en
Feedback
ዳዊት ጌታቸው።(እይታ)

ዳዊት ጌታቸው።(እይታ)

Open in Telegram

ፍቅር!ሰላም!ግጥም!እይታ! sad! ለ አስተያየት @addemiinilik

Show more
452
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በአንድ በኩል ደግሞ ሁሉንም አሪፍ ነገር ኢሉሚናቲ ነው ብለን አንዘልቀውም ወገኖቼ😂

ቴሌግራሜን ገልብጬ አራገፍጉት አዲስ መረጃ አጣው።ተኔ ቻናል ወደ አንዱ ከነፍሁ "ሴት ልጅ እንደወደደችህ ማወቂያ ዘዴ ከሚል ፅሁፍ ውጭ ምንም አጣሁ።በስተመጨረሻ ግን አይኔ አንድ ነገር ለይ አረፈ"ሰላም ተስፋዬ ሻወር ቤት ስትታጠብ ለማየት ይህን ማስፈንጠሪያ(link) ይጫኑ ይላል።ማስፈንጠሪያውን ሳልነካ ግን ስለ አርቲስቷ ይህንን መላምቴን አስቀመጥሁ.... ለማንኛውም አንድ ነገር ልበል...ያ ጅማት አበጣሪ(ጊታሩን ለመንቀፍ ነው)ቧሏ ነው እንዲህ ጉድ የሰራት።በፌሽታቸው ቀን የቀዱትን ካሴት ይዞ ገና ለገና ተፋታው ብሎ መበተኑ ነው ቱ!እሱን ብሎ ወንድ!ይሄኔ እኮ ቆሎ ማይገዛ ገንዘብ ጠይቆ"እንቢ ታልሽኝ ጉድሽን እንደ ኢትዮጵያዊ እንባ በየትቢያው በትነዋለው ብሏት እንቢ ብላው ነው:: ለነገሩ ገንዘብ ቢጠይቅ አትነፍገውም።ለቆሎ መግዣ የጠያቅትን ፍራንክ እንደ መንገድ ዳር ስልክ በአፉ ጠቅጥቃ ዝም ታስብለው ነበር!!ለነገሩ የብር ችግር የለባትም አይደለም ቆሎ የቆሎ ፋብሪካ ገንብታ ሚስጥሯን ትጠብቅ ነበር።እንደው ብታጣ ብታጣ...በተቸገረ አርቲስት በማይጨክኑት ከሼሁ ለይም ቢሆን ተ.በ.*ራ(ተበድራ ብለህ አንብብ አንባቢ ሆይ ኪቦርድ እንቢ ብሎኝ ነው)ትሰጠው እና ሚስጥሯን ትጠብቅ ነበር...ግና ስለፈታችው እንደ ቡሄ ችቦ ተቃጥሎ ሳያስጠነቅቃት ጉዷን እንደ ክረምት አግቢ አባዝቶ በተነው ብዬ አሰብሁ እና እየተከዝሁ..ከ አርቲስቷ መሠረታዊ የገላ አስተጣጠብን ልቅሰም ብዬ(እንጂ አዳማዊ ስሜት ሳይሰማኝ)ምራቄን ውጬ በሬን በጨርቅ ጠቅጥቄ(ምናልባት ድምፅ ካለው አርቲስቷ እንዳትሳጣ ብዬ)ማስፈንጠሪያውን ነካውት።ቀጥሎ ግና እራሴን ሳሚ የኮሚሽን ስራ የሚል ቻናል ውስጥ አገኘውት።አይ ሀበሻ እግዜር ይይልህ።እኔ ግን ድሮም አርቲስቷ እንደዚ እንደማታደርግ አውቅ ነበር!!! ዳዊት ጌታቸው @addemiinilik @dawitview

ተአምር ባልሰራም ለምጣም አቅልሜ ሽባ ባልጠግን በሽባ አቅሜ ውሀን ባልጠምቅ እንደ አዋሽ ጉደር ሙት ባልቀሰቅስ ከ ዝግ መቃብር እንኳን ውቅያኖስ እንኳን ወጀቡን መገሰፅ ባልችል የበኩር ልጄን አትፍረጂብኝ አንቺን መውደዱ አምላክ ያረገኝ እየመሠለኝ.... እንጂ ማድረጉ ከቶ መች ጠፋኝ?! እይልኝ ፍቅርሽ ገደል ሲከተኝ ያኛውን ጌታ እያዳፈረኝ አምላክ ሁን ሲለኝ:: እምምምቢ። ዳዊት ጌታቸው @dawitview @addemiinilik

የእድሜሽ ማለዳ ፈጥኖ እየነጋ ረግፈሽ አደርሽ ስትይ ነኝ ለጋ

ትናንቴ ዛሬ ላይ አሸነፈኝ እና እኔም መውደድ አልቻልኩም እምነት ጠፋኝና

የዘንባባ ቀለበት ስራልኝ አለችኝ...ከነጠላዋ አምልጠው የወጡትን ፀጉሮችዋን እያስገባች....እሺ ዘንባባው የታል አልኳት....ቆንጆ ቢጫ በአረንጓዴ ዘንባባ ሰጠችኝ ጫፉ ሹል ነው---እንደ አይኗ የሚዋጋ።ጣትሽን ልለካው ብዬ ተጠጋዋት...እጣን እጣን ትሸታለች...እንደ እድሜ እኩዮቿ የአልኮል ዴዎድራንት ከላይዋ አይተንም....መቅደስ ውስጥ ነበርሽ አልኳት....እንዴት አወክ ብላ አየችኝ....ሽታሽ....አፈረች...ከ ጳጉሜ ያጠረ....እንደ ቅዳሜ ትደገም የምትባል ቢራቢሮ መሽኮርመም አፍንጫዋ ለይ አርፋ በረረች....አይከብድም ግን እራስ ውስጥ መግባት አልኳት...ማለት አለችኝ...መቅደስ ውስጥ ነበርኩ ስላልሽ ነው....ሌላ ከ ጎንደሬ የተቀዳ መሽኮርመም አሳየች...ጣቷን ለክቼ ዘንባባባውን ማጠላለፍ እንደ ጀመርኩ...አንተ ግን ቀለበት መስራት እየቻልክ ለምን ጣትህ ባዶ ሆነ አለችኝ....አስረዳዋት....ቀለበቴን በ ደረቅ ዘንባባ ሰርቼው ነው...ደረቅ ዘንባባ አይታጠፍም...ላጥፈው ሳዞረው ተሰበረ....ከሽ...ለዛ ነው ቀለበት የሌለኝ...ስላት አይዞህ እኔ ለጋ ዘንባባ ሰጥሀለው አለችኝ...አልገባትም እንጂ ልላት የፈለኩት ከ ሚስቴ ተፋትቻለው ነው....ቀለበትሽ ይኸው ስላት ዘንባባ ሰታኝ ሄደች.....ዛሬ ነገ ሰራዋለው ስል ይሄም ደረቀ...አልገባችሁም እንጂ ልላችሁ የፈለኩት..... ዳዊት ጌታቸው @addeemiiniilik @dawitview

ምን ይላል ይሄ!!!

እየመጡ ነው 🏃 ሰሞኑን የታላቁ ሩጫ ተካሂዶ ነበር።ፊቴን አቅልሜ አልያም ሄዋኔን አስከትዬ ዱብ ዱብ ሳልል ነው ያለፈው። ለቀጣይ አመት ግን እቅድ ነድፌአለሁ።ቢያነስ በጂም ቀርቶ በፀሀይ ካሎሪ ማቃጠል ስላለብኝ መንጎማለሌ አይቀርም!! ወደ ቀደመው ነገሬ ስመለስ...ሩጫው ለይ አሪፍ አሪፍ ነጥቦች ተነስተዋል ባይ ነኝ.... አስፓልት ለይ ከመቦረቅ በዘለለ ቁም ነገር የዘነበበት ወቅት ነበር።የ ሩጫ ትራክን ለ ፓርላማ መጠቀም ጤናን እና መብትን ማስጠበቅ እንደሚቻል አይቼበታለሁ....እየመጡ ነው የሚለው ሀረግ እጅግ ተስፋ ሰጪ ሆኖ ነው ያገኘውት...የ ቴሌቭዥን ጣባያዎቻችን በወጥ ቀማሾች እና በጥፍር ሞራጆች ስለተሞሉ እንዲህ አይነት መድረኮች ጭንቅን መተንፈሻ ቢሆኑ አይከፋም....እየመጡ ነው....አዎ እውነት ነው እየመጡ ነው ባለፈው እንጦጦ ንፁህ አየር ለመቀበል የሰው ፓርክ እንዳልረግጥ ጥግጥጉን ስራመድ እልፍ አናብስት እየመጡ አየሁ....በጣም ተቆጥተዋል...በአሁኑ አመጣጣቸው ቀጥታ አንበሳ ግቢ ገብተው ፍርግርግ ጀርባ ተኝተው ጠሀይ ሚሞቁ አይመስሉም።ስለዚህ አናብስቱን የምትቃወሙ ካላችሁ ሌላ ታላቅ የሽሽት ሩጫ ሩጡ....መናገር የምችለው ግን አዎ "እየመጡ ነው"!!! ደህና ሁኑ ዳዊት ጌታቸው @addemiinilik @dawitview

በግዜ ተኙ ደህናም እደሩ!!!

እንዲሁ በዋዛ መሞት አለወይ?! ሰውስ ስላወራ መሞት አለ ወይ???

ወተው ሲቀሩ ለሞት ሲዳሩ 👰 ደረስን ሲሉ ከ ተስፋ መንደር ቆመው ሲገኙ በሰማይ ቤት በር አልቅሰን ቀብረን ሀዘናችንን በንፍሮ ውጠን ወጥቼ ገባው እግዜር ይመስገን!! በልብሷ ቀለም በአፉ ቋንቋ ወገን ሲረግፍ እንደ እግር ዶቃ ጋሬጣ ይዞ እንደበጠሰው ጎዳና ወድቆ ጭቃ ሲውጠው አለው ተመስገን ዛሬን አይቼ ኑሮ እና ሰውን ከ አውሬ ሰግቼ ወጥቼ ገባው ውብ ገፄ ቆስሎ ወጥቼ ገባው አንድ አይኔ ጎድሎ ይሁን ይመስገን መትረፌ ጤና ጉድን ለማየት መች አነሰና!! ዳዊት ጌታቸው for comment @addemiinilik @dawitview

እማር መስሎኝ "ሀ"ብዬ በሳር መከራዬን ሸመትኩት ባሳር ቆቤ ቆቤ ምን ፈየደ ጠሀይ ፊቴን ካነደደ። ውስጡ ተስፋ አለ ሲሉኝ ምነው ታዲያ እኔን ሰፋኝ። ልጅነቴን ጠመኔ ፈጀው ውሀ አይኔን ወረቀት ወጋው
እማር መስሎኝ "ሀ"ብዬ በሳር መከራዬን ሸመትኩት ባሳር ቆቤ ቆቤ ምን ፈየደ ጠሀይ ፊቴን ካነደደ። ውስጡ ተስፋ አለ ሲሉኝ ምነው ታዲያ እኔን ሰፋኝ። ልጅነቴን ጠመኔ ፈጀው ውሀ አይኔን ወረቀት ወጋው ለጋ ወገቤ ቦርሳ አግብቶ ጮርቃ ጣቴ ደብተር በስቶ ሀገር ብዬ ፈርሶ ቤቴ እዳ ነው ወይ ሽልማቴ?? ገዋን ደጉን  ንፋስ ገብቶ ያነሳዋል በዚ መጠን መማር ቀሏል?!!! ዳዊት ጌታቸው @dawitview comment @addemiinilik የስእሉ ባለቤት እግዜር ይስጥህ/ሽ።ጥሩ መንደርደሪያ ነው።

በደጉ መሪአችን ግዜ ቶሞካ በረንዳ ለይ ቁጭ ብዬ ቡና እየጠጣው እግረ መንገዴን የ አዳም ረታን"ከሰማይ የወረደ ፍርፍር አነብባለሁ።ታዲያ እንዲህ የማደርገው ከኩንስፓኛ የወረደ ጥብሴን በልቼ ነው!!ወዜም ሸጋ ነበር።እንዲህ እያነበብሁ በመሀል.."ምሳ ሰአት ለይ ፍርፍር አይከብድም ግን"የሚል የሴት ድምፅ ሰማለው(በመጥሀፉ ርእስ ልትጃለስ መሆኑ ነው)....አዲሱ የለከፋ ስልት እንደሆነ ስለማውቅ ፊቴን መጣፉ ውስጥ ቀብሬ"ዋናው በቀን 3 ግዜ መብላቱ ነው:ይህንንም እንዳናጣ አልሁዋት!!ሳልፈቅድ ወንበር ስባ ተቀመጠች:ሰርኔ በሽቶዋ ሰርግ ደገሰ።አንባቢ ወንድ እወዳለሁ አለችኝ።አንባቢ ወንድ የምትወድ ሴት ምርጫዬ ናት አልሁዋት ሳቀች።ከዚ በላይ አቀርቅሮ ማንበብ ንቀት ስለመለኝ መጥሀፌ ውስጥ ጣቴን እንደ እልባት ተጠቅሜ በአንድ እጄ ቡናዬን ፉት እያልሁ ብዙ አወራን።ቆንጆ ነች ውሀ መነጥር ያደረገች፣ጠጉሯ ከቡሄ ጅራፍ የረዘመ በፈጣጣነቷ ልክ አይን አፋር።ቡና ጋበዝኃት ኬክ በላን።ሂሳብ ሲመጣ 56 ከነ ቲፑ ከፍዬ እንድንራመድ ወጣን።ከ ምናምን አመት በኋላ ጠሀዩ መንግስታችን መጣ ቶሞካ መግቢያው በር ለይ ቆሜ ከሰማይ የሚወርድ ፍርፍር ካለ ብዬ አንጋጠጥሁ።ጠግቦ ማንበቡ ቀረ እና አንጋጠን አነባን። ዳዊት ጌታቸው @dawitview Comment @addemiinilik

ቁጥርጥሯ ያምራል።አንዱን ዘለላ ወስጄ ቋጠርኩት....እንደዚህ ማሰር ትችላለህ እንዴ?አሳየኝ!አለችኝ።መልሼ ፈታውት እና ልብ ብለሽ እይ አልኳት...ወዲያው ቻለች ደስ አላት....የት ለመድክ ግን እንደዚ ማሰር አለች...አፏ በጠጣችው አራዳ ተሳስሯል...መጠጥ አትችልም...እ አልኳት...የት ለመድክ እንዲ ማሰር ነው ያልኩህ አለችኝ....ወፍ የሆነሽ ሴት አጋጥመሽኝ እንጂ ማሰር አልችልም ነበር አልኳት...እናትን ብላ ሳቀች....ታምራለች...መሳል ነበረ!!!!

ሰው ከሰማህ ወዳቂ እንደሆነህ እወቀው....እየጣርክ እየደከምክ ባለህበት ሰአት ያንተን ልፋት ከተጠናቀቀ ስኬት ጋር እያወዳደሩ ልፋትህ ምንም እንደሆነ ሊያሳዩህ ይጥራሉ።ያንተ የስኬት ቀን ካንተ ምን ያህል እንደራቀ በተወላገደ መነጥራቸው ያሳዩሀል።የዚኔ ከሰማሀቸው እውነትም ዝም ብዬ ነው የለፋሁት እኔን ብሎ ትጉህ ትል እና ውሎህ ጃንቦ ቤት አዳርህ ኬኖ ይሆናል።ምክር ቢጤ አስታውስ ቤትህ አጠገብ ያለ ኩሬ ውስጥ እንቁራሪቶች እየጮሁ እንቅልፍ እንደሚይዝህ!!!! ዳዊት ጌታቸው

ቀሚስ እና ታቦት እግዜር ተቆጣ ሄዋን ተገልጣ ቢያያት ፈራርሳ ቁጣው ነገሰ በሸማኔ ለይ ጥርሱን ነከሰ መብረቁን አጥኖ ኩንታል ሞት ዘግኖ ሸማኔን ላጥፋ ከነ ድራሹ ብሎ ሲነሳ ትዝ አለው ደሞ ታቦት አልባሹ መሆኑ ማረው!!!!! ዳዊት ጌታቸው!!!

Rediet is back with monster lines❤❤
Rediet is back with monster lines❤❤

I loved their voice and meaning of song