912
Subscribers
-124 hours
+37 days
-730 days
Posts Archive
ነሐሴ 08/2018 ዓ/ም
የገጠር ኮሪደር ልማት እሳቤን ተግባራዊ በማድረጋቸው የአኗኗር ዘይቤያቸው ከመቀየሩ ባለፈ ተጠቃሚ መሆናቸውን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ያነጋገርናቸው አርሶ አደሮች ተናገሩ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በወረዳው የወለጋ ደሴ ቀበሌ ደበሌ መንደና የጎምራ ቀበሌ የገጠር ኮሪደር ልማት ስራን ምልከታ ተደርጎባቸዋል።
በገጠር ኮሪደር ልማት ውጤታማ ስራ ለመስራት ቅንጅታዊ አስራሮች ተግባራዊ እየተደሩ እንደሆነ ተመላክቷል።
የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አብድረሂም ርዳ በበኩላቸው በገጠር ኮሪደር የገጠሩን ማኅበረሰብ የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ያለመ በመሆኑ የወረዳውን ህብረተሰብ ኑሮ ለማሻሻል ሞዴለ መንደሮችን በመምረጥ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በገጠር ኮሪደር ልማት የመንደሮችን ጽዳትና ውበቱ እንዲጠበቅ ብቻ ሳይሆን ድህነት በመቀነስ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ያነሱት አቶ አብድረሂም ለዚህም ስነምህዳሩ ታሳቢ ያደረጉ በአትክልትና ፍራፍሬና በእንሳት ዘርፍ አርሶአደሮች የተሻሻሉ ዝርያዎች እንዲኖራቸው እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ይህም አርሶ አደሩ በምግብ ራሱ እንዲችል፣ የተመጣጠነ የአመጋገብ ስርአት እንዲኖረው ከኮሪደር ልማቱ በማስተሳሰር እየተሰራ ነው ያሉት።
አክለውም በኮሪደሩ የሰውና የእንሰሳት ቤት እንዲለይ፣ መጸዳጃ ቤት እንዲኖር፣ መብራት የሌለባቸው አካባቢዎች የሶላር ተጠቃሚ ለማድረግና የአኗኗር ስርአቱ የተስተካከለ እንዲሆን እየተሰራ ያለው ስራ በተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል።
በወረዳው የሚገኙ ሞዴል አርሶአደሮችን በመለየት በወረዳው በተመረጡ አካባቢዎች ሞዴል መንደር እንዲመሰርቱ የግንባታ ስራዎች መጀመሩንም ጠቁመዋል።
በቀጣይ የአካባቢ ተወላጅ ባለሀብቶችን በማስተባበር ወረዳውን ወደ ተሻለች ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ ወረዳው እንደሚሰራ ገልጸዋል።
አርሶአደር ሰይድ ያሲኖና እቴነሽ ቱሉ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የወለጋ ደሴና የጎምራ ቀበሌ ነዋሪዎች ሲሆኑ በገጠር ኮሪደር ልማት ራሳቸውንና አካባቢያቸውን ጽዱ በማድረግ ጤናቸውን በተገቢው እየጠበቁ መሆናቸውን አስረድተዋል።
በገጠር ኮሪደር በተሠራው ቤት የሚያረቡትን የቤት እንስሳት በልዩ ሁኔታ በመንከባከብ የተሻለ ኑሮ እየኖሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ነሐሴ 07/2018 ዓ/ም
የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ እየተሰራ እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ አስታውቋል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
መምሪያው በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ መሃልአምባ ከተማን ጨምሮ በስድስቱም ማዘጋጃ ቤቶች እየተሰሩ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን የመስክ ጉብኝት እያደረገ ይገኛል።
በወረዳው ከሚገኙ የማዘጋጃ ከተሞች አንዱ የሆነው የኮምበል ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሲሆን በከተማው የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት በመንግስት በባለሀብትና በህብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰራ የሚገኘው የመዋዕለ ህጻናት ትምህርት ቤት ከ6.5 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ እንደሚገኝ ተመላክቷል።
ሌላው የከተማውን የህብረተሰብ ክፍልና አጎራባች አካባቢዎችን ተጠቃሚ የሚያደርገውን የ3.5 ኪሜ የመብራት ዝርጋት የአካባቢውን ተወላጅ ባለሀብቶችን በማሳተፍ እየተሰራ የሚገኝ ሲሆን ሲጠናቀቅ የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ይፈታል ተብሏል።
በፕሮግራሙ በወረዳው የሚደረጉ የገጠር ኮሪደር ስራና ሞዴል የገጠር መንደር ምስረታ እንቅስቃሴም ይታያል ተብሎ ይጠበቃል።
በመስክ ምልከታው የጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትብለጥ እስጢፋኖስ ፣የጉራጌ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብድረሂም ርዳ ጨምሮ የዞንና የወረዳ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛል።
ነሐሴ 06/2018 ዓ/ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰው ተኮር የሆኑ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ የስራ መስኮች ተጠናክረው ቀጥለዋል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በወረዳው አመቶ፣ቀቻ እና ዋቦን ቀበሌዎች ነዋሪ ለሆኑት 3 አቅመ-ደካማ አረጋውያን ለእያንዳዳቸው 40 ቆርቆሮና 2 ፓኬት ሚስማር በአጠቃላይ በእለቱ 120 ቆርቆሮና 6 ፓኬት ሚስማር ድጋፍ ተደርጓል።
በወረዳው "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ እና የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ጀማል ናስር በጋራ በመሆን ለአቅመ ደካማ አረጋዊያን የቆርቆሮና ሚስምር በአካል በመገኘት ድጋፍ አድርገዋል።
ነሐሴ 05/2018 ዓ/ም
በ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፍቃድ በከሲብ ማራንቶ ቀበሌ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ከመንግስት ከህብረተሰቡ እና ከባለሀብት በማሰባሰብ የተለያዩ በጎ አድራጎት ተግባራት እየተከናወነ ይገኛል።
፨፨፨፨፨፨፨//፨፨፨፨፨፨
በገደባኖ ጉታዘር በወረዳው ከሲብማራንቶ ቀበሌ ነዋሪ ለሆኑት 2 አቅመ-ደካማ አረጋውያን ለእያንዳዳቸው 40 ቆርቆሮና 2 ፓኬት ሚስማር በአጠቃላይ በዛሬው እለት 80 ቆርቆሮና 4 ፓኬት ሚስማር ድጋፍ የተደረገ ሲሆን ጠቅላላው ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን 110 ሺህ ብር የሚያወጣ መሆኑ ተገልጿል ።
በድጋፍ ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የከሲብ ማራቶን ቀበሌ አስተዳደር አቶ አረቦ ኡርጂ እንደተናገሩት በ2018 ዓ.ም የክርምት በጎ ፍቃድ በከሲብ ማራንቶቀበሌ ነዋሪዎች ፣በባለሀብቶችና በመንግስት ሀብት በማሰባሰብ በቀበሌው 6 አዳዲስ አረጋውያን የመኖሪያ ቤት ግንባታ መጀመሩን ገልፀው በዛሬው ዕለት ባቦ ልማት ቡደን ለወ/ሮ ረዲቱ አትርሳ እና አውራ ልማት ቡድን አቅመ ደካማ ለሆኑት አትርሳ ጆቢር ለእያንዳንዳቸው 40 ቆርቆሮና 2 ካርቶን ሚስማር ድጋፍ ከወረዳው መንግስት ድጋፍ መደረጉን አብራርተዋል።
አቶ አረቦ አክለውም በዘንድሮ በጎ ፍቃድ ከአዲስ ቤት ግንባታ በተጨማሪ 4 ቤቶች መታደሳቸው 2 አዳዲስ የእንጨት ድልድይ እንደተሰራ፣ወጣቱን በማስተባበር ከ40ሺ ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ ዶዘር በመከራየት 4.5ኪ.ሜ የመንገድ ቦይ ከፈታ መደረጉን ፣15ሄክታር የአቅመ ደካማ አረጋውያን መሬት የመኸር ዘር መዘራቱን ገልፀው በ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፍቃድ በአጠቃላይ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ከመንግሥት ከህብረተሰቡ ተሳትፎና ከባለሀብት በማሰባሰብ በቀበሌው የተለያዩ በጎ አድራጎት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ሚፍታ ሁሴን፣ የት/ቤቶች ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ኬኔ ጨምሮ የወረዳ አመራሮችና የቀበሌው አመራሮች በመገኘት ለአቅመ ደካማ የቆርቆሮና ሚስማር ድጋፍ አድርገዋል።
ነሐሴ 05/2018 ዓ/ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የገደባኖ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት በክረምት በጎ ፍቃድ መርሃ ግብር ለአቅመ ደካማ ተማሪዎች የሚሆን የ32 ደርዘን ደብተር ድጋፍ ተድርጓል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የገደባኖ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት በክረምት በጎ ፍቃድ መርሃ ግብር ለአቅመ ደካማ ተማሪዎች የሚሆን የ32 ደርዘን ደብተር ድጋፍ የተደረገ ሲሆን
ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን ከ26,500 ብር በላይ መሆኑ ተመላክቷል።
በርክክቡ ወቅት ተገኝተው ድጋፉን የተረከቡት የወረዳው የወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሸምሱ ኢብራሂም ህብረቱ ለአቅመ ደካማ ወገኖቻችን ላደረገው ትልቅ አጋርነት እና በጎ ተግባር በፅህፈት ቤቱ ስም ከፍተኛ ምስጋና በማቅረብ
መሰል መልካም ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል።
ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በክረምት በጎ እቃድ ለአቅመ-ደካማ አረጋውያን የቆርቆሮና ሚስማር ደጋፍ ተደረገ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በወረዳው ዘልዋን ሰፋቶ እና መሀል ጉታዘር ቀበሌዎች ነዋሪ ለሆኑት 2 አቅመ-ደካማ አረጋውያን ለእያንዳዳቸው 40 ቆርቆሮና 2 ፓኬት ሚስማር በአጠቃላይ በእለቱ 80 ቆርቆሮና 4 ፓኬት ሚስማር ድጋፍ ተደርጓል።
በወረዳው "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪና ፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሚፋታ አረቦ፣የወረዳው አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አ/በር አብራር እና የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ጀማል ናስር በጋራ በመሆን ለአቅመ ደካማ አረጋዊያን የቆርቆሮና ሚስምር በአካል በመገኘት ድጋፍ አድርገዋል።
ነሐሴ 04/2018 ዓ/ም
በአረቅጥ ሀይቅ መልክአምድራዊ የመሬት ገጽታዎች አሳታፊና የተቀናጀ የመሬት አጠቃቀም ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት የተፈጥሮ ሀብቶችን በዘላቂነት በመጠበቅና መንከባከብ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ኤጀንሲ አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኤጀንሲ Giz አለም አቀፍ የልማት ትብብር ድርጅት ጋር በመተባበር በአረቅጥ ሀይቅ እና ዙርያ መልካም ምድር ገፅታ ላይ አሳታፊ የተቀናጀ የመሬት አጠቃቀም ዕቅድን በተመለከተ ክልላዊ የግንዛቤ ፈጠራ ወይይት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የውይይት መድረክ እተካሄደ ነው።
የክልሉ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ኤጀንሲ ስራአስኪያጅ አቶ አብዱልሃፊዝ ሁሴን መድረኩን በንግግር ባስጀመሩበት ወቅት "የመሬት ገጽታችን የተፈጥሮ ሀብታችን ህልውና እና መሰረት ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
በተለይም የአረቅጥ ሐይቅ ለአካባቢው ተፋሰስ እና ማህበረሰብ የህይወት ምንጭ፣ ለግብርና እና እንስሳት እርባታ ወሳኝ የውሃ አቅርቦት የሚሰጥ፣ የብዙሃን ህይወት መጠለያ እና የአካባቢው የስነ-ምህዳር ሚዛን ጠብቆ የቆየ ታላቅ ተፈጥሮአዊ እና ኢኮኖሚያዊ ሀብት መሆኑን ተናግረዋል።
ሐይቁ ለአካባቢው ውበት እና የልማት እምቅ አቅም ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድም መተላለፍ ያለበት ውድ ቅርስ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
ይህን የተፈጥሮ ሀብት የሆነውን ሐይቅ እና ተፋሰስ በዘላቂነት መጠበቅ ካልተቻለ፣ የተቀናጀ የመሬት አጠቃቀም ተግባራዊ ካልተደረገ የአካባቢው በአፈር መሸርሸር፣ በደለል ክምችት፣ በውሃ ብክለት እና በከብቶች ማደሪያ ማጣት ምክንያት ህልውናው አደጋ ላይ ሊወድቅ የሚችልባቸው በርካታ አጋጣሚዎች እንደሚኖሩ ተናግረዋል።
ይህን ውድ የተፈጥሮ ሀብታ መታደግ እና የአካባቢው ማህበረሰብ ኑሮ ማሻሻል ለአንድ ተቋም ብቻ የሚተው ኃላፊነት ሊሆን አይችልም ሲሉ አቶ አብዱሃፊዝ ተናግረዋል።
በመሆኑም በክልሉ ሁለት ወሳኝ የመሬት ገጽታዎች (Critical Landscapes ) ማለትም በአምበሪቾ እና በአረቅጥ ተፋሰስ አካባቢ የተጀመረው አሳታፊ የመሬት አጠቃቀም እቅድ ዝግጅት የመሬት እና የውሃ ሀብታችን ከባህላዊ አሰራር ወጥተን በሳይንሳዊ እና አቃፊ በሆነ መልኩ ዘላቂ መንገድ ለመምራት የተያዘ ትልቅ ራዕይ መሆኑን ስራ አስከያጁ ተናግረዋል።
የመሬት አጠቃቀም እቅድ የግብርና፣ የውሃ፣ የደን እና የዱር አራዊት ጥበቃ፣ የማዕድን እና የኢንቨስትመንት ዘርፎችን በጥምረት የሚያስተናግድ የጋራ መድረክ ነው ብለዋል።
በዚህ ውይይት በአረቂጥ ወሳኝ የመሬት ገጽታ የሚታዩ የሀብት አጠቃቀም፣ የልማት እድሎች እና የአካባቢ ስጋቶችን በጋራ በመገምገም የአካባቢው ማህበረሰብ ያከማቸው ባህላዊ እውቀት እና ልምድ፣ በተለይም የሴቶች እና ወጣቶች ድምፅ እና ተሳትፎ የእቅዱ አካል የሚሆኑባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አቶ አብዱልሃፊዝ አክለዋል።
ለውጤታማነቱም ሁሉም በሐይቁ ዙሪያ ያሉት ባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ በመሆኑ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉም ዋና ሥራአስኪያጁ ጥሪ አቅርበዋል።
GIZ አለም አቀፍ የልማት ድርጅት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሁለት ዞኖች አሳታፊ እና የተቀናጀ የመሬት አጠቃቀም ዝግጅት ፕሮጀክት ከባለፈው ዓመት ጀምሮ እየሰራ መሆኑን በGiz አለም አቀፍ የልማት ድርጅት የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል አስተባባሪ አቶ አንተነህ ወንድሙ ተናግረዋል።
በዚህ የምክክር መድረክ በዋናነት በአረቅጥ ሀይቅ አሳታፊ እና የተቀናጀ የመሬት አጠቃቀም መሬት ዝግጅት ፕሮጀክት ላይ የጋራ የሆነ ግንዛቤ እንዲኖርና መልካም አጋጣሚዎች፣ ስጋቶች እና በቀጣይ ለሚሰሩ ስራዎች ግብአት ለመውሰድ መሆኑን ገልፀዋል።
የክልሉ መንግስት ግብርና ቢሮ
ነሐሴ 03/2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በቤደር ቀበሌ በክረምት በጎ ፍቃድ ለአንድ አቅመ ደካማ ቤተሰብ የተገነባው የመኖሪያ ቤት በማየት ፍራሽና ብርድ ልብስ ድጋፍ ተደረገ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በቤደር ቀበሌ ለአንድ አቅመ ደካማ ቤተሰብ የተገነባው የመኖሪያ ቤት የደረሰበት በማየት ፍራሽ፣ ብርድ ልብስ እና የመሬት ወለል መንጣፍ ድጋፍ ተደርጓል።
በወረዳው የዘንድሮው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ57 ሺህ 2 መቶ 28 በላይ ወጣቶች በተመረጡ 16 የስምሪት መስኮች ላይ ተሰማርተው መጠነ - ሰፊ እንቅስቃሴ በማድረግ በረካታ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣ የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪና ፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሚፋታ አረቦ፣ የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጠይብ አስፍር፣ የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ጀማል ናስርና ባለድርሻ ተገኝተው ድጋፉን አበርክተዋል።
ነሐሴ 03/2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በቦኔ ቀበሌ ቀጠሮ መንደር አቮካዶ ልማት በክላስተር ተካላ ተካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ኢንሼቲቭ አካል የሆነው የአቮካዶ ልማት ክላስተር በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ቦኔ ቀበሌ ቀጠሮ መንደር ተመሰረተ።
በወረዳው በተለያዩ 10 ቀበሌዎች የ30-40-30 የፍራፍሬ መንደር ለመመስራት ታቅዶ እየተሰራ ሲሆን በዛሬው እለትም 500 የአቮካዶ ዝርያ በቦኔ ቀበሌ ቀጠሮ መንደር ተተክሏል።
በተካላው ፕሮግራም ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን፣ የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪና ፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሚፋታ አረቦ፣የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጠይብ አስፍር፣ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋና እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
