913
Subscribers
-124 hours
+27 days
-730 days
Posts Archive
"በ7ኛው ዙር አገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሰላማዊ መንገድ በማጠናቀቅ የተገኘውን ድል በማስቀጠል በቀጣይ ጊዜ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በሚደረገው ርብርብ መላው አመራርና አባላት ከልማት ወዳዱ ህዝብ ጎን በመሰለፍ የበኩሉን ድጋፍ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል"
አቶ ሚፋታ ሁሴን
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ
ሰኔ 15/2018 ዓ/ም
በ2018/19 ምርት ዘመን 20 ሺህ 518 ሄክታ በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህን ያስታወቀው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት የ2018/19 ዓ.ም የመኸር የተቀናጀ የግብርና ልማት የንቅናቄ መድረክ ''የተቀናጀ ግብርና ለቤተሰብ ብልጽግና "በሚል መሪ ቃል የንቅናቄ መድረክ ባካሄደበት ወቅት ነው ።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ሚፍታ ሁሴን የመክፈቻ ንግግር የግብርና ልማት የወረዳችንና የሃገራችን ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት በመሆኑ ይህንን አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ዘርፉን ለማዘመንና የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መንግስት ልዩ ትኩረት ሠጥቶት እየሰራ እንደሚገኝና ተጨባጭ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ገልጸዋል።
የጽ/ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ መሀመድ ሁሴን ለመድረኩ የተዘጋጁ የወይይት ሠነድ እቅድ አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት ተደርጓበታል።
የግብርናው ዘርፍ ለማዘመንና ውጤታማ ለማድረግ የተሻሻለ ዘር ማቅረብ ፣በዘርፉ የሰለጠነ የባለሙያ ድጋፍ ክትትል ውስንነት መኖር፣ መሬትን አሟጦ ለእርሻ ስራ አለማዋል፣ የቡና ችግኝ ተደራሽነት አናሳ መሆን በወቅቱ መቅረብ አለመቻሉን፣አርሶ አደሩ ላመረተው ምርት የገበያ ትስስር መፈጠር እንደሚገባ፤አሲዳማ መሬቶች በኖራ በመታከማቸው ምርት መስጠት መቻላቸው ፤በማሳ ውስጥ ያሉ ዛፎች ማስነሳት እንደሚገባ በውይይት መድረኩ ከተነሱ ሃሳብና አስተያየቶች መካከል በዋናነት ተጠቃሾች ናቸው።
ለተነሱ ሀሳብ አስተያየት ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ሚፍታ ሁሴን ወረዳችን እውቅና እያገኘባቸው እየመጣ ያለው የቡናና የማር ምርት ይበልጥ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አርሶ አደሩ በትኩረት በመስራት በቀጥታ ለውጭ ገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባ አብራርተዋል።
ዛፍን በማንሳትና የማይታረሱ የወል ፣ የማህበር፣ የተቋማትና የግል መሬቶች በማረስ የማይታረስ መሬት ዜሮ ለማድረግ ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንደሚገባ ዋና አስተዳዳሪው አስገንዝበዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የወረዳው የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት
እየተከናወ ያለው የመኸር ስራ በጥራት በመስራት ምርታማነት ለማሳደግ FTC፣የማህበራት እርሻዎች
የግልና የተቋማት ማሳ ላይ ትኩረት በማድረግና የተቋሞች አቅም በማጠናከር ራሳቸው መቻል እንዳለባቸው ገልጸዋል።
አቶ አ/ረሂም አክውም በወረዳው የሚታየውን የግብርና ምርታማነት ስራዎችን በማሳደግና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋት ውጤታማ አርሶ አደር ለማፍራት መስራት ያስፈልጋል በማለት የታቀዱ ተግባራት እንዲሳኩ ሁሉንም አደረጃጀቶች መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል።፨
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ በበኩላቸው በኩታ ገጠም ዘር መዝራት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑ ጠቅሰው ለክላስተር ማሳ ልዩ ትኩረት እንደሚደረግና ከምርጥ ዘር አቅርቦት ላይ በቂ ዝግጅት እንደተደረገ ማሳ ውስጥ ያሉ ዛፎችን ለማስነሳት በመመሪያ መሰረት ተግባራዊ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
በመድረኩም የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን፣ የወረዳው የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ፣ የወረዳው የግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ እና የወረዳው አመራሮች ፣ የቀበሌ ስራ አስኪያጆችና አስተዳደሮች ፣ጽ/ቤቱ የማኔጅመንት አካላት እንዲሁም የቀበሌ አመራሮች የግብርና ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ሰኔ 15/2018 ዓ.ም
"ኢትዮጵያ መርጣለች! አሸንፋለች! ኑ አገር በጋራ እንገንባ"በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የህዝብ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ7ኛውን ዙር ጠቅላላ አገራዊና ክልላዊ የምርጫ እቅድ አፈጻጸምን አስመልክቶ
"ኢትዮጵያ መርጣለች! አሸንፋለች! ኑ አገር በጋራ እንገንባ"በሚል መሪ ቃል ከወረዳው ጠቅላላ አመራርና ህዝብ ጋር የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።
በውይይት መድረኩ ተገኝተው የመክፈቻቻ ንግግር ያደረጉት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን እንደገለጹት የ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሰላምና በስኬት እንዲጠናቀቅ ለማስቻል የጠቅላላ አመራሩና አባላት ድርሻ እጅግ ከፍተኛ እንደነበር ጠቅሰው ምርጫው ፍፁም ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ መሆኑን የገለጹ ሲሆን ለአንድ አገር የተረጋጋ ስርዓት የህግ የበላይነት መስፈንና ሀገረ-መንግስት ለመመስረት ምርጫ የህልውና ጉዳይና ከየትኛውም ትግባር ቀዳሚ እንደሆነ አስረድተዋል።
የ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የተቀመጡ ሁለቱ ግቦች ማለትም ምርጫው ሰላማዊ፣ፋትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና በህዝብ ዘንድ ተዓማኚ እንዲሆን ማድረግ እና በምርጫው ብልጽግና ፓርቲ አቀብላጫ ድምጽ በማግኘት ማሸነፍ መቻሉን አቶ ሚፋታ ሁሴን ገልጸዋል።
ዋና አስተዳዳሪው አክለውም በ7ኛው ዙር አገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሰላማዊ መንገድ በማጠናቀቅ የተገኘውን ድል በማስቀጠል በቀጣይ ጊዜም ለዘላቂ ሰላም መስፈንና የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በሚደረገው ርብርብ መላው አመራርና አባላት ከልማት ወዳዱ ህዝብ ጎን በመሰለፍ የበኩሉን ድጋፍ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።
የመወያያ ሰነዱን በወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የወረዳው የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ ለጠቅላላ አባላቱ እያቀረቡ ነው።
በመድረኩ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ሚፋታ ሁሴን የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳና የወረዳው ጠቅላላ አመራር እና ከየቀበሌዎች ከተለያየ መህበራዊ መሰረት የተውጣጡ ተወካዮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የሳምንቱ ዓብይት ዜናዎች
ሰኔ 14/2018 ዓ.ም
🎤 በ2018 ዓ.ም ባለፉት 11 ወራት 279 ሚልዮን 898 ሺህ 342 ብር ገቢ በመሰብሰ የተያዘው ዕቅድ 99 ከመቶ ተፈፃሚ ማድረጉን በጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ2018 ዓ.ም ክልላዊ የ8ኛ ክፍል ፈተና በሰላም መጠናቀቁን የወረዳው ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ለመሀል አምባ ኮንስትራክሽንና እንዱስትሪያል ኮሌጅ ከ1.9 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የተለያዩ ማሽኖች ድጋፍ አደረገ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በ20 ቀናት እንዲፈፀሙ ታቅደው የሚሰሩት ተግባራት አፈፃፀም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተገመገመ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተሰጠ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨
🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ወረዳዊ የአመራር መድረክ እየተካሄደ ነው።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነጻ ቀበሌዎች በማስፋፋት ለጤና ተስማሚ አካባቢ መፍጠር እንደሚገባ
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከዚህ ቀደም ታርሰው የማያውቁ መሬቶችን የማረስና ወደ ልማት የማስገባት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል!!!
የደሳ ቀበሌ የመኸር እርሻ በምስል በከፊሉ:-
🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ መጎራጎር ቀበሌ በገጠር ስራ እድል ፈጠራ በተደራጁ ወጣቶች በበልግ የለማ ድንች አሁናዊ ሁኔታ በምስል:-
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከዚህ ቀደም ታርሰው የማያውቁ መሬቶችን የማረስና ወደ ልማት የማስገባት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል!!!
የደነብ ቀበሌ አዲስ እርሻ በምስል በከፊሉ:-
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተሰጠ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ሰኔ 12/2018 ዓ.ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ2018 ዓ.ም ክልላዊ የ8ኛ ክፍል ፈተና በሰላም መጠናቀቁን የወረዳው ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በወረዳው የ2018 ዓ.ም ክልላዊ የ8ኛ ክፍል ፈተና በ31 የፈተና ጣቢያዎች በሰላም የተጠናቀቀ ሲሆን 1466 ተማሪዎች ፈተናው መውሰድ መቻላቸውን ጽ/ቤቱ አክሎ አስታውቋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየው ኬኔ በወረዳው ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሠላም መጠናቀቁን አስታውቀዋል።
የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በወረዳው ወንድ 736 ሴት 730 በድምሩ 1466 ተማሪዎች መፈተናቸውን የገለጹት ኃላፊው ፈተናው ያለምንም የፀጥታ ችግርና የትኛውም ተማሪ የዲስፕሊን ጉድለት ሳይታይበት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።
በመጨረሻም አቶ አለማየው እንደገለጹት በፈተናው ሂደት የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት፣ የክልል፣የዞን የፈተና አስተባባሪዎች በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች ተዘዋውረው ምልከታ ማድረጋቸው ገልፀው ፈተናው ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ በየደረጃው የድርሻቸውን ሚና ለተወጡ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
ሰኔ 11/2018 ዓ/ም
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ለመሀል አምባ ኮንስትራክሽንና እንዱስትሪያል ኮሌጅ ከ1.9 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የተለያዩ ማሽኖች ድጋፍ አደረገ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ለመሀል አምባ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የሰልጣኞችን ተግባራዊ ክህሎት ለማሳደግ የሚረዱ ልዩ ልዩ የጋርመንት ማሽኖች ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪና የመሀል አምባ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የቦርድ አባላት በጋራ በመሆን የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ያደረገውን ድጋፍ በአካል በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል።
የመሀል አምባ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዋና ዲን ወ/ሪት ሰላማዊት ኡርባኖስ በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልፀው ይህም የዘመነና በቴክኖሎጂው የዳበረ ሠልጣኝ ለማፍራት ለሚሠሩት ስራ አጋዥ መሆኑን ገልጸዋል።
ወ/ሪት ሰላማዊት አክለውም ቢሮው ያደረገው ይህ ድጋፍ ኮሌጁ የነበረበትን የግብዓት እጥረት በከፍተኛ ደረጃ የሚቀርፍ መሆኑን ጠቅሰው ኮሌጁ በተግባር የተደገፈ ጥራት ያለው ስልጠና ለመስጠት ለሚያደርገው ጥረት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርለትና የሰልጣኞችን የፈጠራ ስራና የስራ ዝግጁነት እንደሚያሳድግ ገልጸው ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪና የመሀል አምባ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሚፋታ ሁሴን በበኩላቸው የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ያደረገውን ድጋፍ በወረዳው መንግስት ህዝብ ስም ምስጋናቸውን ገልጸዋል።
ወቅቱ የሚፈልገውን የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት ተቋማትን በቴክኖሎጂ ግብዓቶች ማሟላት ወሳኝ ድርሻ እንዳለው የገለጹት አቶ ሚፋታ ሁሴን ለተቋሙ አስፈላጊ የሆኑ ድጋፎች በወረዳ ደረጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።
ቢሮው ያደረገው የቁሳቁስ ድጋፍ ዘመናዊ የስፌት ማሽኖች፣ የኦቨርሎክ ማሽኖች፣የልብስ መተኳሻ ጠረፔዛዎች፣ የተለያዩ ለጋርመንት ስልጠና የሚያገለግሉ መሳሪያዎች እና ደረጃቸውን የጠበቁ ጠረጴዛዎችን ያካተተ ሲሆን፤ በአጠቃላይ ድጋፍ የተደረገባቸው ንብረቶች በገንዘብ ሲተመኑ ከ1.9ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመቱ እንደሆነ ተመላክቷል።
