912
Subscribers
-124 hours
+37 days
-730 days
Posts Archive
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ነዋሪ ለሆኑ 5 አቅመ-ደካማ አረጋውያንና ከ202 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የቆርቆሮና ሚስማር በዛሬው እለት ደጋፍ ተደረገ።
ነሐሴ 02/2018ዓም መሀል አምባ
በወረዳው ቦኔ፣መጎራጉር፣ፍቴ፣ጅማ እና ሁትር ቀበሌዎች ነዋሪ ለሆኑት 5 አቅመ-ደካማ አረጋውያን ለእያንዳዳቸው 40 ቆርቆሮና 2 ፓኬት ሚስማር በአጠቃላይ በዛሬው እለት 200 ቆርቆሮና 10 ፓኬት ሚስማር ድጋፍ የተደረገ ሲሆን ጠቅላላው ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን 202 ሺህ 500 ብር የሚያወጣ መሆኑ ተመላክቷል።
በወረዳው "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የወረዳው ወጣቶች ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሸምሱ ኢብራሂም
እና የጽ/ቤቱ ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ጀማል ናስር በጋራ በመሆን ለአቅመ ደካማ አረጋዊያን የቆርቆሮና ሚስምር በአካል በመገኘት ድጋፍ አድርገዋል።
ነሐሴ 02/2018 ዓ/ም
የወልቂጤ ክላስተር ኮሌጆች የ2018 የሰልጣኞች ምርቃት ፕሮግራም በወልቂጤ ከተማ ተካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በጉራጌ ዞን የሚገኙ 8 ኮሌጆች ስልጠናቸው ሲከታተሉ የነበሩ 1ሺህ 74 ተማሪዎችን በዛሬው እለት አሰመረቀ።
የመሀል አምባ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በእለቱ ወንድ=31 ሴት=49 በድምሩ 80 ተማሪዎች በዛሬው እለት አስመርቋል።
ተማሪ ቤቴልሄም ደምሰው 3.94 በማምጣት አንደኛ በመሆን የሜዳሊያና የዋንጫ ተሸላሚ ስትሆን፣ባቡና ዝይን 3.93 እና ተማሪ ሙሰማ ሽኩሬ 3.91 ነጥብ በማምጣት 3ኛ መውጣት የሜዳሊያና ዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል።
የወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክና ሳተላይት ኮሌጅ ፣የአገና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፣ የአረቅጥ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፣ የሀዋሪያት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፣የጉንችሬ የመአልአምባ፣ የድንቁላ ፣ የቋንጤ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጆች በጋራ ሰልጣኞቻቸውን አስመርቀዋል።
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እየተከናወኑ ያሉ የግብርናና ሌሎች ወቅታዊ የልማት ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ ሁኔታ እየተከናወኑ ነው፦አቶ ሸምሱ አማን
ነሀሴ 2/2018(ወልቂጤ)
የተቀናጀ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ስራዎች በትኩረት በመስራት የተሻሻለ ኑሮ እንድንኖር አስችሎናል ሲሉ የወረዳው አርሶ አደሮች ተናገሩ።
የዞን ደጋፊ አመራርና የወረዳው የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የግብርናና ሌሎች ወቅታዊ የልማት ስራዎች በተለያዩ ቀበሌዎች በመገኘት የመስክ ጉብኝት አካሂዷል።
የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን በዚህ ወቅት እንዳሉት በየጊዜው በቁጥር ደረጃ እየቀረቡ የሚገመገሙ ተግባራት መሬት ላይ ያሉና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ ስለመሆኑ የአካል ምልከታ በማድረግ ማረጋገጥ ይገባል።
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዛሬ በተደረገው የመስክ ምልከታ ተግባራቱ በእርግጥም መሬት ላይ ያሉና አርሶአደሩን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።
በዚህም አርሶ አደሩ የዝናብ፣የግብአት እና የነዳጅ እጥረት ሳይበግረው በመስራት በወረዳው አመርቂ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑ አስገንዝበዋል።
በዛሬው የመስክ ጉብኝት በወረዳው በመኸር ወቅት እየለሙ ያሉ የገብስ፣የስንዴ፣የድንች ስራዎች እንዲሁም በበልግ ከለሙ ደግሞ የበቆሎ ማሳ መመልከት መቻሉ ተናግረዋል።
አቶ ሸምሱ አክለውም በዞኑ ኩታገጠም የክላስተር እርሻዎች ልምድ እየሆኑ እንደሚገኝ ጠቁመው በዛሬው እለትም በወረዳው የታየው 40 ሄክታር ኩታገጠም የገብስ እርሻ አንዱ ማሳያ መሆኑን አብራርተዋል።
በወረዳው በተቀናጀ ግብርናና በሌማት ትሩፋት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸው አመላክተው የወተት፣የዶሮ፣የንብ ፣የስጋ፣የቡናና የፍራፍሬ መንደሮች ተመስርተው የአርሶ አደሩ ኑሮ እንዲሻሻል አድርገዋል ብለዋል።
በወረዳው የተጀመሩ ተስፋ ሰጪ ስራዎች በቀጣይ መስፋት እንዳለባቸው በመጠቆም አመራሩ በቁርጠኝነት ከሰራ ለውጥ ሊመጣ እንደሚችል አስገንዝበዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አብድረሂም ርዳ እንደተናገሩት መንግስት የምግብ ሉአላዊነት ለማረጋገጥ እና የማህበረሰቡ ኢኮኖሚዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በግብርና ዘርፉ ላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
በፓርቲው የሚወርዱ በርካታ የግብርና ኢኒሼቲቮች በወረዳው ተግባራዊ እየተደረጉ ሲሆን እነዚህም አመርቂ ስኬት ማስመዝገብ እየቻለ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
አዳዲስ ያልታረሱ መሬቶች በማረስ፣ ባህር ዛፍ በማንሳት ፣እስካሁን ያልተመሩቱ ምርቶች ማምረት እየተቻለ መሆኑን የገለጹት አቶ አብድረሂም በቡናና በፍራፍሬ አበረታች ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል።
አርሶ አደሩ ከእጅ ወደ አፍ የሚሆን ምርት ከማምረት ወጥቶ በሁሉም ዘርፎች በኩታገጠም በማረስና የክላስተር መንደሮች በመመስረት ግብርናውን እንዲያድግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ አብራርተዋል።
የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ በዘንድሮ የመኸር ወቅት እስካሁን 17ሺ 812 ሄክታር መሬት በማልማት 96 ፐርሰንት የደረሰ ሲሆን ከ1ዐሚሊየን 98ሺ ኩንታል ምርት በላይ ይጠበቃል።
አሲዳማ መሬቶቾ በኖራ የማከም ስራ መሰራቱ ጠቅሰው በአሁን ጊዜ ዩሪያ የመስጠት ፣የአረም ቁጥጥርና ኬሚካል የመርጨት ስራ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዲጬ ዲምቱ ቀበሌ የለጉዲ ትሬዲንግ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፣የቡና ችግኝ እያፈላ ለአርሶ አደሮች እየሰጠ ያለው ተግባር አርሶ አደሩን በቡና ልማት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስችሏል ነው ያሉት አቶ ከድ
ነሐሴ 01/2018 ዓ/ም
ምክርቤቱ ለ2019 በጀት ዓመት 67 ቢሊየን ብር በጀት አጸደቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሁለተኛ ቀን ውሎው ለ2019 በጀት ዓመት የቀረበለትን ረቂቅ በጀት ተመልክቶ 67 ቢሊየን ብር በጀት አጽድቋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ታመነ ገብሬ ለምክር ቤቱ የ2019 በጀት አመት ረቂቅ በጀት ለምክር ቤቱ በዝርዝር አቅርበዋል።
በጀቱ ከፌደራል መንግስት ግምጃ ቤት፣ከውጭ እርዳታ እና የዘላቂ ልማት ግቦች 31 ቢሊየን 748 ሚሊየን 169ሺ 478 ብር መሆኑን አቶ ታመነ በማብራሪያቸው ገልጸዋል።
በክልሉ ከመደበኛ ገቢ፣ከመስሪያ ቤቶች የውስጥ ገቢ፣ከጤና ተቋማት ገቢ፣ከማዘጋጃ ቤት እና ከትምህርት ቤቶች ገቢ በጥቅሉ 35 ቢሊየን 251ሚሊየን 830ሺ 522 ብር መሆኑን አቶ ታመነ ጠቁመዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘይቱና ኢብራሂም ለ2019 ዓ/ም ስራ ላይ የሚውል ረቂቅ የበጀት አዋጅ መግለጫ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።
ኃላፊዋ በማብራሪያቸው ባለፉት ዓመታት የኢኮኖሚ እድገት ያለበትን ደረጃ ፣የፊሲካል ፖሊሲ አፈጻጸም፣ድህነትን ለመቀነስ እና የዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የተከናወኑ ተግባራትን እና የተመዘገቡ ውጤቶችን በመገምገም ለ2019 በጀት ዓመት ዋና ዋና የኢኮኖሚ፣የድህነት ቅነሳና የፊሲካል ማዕቀፍ ታሳቢ ያደረገ ዝርዝር መግለጫ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ባለፉት ሶስት ዓመታት የክልሉ ኢኮኖሚ በፍጥነት እንዲቀጥል የሀብት ክፍፍሉ ፍትሀዊ እንዲሆን በአስተዳደር እርከኖች እና ድህነት ቀናሽ ዘርፎች ላይ ትኩረት መደረጉን ኃላፊዋ አብራርተዋል።
በክልሉ የተጀመሩ የልማት ስራዎች በዘላቂነት እንዲቀጥሉ እና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተደረገ ጥረት ለዘመናት ግንባታቸው የተጓተቱ ፕሮጀክቶች እንዲጠናቀቁ እና አዳዲስ ፕሮጀክቶች ተገንብተው አገልግሎት እንዲሰጡ መደረጉን ወ/ሮ ዘይቱና ጠቁመዋል።
ባለፉት ዓመታት በክልሉ ምክር ቤት እየጸደቀ ያለው በጀት በአማካይ የ23 በመቶ እድገት ማሳየቱን ወ/ሮ ዘይቱና በማብራሪያቸው አመላክተዋል።
ሐምሌ 30/2018 ዓ/ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአብይና ቴክኒክ ኮሚቴ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልጎሎት ላይ የተከናወኑ ተግባራትን ግምገማ አካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ አብይና ቴክኒክ ኮሚቴ በዛሬው እለት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልጎሎት የእስካሁን የተከናወኑ ተግባራትን በዝርዝር ገመገመ።
የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ጀማል ናስር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን የኮሚቴ አባላት በጥልቀት ተወያይቶበታል።
የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ኃላፊ እና የአብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አ/ረሂም ረዳ በግምገማው ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት የተመዘገቡት ውጤቶች የህብረተሰቡን ተሳትፎና የበጎ ፈቃደኞችን ትጋት የሚያሳዩ በመሆናቸው በሁሉም ዘርፍ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል።
ለክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች ስኬታማነት የተቋማት ቅንጅታዊ የአሰራር ስርአት መጠቀም አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ የአብይና ቴክኒክ ኮሚቴ የውይይት መድረክ ተጠናክሮ ይቀጥላል በመሰለት በሁሉም የበጎ ዘርፎች የተያዙ እቅዶችን በውጤታማነት ማሳካት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
በግምገማ መድረኩም ከሪፖርት መነሻ በጥንካሬ እና በጉድለት የተለየ ሲሆን የታዩ ክፍተቶችን በቀጣይ ለማስተካከል የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
ሐምሌ 30/2018 ዓ/ም
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የአደጋ ስጋት አመራር የወረዳው አብይ ኮሚቴ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ኢንሼቲቭ ላይ ያተኮረ የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ኢንሼቲቭ የ120 ቀናት 517 ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል።
የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ በሪፖርታቸው፤ ዜጎችን በዘላቂነት ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የታለመው ይህ ኢንሼቲቭ በወረዳው በልዩ ትኩረት እየተገበረ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚሁ መነሻነትም በወረዳው ለአደጋ ጊዜ ዝግጁነትና ምላሽ መስጫ የሚውል 517 ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን በመድረኩ ላይ እንዳሉት በዘርፉ ለአቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎች በሰፊው ተደራሽ ለመሆን ለአደጋ ጊዜ የሚሰበሰበው ምርት ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ገልጸዋል።
በወረዳው ለመሰብሰብ የታቀደው ምርት ሲመጣ ያለ ምንም ብክነት በአግባቡ እንዲቀመጥ የአደጋ ጊዜ እህል መጠባበቂያ መጋዘኖችን አዲስ በመስራትና ያሉትን ደግሞ በመጠገን ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የወረዳው አብይ ኮሚቴ ተግባሩን በቅርበት እንደሚከታተለው ጠቅሰው የወረዳውን የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት እቅድ ለማሳካት ሁሉም ሴክተሮች በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል
የወረዳው የብልፅግና ጽህፈት ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ በበኩላቸው የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ በክረምት በጎ ፍቃድ አካል የሆነው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ኢንሼቲቭ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ መቀጠል እዳለበት አሳስበዋል።
አቶ አ/ረሂም አክለውም የአደጋ ስጋት ያለባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች በትክክል በመለየትና በመደገፍ ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ተጠናክሮ መቀጠሉን የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በዘንድሮ የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት እስከ ሐምሌ 29/2018 ድረስ ከ30 ሺህ በላይ ወጣቶችን በማስተፍ 65 ሺህ በላይ የህብረተሠብ ክፍሎች ማስጠቀም መቻሉን እንዲሁም ከ52 ሚሊዮን ብር በላይ መንግስትና ህብረተሰቡ ሊወጣ ይችል የነበረውን ገንዘብ ማዳን መቻሉን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት አክሎ አስታውቋል።
የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሸምሱ ኢብራሂም የእስካሁን አፈጻጸሙን አስመልክተው እንደገለጹት ወጣቶች በልማትና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ በመሳተፍ ተጠቃሚ ከሚሆኑባቸው መንገዶች አንዱና ዋነኛው የወጣቶች የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ ተጠቃሽ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
የዘንድሮውን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ57 ሺህ 2 መቶ 28 በላይ ወጣቶች በተመረጡ 16 የስምሪት መስኮች ላይ ተሰማርተው መጠነ - ሰፊ እንቅስቃሴ በማድረግ በረካታ ስራዎች መሠራታቸውን አስታውቀዋል።
እስካሁን ያለውን አፈጻጸም አስመልክተው እንዳሉት ከጤና አንፃር 105 ዩኒት ደም ልገሳ ለመሰብሰብ ታቅዶ 97 ዩኒት ደም ለእናቶች መሰብሰብ መቻሉ፣ በተለያዩ ጤና ጣቢያዎች ነጻ ምርመራና የምክር አገልግሎት መሰጠቱን ገልጸው በክረመቱ ከ4.7 ሚሊዮን በላይ ዘርፍ ብዙ ጥቅም ያላቸው ችግኞች በወጣቶች መተከላቸውን ፣ 95 ቶን ቆሻሻ በከተሞች መወገዱን አንስተዋል።
ከማህበረሰብ ድጋፍና እንክብካቤ አኳያ 19 ቤቶችን ጠግኖ በማደስ አቅመ-ደካማ አረጋውያንን ከብርድና ከዝናብ መታደግ ስለመቻሉ ጠቅሰው 39 አዲስ ቤቶች በመንግስትና በህብረተሠብ ተሳትፎ እየተገናቡ ሲሆን 7 ቤቶች መጠናቀቃቸውም ገልጸው ከዚህ ውስጥ 3 ቤት የዘማች ቤተሠብ መሆኑን ተናግረዋል።
አቶ ሸምሱ አክለውም 380 ተማሪዎች የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት እየወሠዱ ሲሆን 95 ተማሪዎች መሠረታዊ የኮምፒውተር ስልጠና መውሠዳቸውን ገልጸዋል።
6 አዲስ አንስተኛ መሸጋገሪያ የእንጨት ድልድዮች የተገነቡ ሲሆን 9 የእንጨት ድልድዮች መጠገናቸውን ገልጸው 18.5 ኪሎ ሜትር የመንገድ ዳር ቦይ ከፈታ ስራዎች በበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተሰርተዋል በተጨማሪም በትምህርት ፣ በምግብ ዋስትናና የግብርና ልማት እንዲሁም የመንገድ ደህንነትና ትራፊክ አገልግሎት፣ ስራ አጥ ወጣቶች ልየታን ጨምሮ በስፖርት መስኮች አበረታች እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሚገኝ ጠቅሰው በአንፃሩ የሃብት አሰባሰብ ተግባር ጉድለቶች በቀጣይ ወስዶ መቅረፍ እንደሚገባ የገለጹት አቶ ሸምሱ የበጎ ፈቃድ የዘወትር ተግባርና ልምድ ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚገባና የመደጋገፍና መረዳዳት ባህላችንን አጠናክረን ማስቀጠል ይኖርብናል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
አቶ ሸምሱ በመጨረሻም እንደገለጹት እስካሁን በዘንድሮ የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት 30 ሺህ 6 መቶ 70 በላይ ወጣቶች በበጎ ፈቃድ ስራዎች ላይ በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ 65 ሺህ 964 የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ በማድረግ ከ52 ሚሊዮን 195 ሺህ 678 ብር መንግስትና ህብረተሰቡ ሊወጣ ይችል የነበረውን ገንዘብ ማዳን ተችሏል ሲል የዘገበው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ መንግስት ኮ/ጉ/ፅ/ቤት ነው።
ሐምሌ 28/2018 ዓ.ም
የገጠር ኮሪደር ልማት አርሶ አደሩ በቤተሰብ ደረጃ ህይወቱን እና የአኗኗር ዘዬውን እንዲቀየር ማድረግ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ሚፍታ ሁሴን ገለጹ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በጎምራ ቀበሌ የገጠር ኮሊደር ልማት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በፈንጀሌ ማዕከል ተካሂዷል።
በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ሚፍታ ሁሴን የገጠር ኮሪደር ልማት አርሶ አደሩ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚና ዘመናዊነትን እንዲከተል የሚያደርግ ተግባር ስለሆነ የጎምራ ቀበሌ ማህበረሰብ ባህሉንና ወጉን ጠብቆ አካባቢውን ንጹህ በማድረግ፣ ጓሮውን በዶሮ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ እንዲሁም በማርና ወተት ምርት በማድረግ የገጠር ኮሪደር ልማቱ ቀላል የአኗኗር ስልት እንዲከተሉ አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥርለት ገልጸዋል።
አቶ ሚፍታ አክለው የገጠር ኮሪደር ልማት የፓርቲያችን ኢንሼቲቭ በመሆኑ የዘመናዊነት አኗኗርን ከከተማ ወደ ገጠር በማውረድ የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ ለመቀየር ከፍተኛ ሚና እንዳለው በመግለፅ በተለይም የገጠር መንደሮችን በማዘመን ለአርሶ አደሮች ምቹ የመኖሪያ አካባቢን መፍጠር እንደሚገባ አመላክተዋል።
በወረዳው የገጠር የልማት ኮሪደርን ተግባራዊ ለማድረግ በወረዳው ያሉ መልካም አጋጣሚዎችን አሟጦ በመጠቀም ስራውን በፍጥነት እና በጥራት ማከናወን እንደሚገባም ተናግረዋል።
የገጠር የልማት ኮሪደርን ተግባራዊ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ለማከናወን ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ በቀጣይ ጊዚያት ስራውን በተሟላ መንገድ አስጀመሮ ለማጠናቀቅ በተቀናጀ እና በተናበበ መንገድ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በጎምራ ቀበሌ በፈንጀሌ እስኬጅ ማዕከል በተመረጡ 10 ሞዴሎች በዛሬው እለት የታወጀ ሲሆን ተግባሩ በሌሎች በተመረጡ እስኬጅ ማአከላት የሚቀጥል መሆኑ ተመላክቷል።
በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳደሪ አቶ ሚፍታ ሁሴንን ጨምሮ የአስተባባሪ አካላት የጎምራ ቀበሌ ደጋፊ አመራር እና የከተማ ልማት ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
ሐምሌ 28/2018 ዓ.ም
"ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ደሳ ቀበሌ ከ10 ሄክታር በላይ በክላስተር በተዘጋጀ መሬት ላይ የመኸር የስንዴ ዘር መዝራት ተጀምሯል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
"ከረጂነት ወደ ምርታማነት "በሚል መሪ ሃሳብ በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ደሳ ቀበሌ ከ10 ሄክታር በላይ በክላስተር በተዘጋጀ መሬት ላይ ለአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ የሚሆን የስንዴ ዘር መዝራት ተጀምሯል።
በክላስተር በተዘጋጀ መሬት ላይ ለአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ የሚሆን ስንዴ እየተዘራ ያለው በወረዳው መንግስት በጀት መሆኑ ተመላክቷል።
በዕለቱ የመኸር ስንዴ ዘር ማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ የወረዳው ዋና አስተዳደሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣ የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳን ጨምሮ የአስተባባሪ አካላት እንዲሁም የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ በመገኘት አስጀምረዋል።
ሐምሌ 28/2018 ዓ/ም
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ አካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ጽ/ቤቱ የ2018 በጀት ዓመት የ4ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርትን፣ የዜጎች ቻርተር እና የህዝብ ክንፍ አባላት በተገኙበት በዛሬው እለት የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱ በጽ/ቤቱ የልማት እቅድ ባለሙያ በአቶ ኤሊያስ ለማ አማካይነት የቀረበ ሲሆን፣ በሪፖርቱ ላይ የተከናወኑ ዋና ዋና የፋይናንስና የልማት ተግባራት ዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የወረዳው ፋይናንስ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ እና የበጀት ክፍል አስተባባሪ የሆኑት አቶ መኪ ሃይደር በመድረኩ ተገኝተው እንዳሉት ተቋማት በጀትን በአክሽን ፕላን መመራት እንዳለባቸው ጠቅሰው፣ ለዕቅዶች መሳካት የገቢ እቅድ አፈፃፀምን ከፍ ማድረግ እና የኦዲት ግኝቶችን ማስመለስ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።
አክለውም አቶ መኪ ሃይደር ቀልጣፋና ግልፀኝነት የተላበሰ የፋይናንስ ስርዓትን በማስፈን የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፣ የልማት እቅድ ባለሙያዎች የመንግስት በጀት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አሳስበዋል።
የወረዳው ፋይናንስ ጽ/ቤት የስነ ምግባር ኦፊሰር የሆኑት አቶ ናስር ጫካ በበኩላቸው የደረሰኝ ስርጭትና አመላለስ ላይ ያሉ ጉድለቶች ተስተካክለው በ2019 በጀት አመት መረጃዎች በጥራትና በጊዜ የደሞዝ፣የስራ ማስኬጃ ለሚገዙ እቃዎች በመለየት የተጣራ መረጃ በጊዜ ተቋማት ማድረስ እንዳለባቸው አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
በመድረኩ ላይ የተቋማት የሰው ሃብቶች እና የልማት እቅድ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
