ዳዊት ጌታቸው።(እይታ)
Open in Telegram
452
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ፈረንሳዊው ዮሴፍ ዴዝሬ ኮ በ1826 የሳለው ስእል ነው።
አንድ ሰው በቅርብ ያሉ ልጅና ሚስቱን ፍፁም ዘንግቶ ራቅ ያለውን አባቱን ሊያድን ሲሞክር ይታያል።
~
#ተምሳሌትነት:
ሚስት: ህይወትን ትወክላለች
ልጅ፡ ነገን ይወክላል
አባት፡ ትናንትን ይወክላል
~
የስእሉ ጠቅላላ ፍች፡
ትናንትናውን ሙጥኝ ብሎ ይዟል። ስለዚህም ህይወቱን እና ነገውን ሊያጣ ነው።
~
ትምህርት፡
የኑሮ ጥበብ ደግሞ መቼ መያዝና መቼ መልቀቅ (መተው) እንዳለብህ ማወቅ ነው። ትናንትን ሙጥኝ ብለህ ይዘህ ዛሬ ላይ ያለህይወትህንና የነገ ተስፋህን በከንቱ አትግደል።
~
ከ the HR diary ያገኘሁት🙏
ወንድም በጠፋበት በዚ ጥቁር ዘመን
እንደ እህቴ ሳይሽ
የገዛ ፎቶዬን ሊያውም ከንፈሩ ለይ ስትስሚ አየውሽ....
ቅስሜን ሰበርሽው
ዳዊት ጌታቸው✍️✍️✍️
Still በ ውስጥ መስመር ብሄር እና ሀይማኖት ጠያቂ nigga እያስቸገረ ያለበት ሀገር ውስጥ ነው የምንኖረው እኮ....የ ጃፓን ወጣቶች mars ለይ ኮብልስቶን እና መብራት ገንብተው ጨርሰዋል...የ ሀገሬ ጉዶች ደግሞ እገሌ ያማልዳል አያማልዱም በሚል ክርክር ይፈሳፈሳል😂😂 ለማንኛውም ዘሬን እና ቁርጥ ያለው ሀይማኖቴን አሳውቃችሁ ዘንድ ይኸው 1000299610229...ገቢው ለ አባይ ግድብ ይውላል
እገሌ:-ዝርዝር ሳንቲም ይዘህ አይደል ለ የኔቢጤዎቹ እየሰጠህ እለፍ...
እኔ:-አልያዝኩም!!
እገሌ:-ኪስህ ውስጥ እኮ ሲያቃጭል ሰምቻለው ብዙ ሳንቲም
እኔ:-ሳንቲም አይደለም ጥይት ነው!! ካላመንክ ይኸውልህ አሳየሁት አልደነገጠም
እገሌ:-እሱንም ቢሆን ስጣቸው ከዚ ኑሮ ይገላገሉ ደግሞ እዚ ሀገር ኡፍፍፍ...
እኔ:-ጥይቴን አየሰጠዋቸው"ሙቱልኝ ስለ አዛኝቱ...
የኔቢጤዎቹ:-እግዜር ይስጥህ ገላገልከን...
እያለቀስኩ ወደ ቤቴ
ጥይት እስክመፀውትሽ እቀፊኝ....
@dawitview
ዳዊት ጌታቸው
ቀና አትበይ እሺ!!! ባለፈው ቀና ስል ምን አየው መሰለሽ...ከ ጎራዴ ስለት የከፋ ስድብ የሚተፉ ወጣቶች፣ከ ሰፈር አውደልዳይ የተወነጨፉ ጥይቶች፣በምን ለብሷል እና በምን አላት የሚቅበዘበዙ አይኖች አይቼ ተመለስኩ።አንቺ ደግሞ ይሄን ትርምስ መቋቋም አትችይም።ምክንያቱም መንፈስሽ ገና ልጅ ነው።በ ትእቢት ቀና ብሎ ያልሄደ። ደግሞ ምን እንደሚገርመኝ ታውቂያለሽ? ቀና ባልሽበት ቅፅበት የተመረዘው አለም ትኩረቱ አንቺ ለይ ይሆናል!!ምክንያቱም ብርሀን ነሽ ጨለማ መሀል የምትወጪ።እና ምን ልልሽ ነው ማቀርቀርሽ ባይጠቅምም አይጎዳም!!እንዳቀረቀርሽ እቀፊኝ!!!!!!
@dawitview
ብስራት ሱራፌል አልበሙን ከታሰረበት ሲለቀው እኛም ልንሰማው ተገደድን ከዛ አጨበጨብንለት!!!!
ከዘፈኖቹ የሚጣል ባይኖርም
"እና"፣"እረፊ"፣"በቃ"፣"akka hadhaa" የሚሉትን ግን ሰምቼ አልጠግብ ብያለው። በተለይ እና የሚለው እና እረፊ its golden
በነገራችን ለይ ምስሉ ለይ የምትመለከቱአት ወጣት ፈረንሳዊት ናት እና ለስራ ጉዳይ የፈረንሳይ ቀበሌ የሻይ ክበብ ውስጥ አጊንቻት ነው!!አማርኛ አትችልም!!!😂😂
የሰርጌ እለት ማታ መኝታቤት ተደብቄ እያለቀስኩየፃፍኩት አቤቱታ።
እንደ እድሜ እኩዮቼ...
አራቱን በግራ
ሁለቱን በቀኜ
ደርድሬ አስተኝቼ
አንዷን ከ አንዷ ጋራ
ደብልቄ ጠርቼ
ስማቸው ጠፍቶብኝ
መዝገቤ ሞልቶብኝ..
እስኪደክመው አይኔ በውድቅት ለሊት
ብዙ ሳልጀነጅን በአጭር የፅሁፍ መልእከት
ያለ ፍሬ ስሮጥ
ቢያንስ ለፌሽታ 100 አንሶላ ሳልገልጥ
እንደ ጎረቤቴ መወስለት ሳልኮርጅ
ወጉ ደርሶኝ ሳልክድ የወለድኩትን ልጅ
በ 30 አመቴ 80 ፈርሜ
መብቶቼን በሙሉ ሰብስቤ አውድሜ
ይኸው ዛሬ ለሊት
ጣቴን ረገምኩት
"መብራቱን አጥፋ ልተኛበት" እያለችኝ ነው ደህና ሁኑ😭😭
ዳዊት ጌታቸው ©️
@dawitview
ከተመረቅሁ በሗላ ነገሮች የሚደረጉት በሁለት ተከፍለው እንደሆነ የሰፈር ሰዎች ሊያሳውቁኝ ዳር ዳር ይሉ ጀመር።ዲግሪ ያለው የሚያደርጋቸው እና የማያደርጋቸው ተብለው ይከፈላሉ አሉኝ። ዲግሪ ሳይኖረኝ በፊት ድድ ማስጣት ተቀዳሚ ስራዬ ነበር።ዲግሪ ሲኖረኝ ደግሞ ድድ የማሰጣበትን ድንጋይ ፈልፍሎ የራሴን የላሊበላ አይነት ወይም የሶፍ ኡመር አይነት ዋሻ ሠርቼ እዛ እንድኖር አይነት ይመክሩኛል።
ስራ አገኝህ ብለው ይጠይቁኛል ብዬ ሳስብ እነሱ ደሞዝ አልደረሰም ይሉኛል😭😭...ቆንጥጬ አሳድጌውማ ስራ ሲይዝ አይረሳኝም ባዩ በዛ...ለቆነጠጠኝ ሁሉ ስጦታ ላበርክት ካልኩ እኔም ከመጦር ላልወጣ ሆነ እኮ ወገን
በድፍኑ እግዜር ይስጥልኝ።
ስራም ይዘህ አትወፍርም የሚለውን አባባል ሽሽት ካሁኑ በመተማ አድርጌ ካዛብላንካ ልገባ አስቤአለው😭😭።
ዲግሪ ኖሮህም እርጥብ ትበላለህ የሚል አስተያየት ሲዞረኝ ይታወቀኛል...ግን አምሮኝ እንጂ ዮናስ ጨርጨር በበቃኝ በልቼ የክትፎ ጣባ ማጠብ አቅቶኝ አይደለም።
ዲግሪ ያለው ሰው ከሌለው የሚለየው ፀሀይ በመቋቋም ችሎታው ብቻ ነው።ስለዚ ድሮ የማደርገውን ነገር ሳደርግ ብታዩኝ አትፍረዱ ወገን
