en
Feedback
ቃለ:ጥበብ

ቃለ:ጥበብ

Open in Telegram

ድብርት፣ፍርሀት በመጥፎ መሸበብ ፈፅሞ አይኖሩም ካለ ቃለ ጥበብ😊

Show more
329
Subscribers
-124 hours
+47 days
+2230 days
Posts Archive
ኑሮ ሲሆን ተዓምር ህይወት ስትሆን ዳገት ከለታት አንድ ቀን ፣ አንዲት ወፍ እና አሳ ተወደዱ ድንገት ። ወፎች ባህር ወርደው አይቀዝፉ አይዋኙ አሶች ከውሀ ወጥተው ከዛፍ ላይ አይተኙ እኚ ሁለት ነፍሶች ፣ በምን ይዋሀዱ በምን ይገናኙ ። እንዲህ ነው አንዳንዴ ፣ መኖር በሰቀቀን በከንቱ ዕድሜ መፍጀት የማያገኙትን እያሰቡ መጃጀት ። (እዮብ ዘ ማርያም)

አ .ል .ወ .ድ .ሽ .ም .እ .ን.ጂ አልወድሽም እንጂ እኔ ከወደድኩሽ ያዩሽም አይኖሩ ይቅርና የነኩሽ:: አልወድሽም እንጂ ከወደድኩሽማ አደባባይ ቆሜ ከመሃል ከተማ በጂጉ በሚልቅ ከወፎቹ ዜማ አዜምልሽ ነበር ህዝብ ሁሉ እንዲሰማ:: ያው እንደነገርኩሽ አልወድሽም እንጂ እኔ ከወደድኩሽ ፅሀይ ትቆማለች ጨርቃም አትወጣም ነፋሱም ፅጥ ይላል ብርዱም አይበረታም:: ወንዞችም አይፈሱም ቆመው ይሰማሉ የፍቅራቸው ነገር ዕፁብ ነው እያሉ:: ከፍቅራችን በላይ እጅግ የሚገርመው እኛ ስንጎዳ ህዝቡን ነው የሚያመው:: አልወድሽም እንጂ ! አልወድሽም እንጂ ! እኔ ከወደድኩሽ ያው እንደነገርኩሽ አመት አንድ ቀን ነው በፊትሽ በፊቴ ምድርም አንድ እርምጃ ላንቺ ና ኔ ኮቴ:: እኔማ ስወድሽ ሰማይ ትጠባለች በፍቅራችን ደስታ እኛ ከፈለግን ቀን ይሆናል ማታ:: እምልልሻለሁ "አልወድሽም እንጂ ከወደድኩሽ ብዬ" ደስ አሰኝሻለሁ ሰጎንን ቀድሜ አንበሳን ታግዬ:: እኔ ከወደድኩሽ እየተራመድን ነፋስ እንቀድማለን እየተናገርን ዓለት እንሰብራለን ከደመና መሃል ደመና እንፈጥራለን :: አትጠራጠሪ አልወድሽም እንጂ የወደድኩሽ ዕለት ብረት እና ሳት ነን አንቺ ና ኔ ማለት:: እሳት ና ብረት ግጥም እና ዜማ ንጉስ እና ንግስት እግር እና ጫማ አንድ መሆን ታውቂያለሽ አንድ መልክ አንድ ቀለም እኔ አንችን ስወድሽ የሚመስለን የለም:: ግን እኔ ከማልኩልሽ በሚበልጥ መሃላ ከምድራዊው ፍቅር ባይደለ በሌላ አለት በሆነ ልብ በማይጎድል ተስፋ በማይናድ ፅናት ቅፅበት በማይጠፋ በውበትሽ ሰክረው ቅኔ እየዘረፉ በነበልባል ፍቅርሽ ነደው እየጠፉ የሚወዱሽ አሉ እኔ ከወደድኩሽ ታዲያ እነዚህ ሰዎች ምንድን ይሆናሉ።       ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲                   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

እንኳን አደረሳችሁ ለመስቀል የደመራ በዐል 🥳 🎉

📜የእለቱ ጥቅስ ህይወት:- ፍቅርን ታስተምርሃለች ጊዜ:- ማንን ማፍቀር እንዳለብህ ታስተምርሃለች  ሁኔታዎች:- ደግሞ ማን እንደሚያፈቅርህ ያስተምሩሃል። 👉ባለፈ ነገር #ተማር እንጂ ተፀፅተህ አትለፈው 🌿❤️‍🩹

እንቁላል ተቦክቶ ጡብ እንዳልተሰራ ከጭቃ ተላፍቶ እንዳልሆነ ጋራ ዛሬ ሰው ቢቀምሰው ዋጋው ነካ ጣራ #ዜራክ

ስማኝ ልጄ!!!!!!! 1. ጠንካራ ሰው ሁን ማለት አትውደቅ ማለት አይደለም ወድቀህ መነሳትንም ልመድ ማለት እንጂ!!!! 2. ዝም በል ማለት አትናገር ማለት አይደለም ሌሎችን ለመስማት ጆሮ ስጥ ማለት እንጂ!!!! 3. ሆዳም አትሁን ማለት አትብላ ማለት አይደለም በሰው ሀቅ አትለፍ ማለት እንጂ!!!! 4. አትቆጣ ማለት ስሜት አይኑርህ ማለት አይደለም ከቁጣ ቶሎ ተመለስ ማለት እንጂ!!!! 5. ይቅርታ አድርግ ማለት አልተጎዳህም ማለት አይደለም በሆድህ ቂም መያዝ ሌላ ጉዳት ስለሆነ እንጂ!!!! 6. ጠላትህን ውደድ ማለት ጠላት ጥሩ ነው ማለት አይደለም ከጥላቻ ይልቅ ፍቅር ስለሚያሸንፍ!!! 7. ደስተኛ ሁን ማለት ሁሉ ይኑርህ ማለት አይደለም ባለህ ነገር ደስ ይበልህ ማለት እንጂ!!!! 8. ስራህን ውደድ ማለት የምትሰራው ስራ ጥሩ ነው ማለት አይደለም ነገ ጥሩ ስራ እንዲኖርህ ዛሬ የምትሰራውን ስራ ውደድ ማለት እንጂ!!!! 9. ወረኛ አትሁን ማለት አታውራ ማለት አይደለም ምንም ስለማታውቀው ነገር አታውራ ማለት እንጂ!!!! 10. ትሞታለህ ማለት አትስራ ማለት አይደለም ምንም ቁም ነገር ስትሰራ አትሙት ማለት እንጂ!!!! 11. ብቸኛ አትሁን ማለት ሮጠህ ትዳር ያዝ ማለት አይደለም ልብህን ግዜህን ያለህን ሁሉ አሳልፈ ለመስጠት ዝግጁ ሁን ማለት እንጂ!!!! 12. እውነተኛ ሁን ማለት ሰዎች ባሉበት ብቻ እውነትተናገር ማለት አይደለም ለራስህም የእውነት ኑሮ ኑር ማለት ማለት እንጂ!!!! 13. አትጣላ ማለት ከሰው ጋር አትኑር ማለት አይደለም ቂም ይዘህ አትቆይ ማለት እንጂ!!!! 14. ኩራተኛ አትሁን ማለት አትዘንጥ ማለት አይደለም ሌሎችን አትናቅ ማለት እንጂ!!! 15. ቆንጆ ነህ ማለት ከሌሎች የተሻልክህ ነህ ማለት አይደለም አምሮብሃል ማለት እንጂ!!!! 16. አዋቂ ሁን ማለት እንደገና ት/ቤት ሂድ ማለት አይደለም ብልህ ሁን ማለት እንጂ!!!! #የማረ_የሸበረቀ_ቀን_ይሁንላችሁ 😇😊😇

ወፈፌ ቀን አልፎ እብድ ቀን ሲመጣ ሰይጣን ፀበል ገብቶ ሰው ከሰይጣን ወጣ # ማስረሻ

የልብህን ቁስል ትተው የደረትህን ንቅሳት ያደንቃሉ፤ የጭንቅላትህን ዋጋ በኮፍያህ ይተምኑልሃል፤ ጫማ ከሌለህ እግርህ አይታይም፤ መከራ ተሸክሞ ሲኖር ያላዩትን ትከሻ ኮት ሲለብስ ያጨበጭቡለታል፤ ታሪክህን ጨርቅህ ላይ... ስምህን ልብስህ ላይ ለማንበብ ይሽቀዳደማል።

እኔ ላጠና ስል🤓😝👍 :✍ #እኔ ላጠና ስል📝 እኔ ላጠና ስል   እስኪብርቶ ያልቃል🖊 እኔ ላጠና ስል   እንቅልፌ ይመጣል 🙇‍♀🙇‍♀ እኔ ላጠና ስል   ምሳ ሰአት ይደርሳል🍨🍔🍛 እኔ ላጠና ስል   ሆዴን ይቆርጠኛል🤑😤😩 እኔ ላጠና ስል   እራሴን ያመኛል😱😱 እኔ ላጠና ስል   ያቁነጠንጠኛል🤓🤗😳 እኔ ላጠና ስል   መብራቱ ይጠፋል🙊🙊 እኔ ላጠና ስል   ላይብረሪ ይዘጋል🤦‍♀🤦‍♀🤦‍♀ እኔ ላጠና ስል   ብጥብጥ ይነሳል💃💃💃 እኔ ላጠና ስል   ዶርም ይንጫጬብኛል😔🙈 እኔ ላጠና ስል   አዲስ ፊልም ይወጣል👀??🎬 እኔ ላጠና ስል   ስልኬ ይደወላል📞📞 እኔ ላጠና ስል   ወክ እናርግ ይሉኛል🚶‍♀👭 እኔ ላጠና ስል ጋባዥ አገኝና እንውጣ ይሉኛል👩‍❤️‍💋‍👩🍩🍷 እኔ ላጠና ስል   Wifi ይሞላል📡📡 እኔ ላጠና ስል ቀኑ እራሱ ያጥራል 😜😜 እኔ ላጠና ስል   ቴሌግራም ያምረኛል💬💬 እኔ ላጠና ስል   አይኔን ይበላኛል👁👁 እኔ ላጠና ስል   ሙቀቱ ያሳብዳል🙆🤦‍♀ እኔ ላጠና ስል   ውሀው ይመጣና መታጠብ ያምረኛል👳‍♀👳‍♀ ታጥቤ አረፍ ስል እንቅልፍ ይወስደኛል🙇‍♀🙇‍♀💆 እኔ ላጠና ስል   መጫወት ያምረኛል🎡⚽️🤼‍♀ እኔ ላጠና ስል   በሀሳቤ መሀል ግጥም ይወለዳል📖📖 እኔ ላጠና ስል   ደም ግፊቴ ይነሳል😜😞😏 ይሄን ሳብሰለስል ይሄንን ልብ ስል ሳነሳና ስጥል ጊዜው ይሮጠዋል🕚🕣 ላጠና ስል እያልኩ finalu ይደርሳል📆🗓 እናም ይጨንቀኛል ደሞ ልተኛ ስል በህልሞቼ መሀል f(x) ይታየኛል📈 ላጠና ስል ደሞ ይህ ሁሉ ይሆናል ቆይ ምን ይሻለኛል🤷‍♀🤷‍♀ ባቆም ደስ ይለኛል 👌 እዚ ከምነቅል ብነግድ ይሻላል👩‍🎤👖🎒 ግን ማን ይሰማኛል🤷‍♀🤷‍♀🙆      አረ ምን ይሻላል!!!!🤷‍♀🤷‍♀

እቺን ቃል ንገሯት ተፈርዶብኝ እንጂ መለየት ተስኖኝ ጥሬውን ከብቅል፤ አገሬው ምድር ላይ እሷ ብቻ ቆንጆ የቀረች ይመስል፤ ዞር ባለች ቁጥር አትራቂኝ እያልኩኝ የምለማመጣት፤ ልቻለው ብዬ እንጂ ምሳሌ ከመሆን አፍቅሮ ከማጣት፤ ገደል ግቢ በሏት . . . ይሄው ደሞ ዛሬ... ይሄው ደሞ ዛሬ ገላዋን በሙሉ አወደችው ሎሽን፤ ፀጉሯን አጎፈረች ደመቀች በሽንሽን፤ ከንፈሯን ምን ይሆን ደሞ የቀባችው፤ የእጇን አይበሉባ በቄንጥ አጎናትራ ሰዓቷን አየችው፤ ገና ነው መሰለኝ .. ጊዜን ታዘበችው.. በአፏ ሸብረክ አርጋ እየገረመመች፤ መንቀር አለችና እግሯን አመሳቅላ መስታወት ፊት ቆመች፤ ደሞ ፈገግ አለች፤ ጥርሷ ይርገፍና... ማሪያምን ታምራለች. . . ዘከርኳት በወዳጅ መከርኳት በዘመድ፤ ቀለበት አይጠቅማት አሰርኳት በገመድ፤ ገደል ግቢ በሏት. . . ልቧን ከጋረደው ወዳጅ ከከለላት ስውር አይነ ጥላ፤ እዲህ እያማረባት መሄድ ከጀመረች አፍቃሪ ሰው ጥላ፤ ልክ እንደ ገላዋ ይለስልስ መንገዱ ፍፁም አይጎርብጣት፤ አየሩ በሙሉ ፍክት ይበልላት ልክ እንደ ጥርሷ ንጣት፤ እያልኩኝ መርቄ፤ እያልኩኝ ፎክሬ፣ እንደ ገጣሚ ቃል ልቤን አልጀነጅን የት አባቷንና... የት አባቷንና እዲህ የሚያምርባት የት እናቷንና እዲህ ሚደምቅባት እስከ መቼ ድረስ... እስከ መቼ ድረስ ስቀባ ኖራለው ጉድፍ ልቧን ስኩል፤ ገደል ግቢ በሏት. . . እኔ ገደል ስር ነኝ ድገት ከወደቀች በቆሻሻው በኩል፤       #ሼር  

​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​▓▓▓▓▓▓  ግጥም  ▓▓▓▓▓▓ እንደውም እግዜር ቢፈቅድ በቸር በፀጋው ቢቀባኝ በነጥብ ምልክት አርጎ ከንፈርሽ ግርጌ ባስገባኝ! አንቺም መስታወትሽ ፊት ቀለም ልትቀቢ ከንፈርሽን እሽኩርምም ፍንድቅ ስትይ አያለሁና ማፈርሽን፤ ለወዳጅ ዘመድ በሙሉ ማርያም በተኛሽበት በድንገት እንደሳመችሽ አወራሽ አይደል? ይመችሽ! ሳቂበት የታባቱና ድመቂ ፍ-ክት ፍክትክት በማርያም የተመሰልኩት እኔ ነኝ ያንቺ ምልክት! እንኳንስ ከንፈርሽ ግርጌ ቢያኖሩኝ ተረከዝሽ ስር ለመኖር እንዴት ይመቻል ሳይወደው ከኖረው ህይወት በፈቃድ የተረገጠ አፍቃሪ መች ይሰለቻል! ለወዳጅ ዘመድ በሙሉ ማርያም በተኛሽበት በድንገት እንደሳመችሽ አወራሽ አይደል? ይመችሽ! (አስታወሰኝ ረጋሳ) ━━━━━━✦✗✦━━━━━━━ ምርጫዎ ስለሆነ እናመሰግናለን 🙏 Join us 👇👇👇 🔥 @HIYWETE_QUOTES 🔥 🔥 @HIYWETE_QUOTES 🔥

ቤተክርስቲያን በአንድ መንበር የኖረች በአንድ ሲኖዶስ የፀናች የሀዋርያት ወርች ሁሉን ያሳለፈች አንዲት ቅድስት ክብርት ቤተክርስቲያን ዛሬ በዚህ ዘመን ቀላዋጭ ቅልውጥውጥ የበግ ለምድ ለብሶ ደጃፏን በርቅሶ ስርዓቷን አፍርሶ ጥራዝ ነጠቅ ሆኖ እራሱን አግኖ ሌላን አኮስሶ ሀቅ አመድ አልብሶ በጉልበቱ ነግሶ ቢዝት ቢፎክርም ቃልኪዳን የሰጣት በደሙ ያፀናት እርሱ አይጥላትም ሌሎች ምን ቢገፏት ናትናኤል በላይነህ 🖋🖋🖋

photo content

1.97 MB

🏁🏁🏁 ገላሽ ገላ አይመርጥም 🏁🏁🏁 ገላሽ ገላ አይመርጥም ፣ ከሁሉ ይጋደማል ከንፈርሽ አየር ነው ፣ በሁሉም ይሳማል ከሴት ክብርሽ ይልቅ ፣ ስሜትሽ ይቀድማል። ።።። ነግሬሽ ነበረ፡፡ ጭን ከሰማይ ቢገዝፍ ፣ ከጭንቅላት ያንሳል ምን ተራራ ቢመስል... ጡትም አቅመ ቢስ ነው ፣ ሲነኩት ይፈርሳል፡፡ ነግሬሽ ነበረ.... ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን እንደሚስብ የወንድ ልጅን ዐይን.. ከተበተነበት ፣ እንደሚሰበስብ ነግሬሽ ነበረ... ሴት ክብሯ የአምላክ ነው ፣ እንደ እናት ስታስብ!!! ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ ነግሬሽ ነበረ... ክብረቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም የወለዱ ሁሉ ፣ እናቶች አይደሉም ሴት ልጅ ስታማርጥ ፣ ለራሷ ምራጭ ናት በክብር ነው እንጂ. በመውለድ አይደለም ፣ የሚኮነው እናት፡፡ ።።።።። ነግሬሽ ነበረ እናትነት ስሟ ከክብሯ ነው እንጂ ፣ ከልጇ እንዳልመጣ ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ። ሴት ክብሯን ስታጣ ፣ እድሜዋ ይሔዳል የወንድ ልጅ ቤቱ... የሴትልጅ ውበት ነው ፣ ካየበት ይለምዳል፡፡ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ ነግሬሽ ነበረ... ጭንሽ ሴትነትን ፣ ከቶ እንደማይበልጠው ቁንጅናም ይረክሳል! ብቻውን እንዲቀር ፣ ሁሉም ከመረጠው! ።።።። ነግሬሽ ነበረ ብነግርሽ ብነግርሽ ፣ ባትሰሚኝም ቅሉ "ሰደበኝ" በማለት ፣ ታወሪያለሽ አሉ ልክ ነሽ አንዳንዴ እውነቶች ስሜት ፊት ፣ ስድብ ይመሥላሉ። ።።። ሞኝ ሰው ሲመክሩት ሞኝ ሰው ሲነግሩት የቀኑበት መስሎት ፣ በከንቱ ቢታበይ ግን እነግርሻለሁ! ነግሪያት ነበር ስል ቀንቶ ተናገረኝ ፣ ወይም ሰደበኝ በይ። ።።። ግን እነግርሻለሁ ግን እመክርሻለሁ ሴት ልጅ ክብሯ ሲጎድል ፣ ውበቷ አይመችም ሁሉም ይተኛታል ፣ ከአንዱም ልብ የለችም

ህገ ሰካራም (በላይ በቀለ ወያ) . . "ነገሩ ነው እንጂ ፣ አረቄ አያሰክርም አሳሪ ከሌለ ፣ ገመድ ሰው አያስርም ወዳጅ ዘመድ እንጂ ፣ አፈር ሰው አይቀብርም፡፡" ይላል የሰከረ! አረቄ ቤት ሆኖ... መተዳደሪያውን ፣ ህግ እያዋቀረ ። ......................................................... እንደሰካራም ህግ ፣ እንደስካር ወሬ አረቄ ቤት ሆኜ... አረቄ እየጠጣሁ ፣ በነገር ሰክሬ ስለ ሰካራም ህግ ፣ ላውራሽማ ፍቅሬ ። ............................................................. እዚህ አረቄ ቤት... ከተሰበሰበው ፣ የሰካራም አባል ስሙን የማላውቀው ፣ "ሰካራም" የሚባል አንድ የሰከረ ሰው ፣ እንደተናገረው ሀገርሽ ሀገሬ... "መልሱን ጠጣንበት!" በሚለው ህግ ነው ፣ ምትተዳደረው ። .......................................................... "ለውሃ" እያሉን ፣ ገንዘብ እያዋጣን "ለመብራ " እያሉን " ገንዘብ እያዋጣን "ለመንገድ " እያሉን ፣ ገንዘብ እያዋጣን "ለምን መብራት ጠፋ? እንዴት ውሃ የለም ፣ ለምን መሄጃ አጣን?" ብሎ ከመጠየቅ ሳይሻል አይቀርም... "መልሱን ጠጣንበት " ፣የሚል ህግ ማፅደቅ ። ............................................................ ህጉ እንደመፅደቁ የህዝብ ጥያቄ ፣ እንዳለማለቁ " ለምን እንዴት ?" ብሎ ፣ መጠየቅ አይሰራም "መልሱን ጠጣንበት!" ብሎ ያፀደቀው ፣ ህግ አለው ሰካራም ። ............................................................ ወንጀለኛው ሁላ ... ዳኛውን ጠብቆ ፣ ገንዘብ ካቀበለ በሺህ ምስክር ፊት.... የመሰረትነው ክስ ፣ "ውድቅ" ከተባለ "ለምን እንዴት ?" የሚል ... የከሳሽ ጥያቄ ፣ መልስ ካልተሰጠው በሰካራም አንቀፅ... "መልሱን ጠጣንበት !" የሚለው ህግ ነው ፣ የሚረጋገጠው ። ........................................................... አንደ ህገ መንግስት... ተፈፃሚነቱ ፣ ቢሰራም ባይሰራም "መልሱን ጠጣንበት!!" ብሎ ያፀደቀው ፣ ህግ አለው ሰካራም ። እንደሰካራም ህግ ፣ እንደስካር ወሬ አረቄ ቤት ሆኜ.... አረቄ እየጠጣሁ ፣ በነገር ሰክሬ እኔን አረቄ ቤት ፣ ምን እንደወሰደኝ? አረቄ መጠጣት ፣ ማን እንዳስለመደኝ? አትጠይቂኝ ፎቅሬ ። . . . መልሱን ጠጣሁበት !!! 👇👇

ከስራ ስመጣ ማታ ላይ አምሽቼ * ስኳር የለም እንጂ ሻይ ቅጠል ገዝቼ…*    ውሃ የለም  እንጂ ማንቆርቆርያ አምጥቼ…*    መብራት  የለም እንጂ           እቤቴ ገብቼ…* ኔትወርክም አይሰራም    ሞባይል ገዝቼ…**    ታዳያ ምን ይሻላል ሀሳቤን ቀየርኩኝ…* እንቅልፌን ሳይዘጉት   ቀድሚ ተኛሁኝ…* 😅😁😜

እሳት_ወይ_አበባ፤_ሎሬት_ጸጋዬ_ገመድህን_የግጥም_መድብል.pdf1.13 MB

እንኳን ለወርኀ ጳጉሜን በሰላም አደረሰን::