖች ታላቅ ተምሳሌት ከመሆን ሌላ አማራጭ የለኝም።
ጀግንነት ማለት በሁሉም መልክ ለጠላት ምቹ ሁኖ አለመገኘት ነው። እኔ ዛሬ ብሞት ብሸነፍም በታሪክና በመጭው የኢትዮጵያ ትውልድ ፊት አልሸነፍም። የአጼ ቴወድሮስን እድል በማግኘቴ በጣም እኮራለሁ።
ጎበዝ ስሙኝ! ይህ የአደራ መልክቴ ነው። ነገ ለኢትዮጵያ ህዝብ ይደርስ ይሆናል። ምን አልባት አምላክ ካለ ከእናንተ አንዱ መልዕክቴን ያደርስልኛል።
ዛሬ ሻብያ ምጽዋን ይቆጣጠራል ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያ ሀገሬ እና ህዝቧ ትልቅ አደጋ ነው ምናልባትም የኢትዮጵያ የተፈጥሮ ደንበር የሆነውንና ለዘመናት በአባቶቻችን የደም ዋጋ ጸንቶ የቆየውን የባህር በራችንን በመዝጋት በምድር ተወስነን እንድንቆይ ይደረግ ይሆናል። ይህ ደግሞ የሞት ሞት ነው።
4 223
ሶማሊላንድ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ አምባሳደሯን ሾመች !
🌍
የሶማሊላንድ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት አብዱራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ በኢትዮጵያ የሶማሊላንድ ኢምባሲ አምባሳደር እና ምክትል አምባሳደር ሹመት ሰጥተዋል።
ሻርማርኬ ጌሌ በኢትዮጵያ የሶማሊላንድ ኢምባሲ አምባሳደር ሆነው ሲሾሙ ሞሐመድ አብዲ አብዲላሂ ደግሞ ምክትል አምባሳደር ሆነው በፕሬዝዳንት አብዱራህማን ተሹመዋል።
ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ በሁለንተናዊ መልኩ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን በጽኑ መሰረት ላይ ለመገንባት በመስራት ላይ ይገኛሉ።
4 223
ሰበር መረጃ‼️
"ጦርነቱ ከተጀመረ የኤርትራ ጄኔራሎች ይደመሰሳሉ" ኮሎኔል ነጋሽ
ጦርነት ከተቀሰቀሰ የኤርትራ ጄኔራሎችና አመራሮች ሙሉ በሙሉ እንደሚደመሰሱና ኤርትራም በአጭር ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ ቁጥጥር ሥር እንደምትገባ ኮሎኔል ነጋሽ ገለጹ።
የኢትዮጵያ የመጀመሪያ ፍላጎት ሰላም መሆኑንና የገለጹት ኮሎኔል ነጋሽ፣ ነገር ግን ሀገርን የሚያፈርሱና የሚያበጣብጡ ኃይሎችን ዝም ብለን እንደማይመለከቱና ባሉበት ቦታ ድረስ በመሄድ ተገቢውን ዋጋ እንደሚያስከፍሉ አስጠንቅቀዋል።
አሁን ያለው የጦርነት አውድ ሙሉ በሙሉ መቀየሩን የጠቆሙት ኮሎኔሉ፣ ለውጊያ ከፍተኛ የሰው ኃይል ማሰለፍ ሳያስፈልግ በአንድ ቦታ ላይ በመቀመጥ ጦርነቱን ማጠናቀቅ የሚቻልበት ዘመናዊ የሥልትና የቴክኖሎጂ ደረጃ ላይ መደረሱን አብራርተዋል።
4 223
+2
በኤርትራ በኩል ለሁቲዎች የጦር መሳሪያ ይተላለፋል ተባለ‼
የመካከለኛው ምስራቅ የውጥረት ፖለቲካ ወደ አፍሪካ ቀንድ እየተሸጋገረ ባለበት በዚህ ወቅት፣ በኤርትራ ምድር ከፍተኛ ቁጥር ያለው የጦር መሳሪያ እየተራገፈ መሆኑን መረጃዎች ጠቁመዋል።
በአሜሪካ የሚገኘው የጥናት ማዕከል «ሴንቸሪ ፋውንዴሽን» ይፋ ባደረገው ጥናት እንደገለጸው፣ ኢራን ቀይ ባህርን አቋርጣ ለየመን ሁቲዎች የምትልከውን የጦር መሳሪያ በቀጥታ ከመላክ ይልቅ አቅጣጫውን ወደ ኤርትራ ዳህላክ ደሴቶች በመቀየር በዚያ አቆይታ ወደ ታጣቂዎቹ ግዛት ታጓጉዛለች።
ይህ መረጃ ከተረጋገጠ ኤርትራ በአሜሪካና እስራኤል ጥርስ ውስጥ እንድትገባ የሚያደርጋት ሲሆን፣ ተጨማሪ ማዕቀቦችንም ሊያስከትልባት ይችላል።
በጉዳዩ ላይ ከኤርትራ በኩል ጥብቅ ማስተባበያ የተሰጠ ቢሆንም፣ የሁቲ ታጣቂዎች እንቅስቃሴያቸውን ወደ አፍሪካ ቀንድ እያሰፉ መሆናቸው ስጋት ፈጥሯል።
4 223
#ሰበር_ዜና ኢራን አዲስ "አስገራሚ" የጦር መሳሪያዎች በጦር ሜዳው ላይ እንደሚገለጡ ተናገረች
የኢራን የመከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል ሬዛ ታላይ-ኒክ እንዳሉት ኢራን በዋና ዋና ድሮኖች እና በባሊስቲክ ሚሳኤል ቴክኖሎጂዎች ከመቅዳት እና ከተገላቢጦሽ ምህንድስና አልፋለች።
ኢራን ከአገር ውስጥ ተመሳሳይ መሳሪያዎች እስከ 20 እጥፍ የሚበልጥ ዋጋ ያላቸውን የጦር መሳሪያዎች እያመረተች እንደሆነም ተናግረዋል።
4 223
ጄኔራሉ ከህውሃት አምልጠው አዲስ አበባ ገቡ‼
በትግራይ ክልል ያለውን ውጥረት እና የርስ በርስ ፍጥጫ ተከትሎ፣ ሜጀር ጄኔራል ተክለብርሃን ወልደአረጋይ (ጄኔራል ሳንቲም) "ወደ አዲስ ጦርነት መግባት አልፈልግም" በሚል ጠንካራ አቋም ከህውሃት አምልጠው ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸው ታውቋል።
ይህ የጄኔራሉ ውሳኔ ችግሮችን በሚሊታንትነት ሳይሆን በምክንያታዊነት እና በተቋማዊ አሰራር ለመፍታት ካላቸው ጽኑ እምነት የመነጨ መሆኑን ተንታኞች ገልጸዋል። እርምጃቸውም በክልሉ ውስጥ ለሚታየው የጦርነት ቅስቀሳ ግልጽ የተቃውሞ መልዕክት አድርገው ታዛቢዎች ወስደውታል።
4 223
+2
የግብፅ ፖለቲከኞች መንግሰታቸውን እየተቃወሙ ነው…🇪🇹🙏
ኢትዮዽያ በአባይ ወንዟ ላይ ተጨማሪ 3ት ግድቦች ልትገነባ መሆኑን የሰሙት የግብፅ ፖለቲከኞች በንዴት የሚይዙት የሚጨብጡት አጥተዋል። ፖለቲከኞቹ መንግስታችን አባይ ግድብ ዙሪያ በኢትዮዽያ የተወሰደባቸው የፖለቲካ በላይነት ነው ኢትዮዽያ አባይ ወንዝ ላይ ተጨማሪ ግድቦችን ለመገደብ ያሰቡት በማለት እያሉ እየደነፉ ይገኛሉ። ውሻ ይጮሀል ግመሉ ጉዞውን ቀጥልዋል።
እኛ ኢትዮዽያውያን ደስ ብሎናል ለኛ ይህ ግድብ ብቻ አይደለም በግፍ የተወሰደብንን የባህር በር የምናስመልስበት አቋራጭ መንገድ ነው 🇪🇹💪
4 223
+1
ሰበር_ዜና: ሩስያ በዩክሬን ላይ ከባድ የአየር ጥቃት ፈፀመች !
ሩስያ በፈፀመችው ሰፊ የአየር ድብደባ፤ የዩክሬን 7 ክልሎች ከባድ ጥቃት የተፈጸመባቸው መሆኑ ተገለፀ።
የሩሲያ ጦር በዩክሬን የተለያዩ ግዛቶች በሚገኙ የመኖሪያ አካባቢዎች፣ የንግድ ተቋማት እና የሲቪል መሰረተ ልማቶች ላይ ያተኮረ መጠነ ሰፊ ጥቃት ማካሄዱን ቀጥላለች።
ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተሰነዘሩት በእነዚህ ጥቃቶች በርካታ ሰዎች ህይወታቸውን ሲያጡ፣ ከፍተኛ የንብረት ውድመት መድረሱ ታስኒም ዘግቧል።
ጥቃቱ ኬቭን ጨምሮ እንደ ሱሚ፣ ኬርሰን እና ካርኪቭ የመሳሰሉ የዩክሬን ግዛቶች ከፍተኛ ውድመት እንደደረሰባቸው ተገልጿል፡፡
4 223
+3
#ሰበር_ዜና: ቭላድሚር ፑቲን በዩክሬን ላይ፣ የኑክሌር ጥቃት ሊሰነዝሩ የተቃረቡ መሆኑ ተዘገበ !
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን "ከዩክሬን ጋር የሚደረገው የሰላም ድርድር መጨረሻ የሌለው ድቅድቅ መንገድ ውስጥ ገብቷል" የሚል ድምዳሜ ላይ መድረሳቸውን ተከተሎ፣ ጦርነቱን በከፍተኛ ሁኔታ ለማፋፋም እና ምናልባትም ታክቲካል የኑክሌር መሳሪያዎችን ለመጠቀም እየተዘጋጁ እንደሆነ የብሉምበርግ አዲስ ዘገባ አመለከተ።
ከክሬምሊን ጋር ቅርበት ያላቸውን ምንጮች የጠቀሰው ይህ ዘገባ እንደሚያስረዳው፣ ሞስኮ አሁን ባለው ሁኔታ የሰላም ንግግሮች ሙሉ በሙሉ መክሸፋቸውን በማመኗ በዩክሬን መዲና ኪየቭ እና በሌሎች ዋና ዋና ከተሞች የኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚሰነዘሩ የባሊስቲክ ሚሳኤል ጥቃቶችን በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ አቅዳለች።
በምዕራባውያን የተጣሉ የኢኮኖሚ ማዕቀፎች እና የዩክሬን ድሮኖች በሩሲያ የነዳጅ ማጣሪያዎች ላይ ያደረሱት ጥቃት ፑቲን ከወታደራዊ ግባቸው እንዲያጎበድዱ ያላደረጋቸው ሲሆን፣ ከባድ ወታደራዊ እርምጃዎች ውጤት ካላመጡ ከመጨረሻ አማራጭነት ታክቲካል የኑክሌር መሳሪያዎችን ሊጠቀሙ ይችላሉ የሚል ስጋት በሩሲያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ዘንድ እየጨመረ መጥቷል።
ሆኖም ይህ ዘገባ ይፋ ቢሆንም እስካሁን ድረስ ሩሲያ የኑክሌር ጥቃት ለማድረስ በተግባር ዝግጅት እያደረገች መሆኗን የሚያሳይ ምንም አይነት ወታደራዊ እንቅስቃሴ ወይም የእንቅስቃሴ ምልክት አልታየም።
የደህንነት ተንታኞችም ቢሆኑ ሞስኮ አሁንም ቢሆን የኑክሌር መሳሪያዎችን የመጠቀም እድሏ አነስተኛ እንደሆነ እና አሁንም ይፋ የሚደረጉ መረጃዎች ምዕራባውያን ለዩክሬን የሚያደርጉትን ወታደራዊ ድጋፍ ለማስቆም የሚደረጉ የማስፈራሪያ ስልቶች እንደሆኑ ይገልጻሉ።
4 223
+1
ዩናይትድ ኪንግደም የ«ስቶርም ሻዶው» ሚሳኤል ማምረቻ ቴክኖሎጂን ለዩክሬን አሳልፋ ለመስጠት ወሰነች
የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር አንዲ በርንሃም፣ ዩክሬን በራሷ ሀገር ውስጥ የረጅም ርቀት «ስቶርም ሻዶው» (Storm Shadow) ክሩዝ ሚሳኤሎችን ለማምረት የሚያስችላትን የቴክኖሎጂ ሽግግር ጥያቄ ማጽደቃቸውን አስታውቀዋል።
4 223
+3
የመገጭ ግድብ ግንባታ 94% ደረሰ‼
በጎንደር ከተማ አቅራቢያ የሚገነባው የመገጭ ግድብ ግንባታ 94 በመቶ በመድረስ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ መሸጋገሩን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አስታወቀ።
በተደረገው ከፍተኛ ርብርብና የተቋራጭ ለውጥ በፍጥነት እየተከናወነ የሚገኘው ይህ ግድብ፣ እስካሁን 33 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ የያዘ ሲሆን የሲቪልና የውሃ ማስተንፈሻ (Spillway) ስራዎቹ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል።የኤሌክትሮ መካኒካል ገጠማ ስራውም በሂደት ላይ ይገኛል ነው የተባለው።
4 223
+2
የመገጭ ግድብ ግንባታ 94% ደረሰ‼
በጎንደር ከተማ አቅራቢያ የሚገነባው የመገጭ ግድብ ግንባታ 94 በመቶ በመድረስ ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ መሸጋገሩን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አስታወቀ።
በተደረገው ከፍተኛ ርብርብና የተቋራጭ ለውጥ በፍጥነት እየተከናወነ የሚገኘው ይህ ግድብ፣ እስካሁን 33 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ የያዘ ሲሆን የሲቪልና የውሃ ማስተንፈሻ (Spillway) ስራዎቹ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል።የኤሌክትሮ መካኒካል ገጠማ ስራውም በሂደት ላይ ይገኛል ነው የተባለው።
4 223
አዲስ የድሮን ጥቃት‼
ዛሬ ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም በህውሃት ወታደራዊ ስምሪት ቦታወች የድሮን ጥቃቶች መፈፀማቸውን የደረሱኝ መረጃዎች ያመለክታሉ።
📌 ራያ አዘቦ ወረዳ ገነቴ ጣቢያ አንድ መድፍ: አንድ ታንክ ከተለያዩ የመድፍና የታንክ ተተኳሾች
📌በሰሜን ምዕራብ ትግራይ እንዳባጉና ከተማ አቅራቢያ በህውሃት አርሚ 11 ወታደራዊ መጋዘን ላይ የድን ጥቃቶች መፈፀማቸው ታውቋል።
4 223
+1
ኢራን የመካ መከላከያ ጥምረትን እንዲትቀላቀል መጋበዟ ተዘገበ።
ኢስላማዊት ሪፐብሊክ ኢራን ከቱርክ ፣ ሳኡዲ አረቢያ እና ፓኪስታን የመካ መከላከያ ጥምረትን እንዲትቀላቀል ጥሪ ቀርቦላታል። ጄሩሳሌም ፖስት የአልመያድን መረጃ ይዞ እንደዘገበው ኢራን የቀረበላትን የጦምረቱን ግብዣ እያጤነቺው ትገኛለች።
የኢራን ባለስልጣናት ለአልመያዲን እንደገለፁት ጥምረቱ የመቀላቀል ግብዣውን ተቀብለዋል። ይሁንና ኢራንም ሆነች ሶስቱ ሀገራት በጉዳዩ ላይ ኦፊሴላዊ መግለጫ አልሰጡም።
ከኢራን በተጨማሪ ግብፅ እና ኳታር ጥምረቱን በፍጥነት ይቀላቀላሉ ተብለው የታሰቡ ሀገራት ናቸው።
ኢራን ጥምረቱን የምትቀላቀል ከሆነ በቀጠናው ያለው የሀይል አሰላለፍ አዲስ መልክና ሚዛን የሚኖረው ይሆናል።
4 223
+2
ለአምባሳደር ጄኔራል ባጫ ደበሌ የክብር አሸኛኘት ተከናወነ‼️
🇰🇪 የስራ ጊዜያቸውንን አጠናቅቀው ለሚመለሱት የኢፌዲሪ የናይሮቢ ሚሲዮን መሪ ክቡር አምባሳደር ጄኔራል ባጫ ደበሌ የክብር አሸኛኘት ተከናወነ፤
በኬንያ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የናይሮቢ ቢሮ (UNON)፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአካባቢ ጥበቃ ፕሮግራም (UNEP) እንዲሁም በ UN-HABITAT የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ በመሆን ሲያገለግሉ ለቆዩት ክቡር አምባሳደር ጄኔራል ባጫ ደበሌ ቡታ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በናይሮቢ የኢፌዲሪ ኤምባሲ ቅጥር ግቢ ደማቅ የሽኝት መርሃ-ግብር ተከናወነ።
4 223
የኔቶ ኃይሎች በባልቲክ ባህር የአየር መከላከያ ቅኝት አጠናከሩ‼️
ከምስራቅ አውሮፓ የሚቃጣውን የድሮንና የሚሳይል ስጋት ለመመከት የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) አባል ሀገራት በባልቲክ አካባቢ አዳዲስ የቅድመ-ማስጠንቀቂያ የራዳር አውሮፕላኖችን ማሰማራታቸውን ገለጹ።
ዘ ጃፓን ታይምስ እና ሮይተርስ እንደዘገቡት፣ እርምጃው የአየር ክልል ጥበቃን ይበልጥ ያጠናክራል።
ይህ በባልቲክ ባህር የተደረገው የኔቶ የቅኝት አውሮፕላኖች ስምሪት በምስራቃዊ የአሊያንስ ድንበር አቅራቢያ ሊከሰቱ የሚችሉ የአየር ክልል ጥሰቶችን አስቀድሞ ለማክሸፍ የተዘረጋ ዘመናዊ የደህንነት መዋቅር ነው።
4 223
በአፋር አንድ አባባል አለ ‘’ወፍ አመት የገነባችውን ቤት ግመል በአንዴ ይጎርሳል’’ ይባላል
እናም ወያኔ ለሁለት አመት ወርቁ ሳይቀር የከበሩድንጋዮች ሳይቀር ለግብፅና ለኤርትራ ሰጥታ በ167 ሚልዮን ዶላር የገነባችው ‘’ራዳር’’ ጀግናው አየር ሃይላችን በአንድ ቀን ወደ አመድነት ቀየረው።
ወያኔ በአሁን ሰአት ከፍተኛ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ የገቡ ሲሆን ግማሹ እጅ እንስጥ ይላል ግማሹ እንደራደር እያሉ ይገኛሉ።
4 223
ሰበር‼️ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ሩሲያ የ S-400 የአየር መከላከያ ስርአቶችን ለቱርክ እንዳታስረክብ የማስጠንቀቂያ መልእክት አስተላለፉ።
ይህንንም ተከትሎ ፑቲን በሰጡት ምላሽ ሩሲያ ለማንኛውም አይነት ማስፈራሪያ እጅ አትሰጥም፤ ከማን ጋር ጥረትና ትብብር እንደምናደርግም ማንም ሊወስንልን አይችልም ብለዋል።
Wonde Info
4 223
#ሰበር_መረጃ: ሞሳድ ኤርትራን ማስጠንቀቁ ተሰማ !
በስልታዊው የቀይ ባህር ዳርቻ ላይ የምትገኘው ኤርትራ፣ በሱዳን መደበኛ ጦር (SAF) እና በፈጣን ደጋፊ ኃይሎች (RSF) መካከል እየተካሄደ ያለውን አስከፊ ወታደራዊ ግጭት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በምስራቅ ሱዳን አቅጣጫ ያለውን ተፅዕኖዋን በከፍተኛ ደረጃ ለማስፋፋት እየሰራች መሆኑ ተገለጸ።
ሞሳድ ኮሜንታሪ በኦፊሴላዊ የኤክስ ገጹ እንዳመለከተው፣ ኤርትራ በምስራቅ ሱዳን አቅጣጫ ወታደራዊ ማሰልጠኛዎችን ከማቋቋም አልፋ ከጽንፈኛ ኃይሎች ጋር የቀጥታ ግንኙነት በመፍጠር ቀጠናውን የማወክ ስትራቴጂዋን እየተገበረች መሆኑ ተመልክቷል።
ሞሳድ ኮሜንታሪ ይህን ከማለቱ በፊት ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ኤርትራ የሱዳንን ቀውስ በማባባስ፣ አጋጣሚውን በመጠቀም ተዋጊዎችን በማሰልጠንና በማስታጠቅ ዓይነተኛ ሚና እንደምትጫወት “ዓለም ይወቅልኝ” ስትል ደጋግማ አሁን ድረስ እያስገነዘበች መሆኑ ይታወቃል።
ኤርትራ አሁን ላይ ብረት ያነሱ የኢትዮጵያ አማጺያንን በማሰልጠን፣ ከለላ በመስጠት፣ መሳሪያ በማጓጓዝና በማስታጠቅ የምታደርገውን ተሳትፎ አሳድጋ፣ በገሃድ “ጥምር ጦር” ማደራጀቷ ይታወቃል ሲል አዲስ ሪፖርተር አስነብቧል።
