en
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

Open in Telegram
912
Subscribers
+124 hours
+47 days
-430 days
Posts Archive
ነሐሴ 20/2019 ዓ/ም የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽሕፈት ቤት ከባለድርሻ ተቋማት ጋር የግብ ስምምነት ተፈራረመ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽሕፈት ቤት የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትግበራ ዙሪያ ከባለድርሻ ሴክተር መሥሪያ ቤቶች ጋር የግብ ስምምነት ተፈራረመ። በዕቅድ ትግበራውና በግብ ስምምነቱ ላይ በቅንጅት ለመሥራት የተፈራረሙት ሴክተሮች የወረደሰው ትምህርት ጽ/ቤት፣የመንግስት ኮሚኒኬሽን፣ ቴክኒክና ሙያ እና ደንና አካባቢ ጥበቃ መሥሪያ ቤቶች ናቸው። የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሄኖክ ጉልላት በስምምነቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት በበጀት ዓመቱ የተያዙትን የባህልና ቱሪዝም ዕቅዶች በላቀ ደረጃ ለማሳካት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሠራርና ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ሄኖክ አክለውም ስምምነቱ በየሴክተሩ የተጣሉትን ኃላፊነቶች በውጤታማነት ለመወጣትና የወረዳውን የቱሪዝም እምቅ አቅም በጋራ ለማውጣት ትልቅ መሠረት እንደሚጥል አስገንዝበዋል።

የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውጤታቸውን ዛሬ ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምረው ማየት ይችላሉ - የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ነሐሴ 19/2018 (ወልቂጤ) የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል። በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (ሊንክ) በመጠቀም ማየት እንደሚችሉ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ባወጣው መረጃ አስታውቋል። በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል እንደሚችሉ አመልክቷል። #ኢቢሲ

"ለታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ተጠርተናል ብለን የምናምን ከሆነ የነቢዩ ሕይወት ታላቅ ትምህርት ይሆነናል፤ የተጠራንበትን ዓላማ በንግግራችን፣ በሥራችንና በሕይወታችን እንግለጠው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ነሐሴ 19/2018 ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰው ተኮር የሆኑ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ የስራ መስኮች ተጠናክረው ቀጥሏል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በወረዳው መሀል አምባ 01ቀበሌ ነዋሪ ለሆኑት አቅመ-ደካማ ወ/ሮ ዛይዳት በንቲ 40 ቆርቆሮና 2 ፓኬት ሚስማር ድጋፍ ተደረገ። በወረዳው "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ሚፍታ ሁሴን ለአቅመ ደካማ አረጋዊያን የቆርቆሮና ሚስማር በአካል በመገኘት ድጋፍ አድርገዋል።

ነሐሴ 18/2018 ዓ/ም በጉራጌ ዞን የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ክህሎት መር የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ስራ እድል ፈጠራ ለማህበራዊ እና ለኢኮኖሚያዊ እድገት እጅግ ወሳኝ በመሆኑ በዘርፉ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል። በጉራጌ ዞንም ባለፉት 3 አመታት ውስጥ 23 ሺ 318 ዜጎች የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት ስልጠና ተሰጥቷል። ህገ ወጥ ደላሎችን በመከላከል ፣የዜጎች ደህንነት በመጠበቅ፣ ህጋዊ የስራ ስምሪት መስመሮችን ለማጠናከር እና ፍትሀዊ ጥቅም እንዲያገኙ ጉልህ ሚና እንዳለው ተመላክቷል። በጉራጌ ዞን በ2019 በጀት አመት 16ሺ 153 ዜጎች የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት ይሰራል ተብሏል። በመድረኩ የጉራጌ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ደሳለኝ ፈቀደ፣የጉራጌ ዞን ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙራድ ያሲን፣የጉራጌ ዞን ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ አርሺያ አህመድ፣የጉራጌ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ስርግማ፣የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር የብልጽግና ጽ/ቤት አመራሮች፣የጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ባለሙያዎችና የኮሌጅ ዲኖች ተገኝተዋል።

የሳምንቱ ዓብይት ዜናዎች ነሐሴ 17/2018 ዓ.ም 🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ህገ ወጥ የመሬት ወረራና ግንባታን ለመከላከል እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተገመገሙ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የኢንጌ ጤና ጣቢያ ቦርድ አባላት የ2018 በጀት ዓመት የ4ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የአበዘት ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀሙን የቦርድ አባላት በተገኙበት ገመገመ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰው ተኮር የሆኑ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ የስራ መስኮች ተጠናክረው ቀጥሏል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በወረዳው በኢንቨስትመንት ዘርፍ የተጀማመሩ ስራዎችን በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት ይሰራል:- አቶ ሚፍታ ሁሴን ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ቴክኒክ ኮሚቴ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልጎሎት ላይ የተከናወኑ ተግባራትን ግምገማ አካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በወረዳው በተቀናጀ የግብርና ልማት የህብረተሰቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው:- አቶ ሚፍታ ሁሴን ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ወቅታዊ የግብርናና የትምህርት እንደዚሁም ሌሎች የልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ እየተካሄደ ይገኛል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የማዕከላዊ ኢትዮጵየሰ ክልል መንግስት በከተሞች የመሬት ወረራንና ህገ ወጥነት ለመከላከል ያስቀመጠውን አቅጣጫ መነሻ በማድረግ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በሚገኙ የማዘጋጃ ከተሞች ከፍተኛ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የመሃል አምባ ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ ዓመት ተግባር አፈፃፀም የቦርድ አባላት በተገኙበት ገመገመ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የህገ-ወጥ መሬት ወረራን የሚከላከል የቴክኒክ ኮሚቴ ግብረ-ኃይል የጋራ መድረክ ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ2019 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ በሁሉም ትምህርት ቤቶች በይፋ ተጀምሯል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨

በወርቅ ብዕር የተጻፈ ታሪክ፦ የኢትዮጵያ አሸናፊነት! ዛሬ በኢትዮጵያ ምድር ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ ተገልጧል። ዛሬ ኢትዮጵያውያን ተነጋግረው መግባባት እንደሚችሉ ለራሳቸውም ሆነ ለዓለም በተግባር ያረጋገጡበት አንጸባራቂ የድል ዕለት ነው። የሀገራዊ ምክክሩ አጀንዳ ማሰባሰብ እና ማጽደቅ ጉባኤ በመግባባት ተጠናቅቋል። ይህ ክስተት ሀገራችን ለዘመናት ከተዘፈቀችበት የጥፋት አዙሪት ወጥታ፣ በአዲስ የተስፋ ጎዳና ላይ መቆሟን የሚያበስር፣ በወርቅ ብዕር የተጻፈ ደማቅ ታሪክ ነው! ከአውዳሚው አዙሪት መውጣት ለዘመናት ሀገራችንን ወደ ኋላ የጎተታት፣ ወንድምን ከወንድም ያቃቃራት እና የልጆቿን ደም ያስገበረው ክፉ የፖለቲካ አዙሪት ነበር። ችግሮችን በጠመንጃ አፈሙዝ ብቻ የመፍታት አዙሪት፤ "እኔ እችላለሁ፣ አንተ ግን አትችልም" የሚል የትዕቢት አዙሪት፤ "እኔ ብቻ ነኝ የማውቅልህ፣ አንተ አታውቅም" የሚል አግላይ የፖለቲካ አዙሪት፤ እንዲሁም ለልዩነት እና ለቅራኔ ሁሉ መፍትሔው ጦርነት እና ግጭት ብቻ ነው ብሎ የማመን አዙሪት ሀገራችንን ክፉኛ ጎድቷታል። በዚህ አውዳሚ የጥፋት መንገድ፣ የሰው ልጅ ክቡር ሕይወት ረክሷል፣ ትውልዶች አልቀዋል፤ የሀገር ሀብት ወድሟል፤ የሀገረ መንግሥት ግንባታችንም በተደጋጋሚ ተሰንጥቋል። አሸናፊ እና ተሸናፊ በሚፈጥረው በዚህ እኩይ ባህል ውስጥ፣ በመጨረሻ ሁሌም ተሸናፊዋ ሀገር ነበረች። የጠረጴዛው ድል እና የታሪክ ትምህርት ዛሬ ግን ኢትዮጵያውያን ይህንን የሞት እና የጥፋት አዙሪት በድል አሸንፈው ወጥተዋል! ዛሬ የተጠናቀቀው የምክክር ምዕራፍ፣ ጠመንጃዎች የታጠፉበት፣ የጥላቻ ትርክቶች የተሰበሩበት እና የውይይት ጠረጴዛዎች የሞቁበት ታላቅ መድረክ ነው። ልዩነቶቻችን የቱን ያህል የሰፉ ቢመስሉም፣ አንገት ለአንገት ከመተናነቅ ይልቅ ጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠን የጋራ ሀገራዊ አጀንዳዎቻችንን ነቅሰን ማውጣት እና በልብ መግባባት እንደምንችል ዛሬ በተግባር አሳይተናል። ይህ ከራስ ወዳድነት፣ ከግትርነት እና ከጽንፈኝነት ወጥቶ፣ ለእናት ሀገር ሲሉ የራስን ፍላጎት አስማምቶ የጋራ የወል እውነትን የማዋለድ ጥበብ፣ በታሪካችን ውስጥ እጅግ ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ አንጸባራቂ ድል ነው። ኢትዮጵያ በልጆቿ አሸንፋለች! የዛሬው ስኬት የማንም ግለሰብ፣ የትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ወይም የተወሰነ ቡድን አሸናፊነት አይደለም፤ ዛሬ ያሸነፈችው ታላቋ ኢትዮጵያ ናት! አዎ፣ ኢትዮጵያ በገዛ ልጆቿ ጥበብ፣ ብስለት እና አስተዋይነት አሸንፋለች! አንዳንዶች "ኢትዮጵያውያን አይግባቡም፣ መነጋገር አይችሉም፣ ችግራቸውን በጠመንጃ እንጂ በጠረጴዛ ዙሪያ መፍታት አይችሉም" ሲሉ የነበሩትን ሁሉ ኃፍረት ያከናነበ፣ የኢትዮጵያውያንን የሐሳብ ልዕልና ለዓለም ያሳየ ታሪካዊ ውሎ ነው። ይህ ጉባኤ፣ የሰው ልጅ በተፈጥሮው ምክንያታዊ መሆኑን፣ ጥበብ እና መደማመጥ ከማንኛውም የጦር መሣሪያ በላይ ኃያል መሆኑን አረጋግጧል። ይህ የዛሬው ምዕራፍ ለነገው ትውልድ የሚተላለፍ፣ በታሪክ መዛግብት ውስጥ በክብር የሚዘከር ሕያው ትምህርት ነው። አሁን የሀገራችን የፖለቲካ ስብራት የሚጠገንበት፣ ወንድማማችነት የሚጸናበት እና እውነተኛ የመግባባት ዴሞክራሲ ዕውን የሚሆንበት ጽኑ መሠረት በይፋ ተጥሏል። ትናንትን በይቅርታ ዘግተን፣ ልዩነቶቻችንን በሰከነ እና በሠለጠነ ምክክር እያረቅን፣ አንዳችን የሌላኛችንን ሐሳብ አክብረን፣ የሁላችንም የሆነችውን ታላቋን ኢትዮጵያ በጋራ እንገነባለን! ዛሬ በምክክር አውድማ የተገኘው ድንቅ መግባባት፣ ነገ ለምትጸናው፣ በልጆቿ የጋራ ራዕይ ለምትበለጽገው እና ምንጊዜም አሸናፊ ለምትሆነው አዲሲቷ ኢትዮጵያ የማይነቃነቅ ብሩህ ተስፋ ነው! ታሪክ ተሠርቷል፤ ጠመንጃዎች ታጥፈው ጠረጴዛዎች ተዘርግተዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!

ነሐሴ 16/2018 ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ህገ ወጥ የመሬት ወረራና ግንባታን ለመከላከል እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተገመገሙ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የገ/ጉ/ወ ወረዳ ህገ ወጥ የመሬት ወረራና ህገወጥ ግንባታን ለመከላከል የተቋቋመው አብይ ኮሚቴ በእስካሁን ስራዎች አፈፃፀም ላይ ውይይት አካሂዷል። በዚህ ወቅት የዐብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ እንደገለጹት የህዝብና የመንግስት የእድገት ምንጭ የሆነውን የውስን የከተማ መሬት ወረራን በቅንጅት በመከላከል ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ገልጸዋል። መሬት ላይ የሚስተዋሉ ህገወጥና ብልሹ አሰራሮችን በጋራ መከላከል ይገባል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው የወል መሬት ወረራ በበዛባቸው ከተሞች፣ የከተሞችን ገቢ እንዲቀንስ ፣ የአርሶ አደር መሬቶች ህጋዊነት ከህገ ወጦች ጋር መተባበር እንዲሁም የማስፋፊያ በሚል የሚከናወኑ ሌብነቶች የአብይና ቴክኒክ ኮሚቴ ግብረ ሀይል በግልጽ ሊታገለው እንደሚገባ አሳስበዋል። የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አብድልረሂም ረዳ በበኩላቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ በወረዳ ማዘጋጃ ቤቶች ህገ ወጥ መሬት ለማስመለስ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸው ጠቅሰው ከተሞች በፕላን እንዲመሩ በማድረግ እድገታቸው እንዲፋጠን ህገ ወጥነትን መከላከል ቀዳሚ ተግባር አድርጎ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። አቶ አ/ረሂም አክለው ስራው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀናጅቶ መስራት ፣የልየታ ስራን ማጠናከር፣የህግ የበላይነትን ማረጋገጥና ትክክለኛ መረጃ መያዝ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በወረዳው በ6 ከተሞች የህገ ወጥ መሬት ወረራ ልየታ በማድረግ ከ2500 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ማወያየት የተቻለ ሲሆን መሀል አምባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት 3 ሺ 895 ካ/ሜትር ወደ መሬት ባንክ መግባቱን በመድረኩ ተመላክቷል።

ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል የሀገር አቀፍ ፈተና ከተፈተኑ 550,210 ተማሪዎች መካከል ማለፍ የቻሉት 70,544 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ይህም ማለት 479,666 ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ አላመጡም (አላለፉም) ማለት ነው። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 12.8% ተማሪዎች ማለፋቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አሳወቀ። ለፈተና ከተቀመጡ 560,210 ተማሪዎች 70,544 ወይም 12.8% የሚሆኑት ማለፋቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ለጋዜጠኞች ገልፀዋል። በመላ አገሪቱ የመልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ውስጥ 88 ትምህርት ቤቶች 100% ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ማሳለፋቸውን የገለፁ ሲሆን፣ 585 ትምህርት ቤቶች ደግሞ ምንም ተማሪ አለማሳለፋቸውን ገልፀዋል። Via Minstry of Education Ethiopia

ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የኢንጌ ጤና ጣቢያ ቦርድ አባላት የ2018 በጀት ዓመት የ4ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የኢንጌ ጤና ጣቢያ ቦርድ አባላት የ2018 በጀት ዓመት የ5ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም እንዲሁም የጤና ጣቢያውን የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ ባሉ ጥንካሬዎችና ጉድለቶች ላይ ጥልቅ ውይይት በማድረግ የቀጣይ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል። የኢንጌ ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ ታዴ ወርቁ የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ አመት አፈፃፀም ሪፖርት በማቅረብ የቦርድ አባላት ሰፊ ውይይት አካሂደዋል። በመድረኩ የቦርድ አባላት እንዳሉት የተገልጋይ ህብረተሰብን ፍላጎትን መሠረት ያደረገ የመድኃኒት አቅርቦት ፣የባለሙያዎች የአገልግሎት አሰጣጥ ጉድለቶችና የስነ ምግባር ችግሮች እና በሌሎች ጉዳዮች ሰፊ ውይይት ተደርጎ በጥንካሬ የተለዩ ጉዳዮችን አጠናክሮ በማስቀጠል በጉድለት የተለዩትን በቀጣይ የእቅድ አካል አድርጎ ማስተካከል እንደሚገባ እንዲሁም የቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጧል። የቦርድ ውይይቱን የመሩት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪና የጤና ጣቢያ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሚፍታ ሁሴን በማጠቃለያ ወቅት እንዳሉት የጤና ጣቢያው አገለግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ከተገልጋይ ህብረተሰብ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በማረም ለህብረተሰቡ ተገቢ አገለግሎት መሠጠት እንደሚገባ ገልጸዋል። ጤና ጣቢያው ላይ ያሉ ጠንካራ ስራዎችን በተሻለ መልኩ ማስቀጠልና የአገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነትን በማጠናከር ጤናው የተጠበቀና አምራች ማህበረሰብ መፍጠር እንደሚገባ አቶ ሚፍታ አሳስበዋል።