cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ቅዱስ ፋኑኤል አባቴ✝️✝️✝️⛪️⛪️⛪️ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እዚህ ቻናል ላይ ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት ከነዜማቸው, የስብከት video እና መንፈሳዊ ፎቶዎችን ያገኛሉ።

Show more
Advertising posts
715
Subscribers
No data24 hours
+57 days
+1730 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ቅዱስ ጴጥሮስ ወይም ስምዖን ጴጥሮስ (አራማይስጥ፦ ሸማዮን ከፓ፤  ዕብራይስጥ፦ שמעון בר יונה‎ ፦ ሽምዖን ባር ዮና፤ ግሪክኛ፦ ፔትሮስ፤ 8 ዓክልበ. ግ. - 56 ዓም) የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ እና መጀመርያው የሮሜ ጳጳስ (ፓፓ) ነበሩ። የተወለደው በ ፩ኛው ክፍለ ዘመን በገሊላ ስም መጀመሪያ ስምኦን በኋላ ጴጥሮስ የአባት ስም ዮሐንስ ወይም ዮና ዓመታዊ በዓላት ሐምሌ ፭  ጴጥሮስ ወጳውሎስ የሚታወቀው በሊቀ ሐዋርያነቱ፣ የገነትን ቊልፍ ከክርስቶስ በመቀበሉ፣ በሰማዕትነቱ ፣ ተዘቅዝቆ በመሰቀሉ ያረፈበት በ፷፬-፷፰ ዓ.ም.በቯቲካን ሂል፣ ክሌመንታይል ቻፕል፣ ሮም፣ ጣሊያን፣ በሮሜ መንግሥት በራሱ ምርጫ ተዘቅዝቆ በመሰቀል የሚከበረው በመላው የክርስትና ሃይማኖት እምነት ተከታይ ሥራው መጀመሪያ ዐሣ አጥማጅ በኋላ ወንጌል ጸሐፊ ሰባኪም
Show all...
ኹለቱም ሐዋርያት አንድ ቀን ተካፍለዋል፤ እነዚህ ኹለቱ አንድ ነበሩና። እና አንድ ዓይነት መከራ ቢደርስባቸውም አንድ ሆነው ነበር። እኛም በሐዋርያት ደም የተቀደሰን ይህችን ቀን እናከብራለን። ያመኑትን፣ ሕይወታቸውን፣ ድካማቸውን፣ መከራቸውን፣ ስብከታቸውን እና የእምነት ንቀታቸውን እንቀበል። [ሕዝቅኤል 34፡11-16] [እግዚአብሔር አምላክ ለእስራኤል እረኛ ይሆናል፣ እነርሱም መንጋው ይሆናሉ።] [መዝሙረ ዳዊት 87 [የእግዚአብሔር ከተማ የጽዮን መሠረቶች በተቀደሱ ተራሮች ላይ ያርፋሉ። ከብዙ አሕዛብ በጽዮን ተወለዱ።] [2ኛ ጢሞቴዎስ 4፡1-8] [ጳውሎስ እንዲህ ሲል ጽፏል፡- "አሁን ለመሥዋዕት ዝግጁ ነኝ የምሄድበትም ጊዜ ቀርቦአል። መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ ሩጫውን ጨርሼአለሁ ሃይማኖትንም ጠብቄአለሁ”] [ዮሐንስ 21፡15-19] [ኢየሱስ ከሞት ከተነሣ በኋላ ጴጥሮስን፡- "አንተ ወጣት ሳለህ ወደምትወደው ትሄድ ነበር ነገር ግን በሸመገልህ ጊዜ ወደ ተወሰድክበት ትሄዳለህ" አለው። በዚህ ቃል የጴጥሮስን ሞት ተንብዮአል፤ ከዚያም፡- ተከተለኝ አለ።  
Show all...
👍 1
አንተ ሰው ቃለ እግዚአብሔርን ተማር፤ ባትለወጥም ዝም ብለህ ተማር! ኹልጊዜ ተማር። ላትስተካከል ትችላለህ፤ ላትለወጥ ትችላለህ፤ ግን ተማር። ቢያንስ ቢያንስ ጥሩ ሰው እንኳን ባትኾን ራስህን ለመውቀስ የምትችልበት ዓቅም ታገኛለህ። ካልተማርክ ግን ራስህን እንኳን መውቀስ የምትችልበት ዓቅም አታገኝም። ስለዚህ ተማር! ስትማር ቢያንስ ኃጢአት እንኳን ስትሠራ ራስህን እየወቀስክ ትሠራለህ። ይህች የንስሓ በር ትኾንልሃለች፡፡ አንድ ቀን ወደ ንስሓም ትመራሃለች። #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
Show all...
ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ
Show all...
ሐምሌ 5
እንኳን ለብርሐናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ዓመታዊ የእረፍት በዓላቸው እንዲሁም ለፃድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዓለ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን አሜን። #OrthodoxTewahdo #ኦርቶዶክስ #profile #timline #post #story On Telegram👇          • t.me/winagfx2          • t.me/winaGraphics Share 🙏 https://t.me/winaGraphics
Show all...
“ዘወትር በዐይንህ ፊት ፈሪሃ እግዚአብሔር ይኑር፤ ሕይወትና ሞት የሚሰጠውን አዘክረው፡፡ ዓለምንና በዓለም ያለውን ሁሉ ጥላው፤ ከሥጋ የሚመጣውን ደስታና ሰላም አትሻ፤ ለዚህኛው ኑሮ ሙትና ለእግዚአብሔር ሕያው ሁን፤ ለእግዚአብሔር ቃል የገባኸውን አትርሳ፤ ያም በፍርድ ቀን ካንተ ይፈለግብሃል፡፡ ረኀብን በጸጋ ተቀበለው፤ ተጠማ፥ ተራቆት፥ ንቁና በሐዘን የምትኖር ሁን፡፡ በልቡናህ አልቅስና ጩኽ፤ ለእግዚአብሔር የምትመች መሆን አለመሆንህን ፈትን፤ ሥጋህን ቀጥተህ ነፍስህን ታድናት ዘንድ፡፡” (አባ እንጦንስ)
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.