912
Subscribers
+124 hours
+47 days
-430 days
Posts Archive
ነሐሴ 14/2018 ዓ/ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የአበዘት ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀሙን የቦርድ አባላት በተገኙበት ገመገመ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በመድረኩ ላይ የጤና ጣቢያው ኃላፊ አቶ በሀሩ ወኬኔ የሩብ ዓመቱን የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለቦርድ አባላት ያቀረቡ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይት ተደርጎበታል።
ከውይይቱ አስቀድሞ የጤና ጣቢያው የቦርድ አባላት በጤና ጣቢያው ውስጥ ያሉትን ልዩ ልዩ የሕክምና ግብዓቶች፣ለእናቶች ማረፊያ የተዘራ የገብስ ማሳ፣አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴዎችና የአገልግሎት ክፍሎችን በመንቀሳቀስ ተመልክተዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪና የጤና ጣቢያው የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሚፍታ ሁሴን በውይይቱ ላይ እንደገለጹት ማኅበረሰቡን በጤናው ዘርፍ ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግና የጤና ተቋማትን ውጤታማነት ለማረጋገጥ በተቋሙ ውስጥ ያለውን የሰው ኃይል በአግባቡ መጠቀም ያስፈልጋል ብለዋል።
ጤና ጣቢያውን ወደ ላቀ ደረጃ ሊያሻግሩ የሚችሉ አዳዲስ አሠራሮችን መፍጠርና የአገልግሎት አሰጣጥን በየጊዜው ማሻሻል እንደሚገባም አሳስበዋል።
በመድረኩ ላይ የተሳተፉት የቦርድ አባላት በበኩላቸው፣ የጤና ጣቢያውን የውስጥ ገቢ በማሳደግ ተቋሙን ማጠናከርና አገልግሎቶችን ማስፋት እንደሚገባ ጠቁመው የባለሙያዎች የአገልግሎት አሰጣጥ ጉድለቶች ማስተካከል እንደሚገባ አሳስበዋል።
በማጠቃለያው በጤና ጣቢያው የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ላይ የታዩ ጥንካሬዎችና ጉድለቶችን በዝርዝር በመለየት ጥልቅ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ በቀጣይ መስተካከል በሚገባቸው አቅጣጫዎች ላይ የጋራ መግባባት ላይ በመደረስ መድረኩ በስኬት ተጠናቋል።
ነሐሴ 14/2018 ዓ/ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰው ተኮር የሆኑ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ የስራ መስኮች ተጠናክረው ቀጥሏል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በወረዳው ደነብ ቀበሌ ነዋሪ ለሆኑት አቅመ-ደካማ አቶ አምደላ አህመድ 40 ቆርቆሮና 2 ፓኬት ሚስማር ድጋፍ ተደረገ።
በወረዳው "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሸምሱ ኢብራሂም ለአቅመ ደካማ አረጋዊያን የቆርቆሮና ሚስምር በአካል በመገኘት ድጋፍ አድርገዋል።
ነሐሴ 14/2018 ዓ/ም
በወረዳው በኢንቨስትመንት ዘርፍ የተጀማመሩ ስራዎችን በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት ይሰራል:- አቶ ሚፍታ ሁሴን
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የዞን ደጋፊ አመራርና የወረዳው የስራ ኃላፊዎች የሀጂ ለገሰ ሸረፋ አበባ እርሻ ልማት እንቅስቃሴ የመስክ ምልከታ አድርገዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን እንዳሉት በወረዳው ከዚህ ቀደም በኢንቨስትመንት ዘርፍ ብዙም ልምድ እንዳልነበረ ጠቅሰው አሁን ላይ በዘርፉ ጥሩ መነቃቃት ተፈጥሯል።
በዘርፉ በቡናና በአበባ እርሻ ልማት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆኑን አንስተው፤ በዚህም በወረዳው በቡና የተሰማራው ለጉዲ ትሬዲንግ የቡና ልማት ኢንቨስትመንት ጥራት ያለው የቡና ምርት በማምረት ለውጭ ገበያ እያቀረበ መሆኑንም አመላክተዋል።
በዚህም ኢንቨትመንቱ ከ360 ሄክታር መሬት በላይ በመውሰድ ከ2 መቶ ሄክታር በላይ በሆነው እያለማበት መሆኑንም ተናግረዋል።
ሌላው ኤለ ኤል ኤስ አበባ እርሻ ልማት በወረዳው የኢንቨስትመንት ፍቃድ ወስዶ ወደ ተግባር በመግባት ጥራት ያለው አበባ በማምረት ወደ ውጭ ሀገር እየላከ መሆኑን ጠቁመዋል።
እርሻ ልማቱ ለበርካታ ዜጎች በቋሚነት የስራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ ለመንግስት ከፍተኛ ግብር እንደሚከፍልም ገልጸዋል።
ድርጅቱ አሁን እየሰራው ያለው ስራ በይበልጥ ለማስፋት በሚደረገው ጥረት የወረዳው መንግስት አስፈላጊውን እገዛ እያደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።
ከዚህም ባለፈ በወረዳው በሰብል ልማት፣ በቡናና በሌሎችም ዘርፎች የኢቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ተግባር የገቡ እንዳሉ ያነሱት ዋና አስተዳዳሪው ይህ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስገንዝበዋል።
ወረዳው ሰፊ የሚለማ መሬት፣ ምቹ የአየር ንብረት፣ እንግዳ ተቀባይ ማህበረሰብና በርካታ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራ መገኛ በመሆኑ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ያደርገዋል ብለዋል።
ይህንን ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም በወረዳው በተለይም በቡና ልማት፣ በሰብል፣ በኢንደስትሪ፣ በሆቴልና በሌሎችም ዘርፎች መሰማራት ለሚፈልጉ አካላት የወረዳው መንግስት በሩን ክፍት አድርጎ የሚቀበል መሆኑን ያነሱት አቶ ሚፍታ ለዚህም ባለሀብቶች ወደ ወረዳው መጥታችሁ ኢንቨስት እንድታደርጉ ጥሪውን አቅርቧል።
የኤች ኤል ኤስ አበባ እርሻ ልማት ስራ አስኪያጅ አቶ አክሊሉ አሰፋ በበኩላቸው እርሻ ልማቱ በወረዳው 36 ሄክታር መሬት በመረከብ 11 ነጥብ 5 ሄክታር መሬቱ በአንድ አመት ውስጥ ወደ ተግባር ገብቷል።
እርሻ ልማቱ መሬት ተረክቦ ወደ ተግባር ከገባ አንድ አመት እንዳስቆጠረ ያነሱት ስራ አስኪያጁ በዚህም በአመት 24 ሚሊዮን የአበባ ዘንግ ወደ ውጭ እንደሚልክም ተናግረዋል።
አክለውም በእርሻ ልማቱ 76 አይነት የአበባ ዝርያ እንደሚመረት አመላክተው፤ ለ4መቶ 65 ዜጎች በቋሚነት የስራ ዕድል መፍጠሩንም ገልጸዋል።
አበባ ልማቱ 1ነጥብ 5 ቢሊዮን ካፒታል ማስመዝገብ መቻሉን ያነሱት አቶ አክሊሉ ይህም አበባ በጥራት በማምረት ለውጭ ሀገር እንደሚልክም ጠቁመዋል።
ድርጅቱ በኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰደው መሬት ሙሉ ለሙሉ ለማልማት እቅድ እንዳለው ጠቁመው፤ ለዚህም ማነቆ የሆኑ ጉዳዮችን ከወረዳው መንግስት ጋር በመሆን ለመፍታት እየተሰራ መሆኑንም አመላክተዋል።
በእርሻ ልማቱ የስራ ዕድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል ወይዘሮ ባህርነሽ ወዳጄና ወጣት ቃለአብ ሳህሌ ይገኙበታል።
በጋራ በሰጡት አስተያየት ከዚህ ቀደም ስራ አጥ እንደነበሩ አንስተው በእርሻ ልማቱ ተቀጥረው መስራት ከጀመሩ ወዲህ ባገኙት ገቢ ራሳቸውና ቤተሰቦቻቸው መምራት መጀመራቸውን ገልጸዋል።
ከዚህም ባለፈ ድርጅቱ ለበርካታ ጓደኞቻቸው የስራ ዕድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።
ነሐሴ14/2018 ዓ.ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ቴክኒክ ኮሚቴ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልጎሎት ላይ የተከናወኑ ተግባራትን ግምገማ አካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የበጎ ፍቃድ ቴክኒክ ኮሚቴ የእስካሁን የክረምት የበጎ ፍቃድ ስራዎች ገምግሟል የበጎ ፍቃድ ቴክኒክ ኮሚቴ በንቅናቄው የተጀመረው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች አበረታች ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑ ተመላክቷል።
የበጎ ፍቃድ ቴክኒክ ኮሚቴ አባላት በተቋሞች የተከናወኑ ተግባር ሪፖርት ቀርቦ ግምገማ ተደርጓል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ረዳት የመንግስት ተጠሪ እና የበጎ ፍቃድ የቴክኒክ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሚፍታ አረቦ በግምገማው ላይእንደገለፁት፣ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮች በመቅረፍ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ገልፀው የበጎ ፈቃድ ስራ የመንግስትን እና የማህበረሰቡን ወጪ ከመቀነሱም በላይ የህብረተሰቡን የእርስ በርስ የመረዳዳት ባህልን እያጠናከረ መሆኑን ተናግረዋል።
የወረዳው ወጣቶች ስፖርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ጀማል ናስር በበኩላቸው በቀጣይም የተጀመሩ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል የቴክኒክ ኮሚቴው ቅንጅታዊ አሰራርን ማሳደግ እና የወጣቶችን ተሳትፎ በላቀ ደረጃ ማሳደግ እንደሚገባ ጠቅሰው የክረምት የዜጎች በጎ ፍቃድ የታቀደው እቅድ ውጤታማ እንድሆን ቅንጅታዊ አሰራሩ ሊጠናከር እንደሚገባም አሳስበዋል።
ነሐሴ 13/2018 ዓ/ም
በወረዳው በተቀናጀ የግብርና ልማት የህብረተሰቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው:- አቶ ሚፍታ ሁሴን
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የዞን ደጋፊ አመራርና የወረዳው የስራ ኃላፊዎች የግብርናና ሌሎችም ወቅታዊ የልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ አካሂደዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን እንዳሉት በወረዳው በመኸር እርሻ ልማት 17ሺ 814 ሄክታር መሬት በገብስ፣ በስንዴ፣ በመኸር ድንች፣ በባቄላ፣ በአተርና በጤፍ በዘር መሸፈን ተችሏል።
በመኸር ከለማው ማሳ ውስጥ ስንዴ፣ ጤፍና ገብስ በሰፊው በክላስተር መልማቱንም አንስተው፤ ይህም በወረዳው በክላስተር የማልማት ዘዴ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል ብለዋል።
ወረዳው በግብርና ልማት ዘርፍ እምቅ አቅም እንዳለ ያነሱት አቶ ሚፍታ በዚህም የየአካባቢው ስነምህዳር መሰረት ባደረገ መልኩ በዘንድሮ የመኸር ወቅት በአርሶ አደር ማሳ፣ በመንግስት፣ በእምነት ተቋማት፣ በተደራጁ ህብራት ስራ ማህበራትና በወጣቶች መልማቱንም ተናግረዋል።
ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እርሻ በወቅቱ ከማረስ ባለፈ ግብአት በአግባቡ በመጠቀም ዘር መዝራት መቻሉን ጠቅሰው፤ በቀጣይ የማሳ እንክብካቤ በትኩረት ይሰራልም ብለዋል።
በወረዳው በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ8 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን መትከል መቻሉን አውስተዋል።
አክለውም የቡና መንደር ከመመስረት ባለፈ 30-40-30 የፍራፍሬ መንደር በመፍጠር አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በወረዳው በዘንድሮ አመት ከዚህ ቀደም ታርሰው የማይታወቁ ከ4 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ አዳዲስ ማሳዎችን በማረስ በሰብልና ፍራፍሬ መተካት መቻሉንም አስረድተዋል።
በሌማት ትሩፋት የወተት፣ የዶሮ፣ የስጋ፣ የማር መንደር በመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ በዚህም ወጣቱና አርሶ አርሶ በወተት፣ በዶሮ እርባታ፣ በድለባና በንብ ማነብ በመሰማራት ከምግብ ፍጆቻ አልፈው ኢኮኖሚያዊ ጠቃሚ እየሆኑ መሆኑንም አመላክተዋል።
በወረዳው በተቀናጀ የግብርና ልማት የተጀማመሩ ስራዎችን ይበልጥ በማጠናከር የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።
አቶ መሀመድ ያሲንና አቶ ሙዲ ዝዬ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ አግኝተን ያነጋገርናቸው አርሶ አደሮች ናቸው።
አርሶ አደሮቹ እንዳሉት በመኸር ወቅት ማሳቸውን በተገቢው በማረስና ግብአት በመጠቀም ስንዴና ገብስ መዝራታቸውን አንስተዋል።
ለዚህም ከማሳ ዝግጅት ወቅት ጀምሮ የግብርና ባለሙያ የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳብ በመጠቀም መስራታቸው ያነሱት አርሶ አደሮቹ በቀጣይም ከማሳቸው ሳይነጠሉ የመንከባከብ ስራ እንደሚሰሩም ገልጸዋል።
ከዚህም ባለፈ በሌማት ትሩፋት በዶሮ እርባታና በግ ከማሞከት ባለፈ በፍራፍሬ ልማት አቮካዶ፣ ቡና፣ ካሮትና ሌሎችም ሰብሎችን በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተዋል።
ነሐሴ 13/2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ወቅታዊ የግብርናና የትምህርት እንደዚሁም ሌሎች የልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ እየተካሄደ ይገኛል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የዞን ደጋፊ አመራርና የወረዳው የስራ ኃላፊዎች በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የግብርናና ሌሎችም ወቅታዊ የልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ በመካሄድ ላይ ነው።
በወረዳው በዘንድሮ የመኸር እርሻ ልማት 20ሺ 518 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እስካሁን 17ሺ 814 ሄክታር መሬት በገብስ፣ በስንዴ፣ በመኸር ድንች፣ በባቄላ፣ በአተርና በጤፍ ለምቷል።
በመስክ ምልከታው በወረዳው የሀጂ ለገሰ ሸረፋ አበባ እርሻ ልማት የተጎበኘ ሲሆን እርሻ ልማቱ 38 ሄክታር መሬት በመረከብ 11 ነጥብ 5 ሄክታር መሬቱ ወደ ተግባር ገብቷል።
እርሻ ልማቱ 76 አይነት የአበባ ዝርያ ከማምረት ባለፈ ለ465 ሰራተኞች ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠሩንም ተጠቁሟል።
ከግብርና ልማት ስራ በተጨማሪ የተማሪዎች የምዝገባ ሂደትና ሌሎችም ወቅታዊ የልማት ስራዎችን ምልከታ በማድረግ ላይ ናችው።
በመስክ ምልከታው የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣ የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አብድረሂም ርዳ ጨምሮ የወረዳው የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ነሐሴ 08/2018 ዓ/ም
የገጠር ኮሪደር ልማት እሳቤን ተግባራዊ በማድረጋቸው የአኗኗር ዘይቤያቸው ከመቀየሩ ባለፈ ተጠቃሚ መሆናቸውን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ያነጋገርናቸው አርሶ አደሮች ተናገሩ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በወረዳው የወለጋ ደሴ ቀበሌ ደበሌ መንደና የጎምራ ቀበሌ የገጠር ኮሪደር ልማት ስራን ምልከታ ተደርጎባቸዋል።
በገጠር ኮሪደር ልማት ውጤታማ ስራ ለመስራት ቅንጅታዊ አስራሮች ተግባራዊ እየተደሩ እንደሆነ ተመላክቷል።
የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አብድረሂም ርዳ በበኩላቸው በገጠር ኮሪደር የገጠሩን ማኅበረሰብ የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ያለመ በመሆኑ የወረዳውን ህብረተሰብ ኑሮ ለማሻሻል ሞዴለ መንደሮችን በመምረጥ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በገጠር ኮሪደር ልማት የመንደሮችን ጽዳትና ውበቱ እንዲጠበቅ ብቻ ሳይሆን ድህነት በመቀነስ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ያነሱት አቶ አብድረሂም ለዚህም ስነምህዳሩ ታሳቢ ያደረጉ በአትክልትና ፍራፍሬና በእንሳት ዘርፍ አርሶአደሮች የተሻሻሉ ዝርያዎች እንዲኖራቸው እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ይህም አርሶ አደሩ በምግብ ራሱ እንዲችል፣ የተመጣጠነ የአመጋገብ ስርአት እንዲኖረው ከኮሪደር ልማቱ በማስተሳሰር እየተሰራ ነው ያሉት።
አክለውም በኮሪደሩ የሰውና የእንሰሳት ቤት እንዲለይ፣ መጸዳጃ ቤት እንዲኖር፣ መብራት የሌለባቸው አካባቢዎች የሶላር ተጠቃሚ ለማድረግና የአኗኗር ስርአቱ የተስተካከለ እንዲሆን እየተሰራ ያለው ስራ በተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል።
በወረዳው የሚገኙ ሞዴል አርሶአደሮችን በመለየት በወረዳው በተመረጡ አካባቢዎች ሞዴል መንደር እንዲመሰርቱ የግንባታ ስራዎች መጀመሩንም ጠቁመዋል።
በቀጣይ የአካባቢ ተወላጅ ባለሀብቶችን በማስተባበር ወረዳውን ወደ ተሻለች ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ ወረዳው እንደሚሰራ ገልጸዋል።
አርሶአደር ሰይድ ያሲኖና እቴነሽ ቱሉ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የወለጋ ደሴና የጎምራ ቀበሌ ነዋሪዎች ሲሆኑ በገጠር ኮሪደር ልማት ራሳቸውንና አካባቢያቸውን ጽዱ በማድረግ ጤናቸውን በተገቢው እየጠበቁ መሆናቸውን አስረድተዋል።
በገጠር ኮሪደር በተሠራው ቤት የሚያረቡትን የቤት እንስሳት በልዩ ሁኔታ በመንከባከብ የተሻለ ኑሮ እየኖሩ መሆኑን ገልጸዋል።
