en
Feedback
ANRS Ethics and anti-corruption commission

ANRS Ethics and anti-corruption commission

Open in Telegram

ሙስና የተረጋጋ ኑሮ እንዳይኖር፣ መልካም አስተዳደር እንዳይሰፍን፣ የወደፊት ተስፋ እንዲጨልምና የሀገረን የመልማት አቅም እንዲሰናከል ያደርጋል።

Show more
660
Subscribers
No data24 hours
-27 days
+530 days
Posts Archive
እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን! 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም/ አብክመ ሥ.ፀ.ሙ.ኮ/ የአብክመ የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ለመላው ኢትዮጵያውያን አዲ
እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን! 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም/ አብክመ ሥ.ፀ.ሙ.ኮ/ የአብክመ የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ለመላው ኢትዮጵያውያን አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የአንድነትና የብልጽግና ዘመን እንዲሆን መልካም ምኞቱን ይገልፃል። በዓሉን ስናከብር ያለፉ ችግሮቻችን በይቅርታና በንግግር  በመፍታት  በቀጣይ ዓመት ለህዝባችንና ለልማታችን ትልቅ እንቅፋት የሆነውን  ሙስናና ብልሹ አሰራር በጋራ  ለመከላከል ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል በማለት ኮሚሽኑ መልክቱን ያስተላልፋል። መልካም አዲስ ዓመት፤ እንቁጣጣሽ!   "ትዉልድን በሥነ ምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!"

ማህበረሰባዊ አስገዳጅ እሴቶች ምን ምን ናቸዉ? 🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ማህበረሰባዊ አስገዳጅ እሴቶች በአንድ ማህበረሰብ ውስጥ ያሉ ሰዎች አብረው በሰላም፣ በፍትህ እና በመከባበር ለመኖር ሊጠብቋቸው የሚገቡ፣ በማህበራዊ ህግ፣ በባህል፣ በሃይማኖት ወይም በሥነ-ምግባር ደንቦች ታግዘው ሰዎችን የሚያስገድዱ መመሪያዎች ናቸው። እነዚህ እሴቶች ማህበረሰቡ እንደ አስፈላጊነታቸው መጠን በተለያየ መንገድ (በህግ፣ በባህላዊ ቅጣት ወይም በማህበራዊ ማግለል) ተፈጻሚነታቸውን ያረጋግጣል። ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፡ ✔️የሰው ልጅ ህይወት እና አካል የመጠበቅ እሴት፦ ማንኛውንም የሰው ልጅ ህይወት አለማጠፋት እና አለመጉዳት ማህበረሰብ የሚቆምበት መሰረታዊ አስገዳጅ እሴት ነው። ሰዎችን ከጥቃት፣ ከስድብ እና ከእንቅስቃሴ ገደብ መጠበቅ። ✔️ፍትህ፣ እውነት እና ታማኝነት፦ በንግድ፣ በቃል ኪዳን እና በዕለት ተዕለት ግንኙነት ውስጥ እውነትን መናገር እና አለማታለል፤ ሰዎችን በዘር፣ በሃይማኖት ወይም በሀብት ሳይለያዩ በእኩልነት ማየት፤ የሰው ወርቅ/ንብረት አለመመኘት እና የቃል ኪዳን ታማኝነት፡ የተገባን ቃል እና ስምምነት ማክበር ነዉ። ✔️የመከባበር እና የጋራ ኃላፊነት እሴቶች፦ በእድሜ፣ በልምድ እና በኃላፊነት ከፍ ያሉትን ማክበር እና መንከባከብ፤ ህጻናትን፣ አረጋውያንን፣ አካል ጉዳተኞችን እና ችግረኞችን መደገፍ የማህበረሰብ የጋራ ኃላፊነት ነው። የህዝብ ሀብትን፣ ምንጮችን፣ ደኖችን እና የጋራ መጠቀሚያዎችን አለማጥፋት። ✔️ሰላም እና የእርቅ ባህል፦ አለመግባባቶች በግጭት ሳይሆን በውይይት፣ በሽማግሌዎች እና በህግ እንዲፈቱ ማድረግ እና የሌሎችን ልዩነት (ሃይማኖት፣ ባህል፣ አመለካከት) አክብሮ አብሮ መኖር። ✔️ስራ እና ህጋዊነት፦ በህጋዊ እና በቅንነት ስራ መኖር፣ ሌብነትን እና ጥገኝነትን መጸየፍ እንዲሁም በማህበረሰቡ የተደነገጉ ባህላዊ እና ዘመናዊ ህጎችን ማክበር የሚሉ ናቸዉ። በአጠቃላይ እነዚህ እሴቶች ባልተጠበቁበት ማህበረሰብ ውስጥ ስርዓት አልበኝነት፣ ግጭት እና ውድቀት ይከሰታል። ስለዚህ ማህበረሰቡ እነዚህን እሴቶች በትውልድ መካከል በስልጠና፣ በምሳሌነት እና በስርዓተ-ፆታ/ትምህርት በማስተማር እሴቶችን መጠበቅ ያስፈልጋል።

ጳጉሜን 5 "የነገ ቀን" 🌿🌿🌿🌿 "የነገ ቀን" የሚለው ጽንሰ-ሀሳብ ከሥነ-ምግባር ግንባታና ሙስናን ከመከላከል አንጻር ሲታይ፣ የድርጊቶቻችን የረጅም ጊዜ ውጤት፣ የተጠያቂነትን መንፈስ እና የወደፊት ትውልድ እጣ ፈንታን አስቦ የመስራት መሰረታዊ መርህ ነው። የነገን ቀን በሶስት ዋና ዋና አቅጣጫዎች ማየት ይቻላል። 👉የተጠያቂነት እና የውጤት ራዕይ፦ በሙስና ወይም በብልሹ አሰራር የተገኘ ጊዜያዊ ጥቅም የዛሬን ችግር የሚፈታ ቢመስልም፣ "የነገ ቀን" ግን ህጋዊ፣ ማህበራዊ እና ሞራላዊ ተጠያቂነትን ይዞ መምጣቱ አይቀሬ ነው። አሰራርን እና ህግን አክብሮ መስራት የዛሬን ተግባር ማከናወን ብቻ ሳይሆን የተቋሙን የነገ ቀን ህልውና፣ ታማኝነት እና ጥንካሬን የሚያረጋግጥ ነው። 👉የወደፊት ትውልድ ኃላፊነት እና ሀገራዊ ራዕይ፦ ዛሬ የሥነ-ምግባር ጉድለት እና ሙስና ሲኖር የሀገር ሀብትና ንብረት ይባክናል። የነገን ቀን ያሰበ አመራርም ሆነ ሰራተኛ የዛሬን ሀብት በአግባቡ በመጠቀም ለነገው ትውልድ የተረጋጋች እና የበለፀገች ሀገር ያስረክባል። ዛሬ በስራ ቦታና በማህበረሰብ ውስጥ የሚታይ በጎ የሥነ-ምግባር እሴት ለነገው ትውልድ የሚተላለፍ ትልቅ ውርስ ነው ማለት ነዉ። 👉የተስፋ፣ የለውጥ እና የጽናት ምልክት፦ "የነገ ቀን" ሲባል ትናንትና እና ዛሬ በሙስና ወይም በሥነ-ምግባር ጉድለት የተበላሹ አሰራሮችን በቆራጥነት አርሞ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የተሻለ ነገን የመገንባት ተስፋ ነዉ። ጊዜያዊ ጥቅምን ለማግኘት ሲባል ህግንና መመሪያን ከመጣስ ይልቅ፣ ለዘላቂ ስኬት እና ህሊናዊ እረፍት የሚሰጥ የስራ ባህልን መገንባትን ያመላክታል። በአጠቃላይ "የነገ ቀን" ማለት በሥነ-ምግባር ግንባታ ህሊናዊ መስተዋት ሲሆን፣ ሙስናን በመከላከል ረገድ ደግሞ እያንዳንዱ አሰራር፣ ውሳኔ እና ተግባር የዛሬን ፍላጎት ብቻ ሳይሆን የነገን ሀገራዊና ህዝባዊ ደህንነት ያገናዘበ መሆን እንዳለበት የሚያስገነዝብ መሪ ሀሳብ ነው።

"ቁጭ ብለው የሰቀሉት፣ ቆሞ ለማውረድ ይከብዳል!" ሙስና በግለሰቦች ስግብግብነት የሚፈጸም ቀላል ወንጀል ብቻ ሳይሆን፣ የሀገርንና የህዝብን መሰረት የሚንድ፣ ትውልድን የሚበክል እና የሀገርን እድገት
"ቁጭ ብለው የሰቀሉት፣ ቆሞ ለማውረድ ይከብዳል!" ሙስና በግለሰቦች ስግብግብነት የሚፈጸም ቀላል ወንጀል ብቻ ሳይሆን፣ የሀገርንና የህዝብን መሰረት የሚንድ፣ ትውልድን የሚበክል እና የሀገርን እድገት አቀጭጮ የሚቀር አደገኛ መቅሰፍት ነው። «ቁጭ ብለው የሰቀሉት ቆሞ ለማውረድ ይከብዳል» የሚለዉ አባባል የሙስናን እውነተኛ መልክ እና አስከፊነት በእጅጉ የሚገልጽ ነው። ጉቦ በመስጠት፣ ሃላፊነትን ላልተገባ ዓላማ በመጠቀም፣ ህግን በመጣስ እና ዘረፋን በመዘርጋት የሚፈጸም ሕገ-ወጥ ድርጊት ሥር ሲሰድና ተቋማዊ ሲሆን፤ ጉዳዩን ማስተካከል ወይም የተዛባውን ስርዓት ወደ ነበረበት መመለስ እጅግ ከባድና ብዙ ዋጋ የሚያስከፍል ፈተና ይሆናል። የስልጣንና ፍትሃዊ ያልሆነ የሀብት ክፍፍል በጊዜው ካልታረመ፣ በኋላ ላይ የሚመጣው ትውልድ ያንን የተዛባ ስርዓት ለማረም ወይም ቁጭ ብለው የሰቀሉትን ለማውረድ ከፍተኛ ዋጋ የሚያስከፍል ይሆናል ማለት ነዉ፡፡ #በመሠረት ተስፋዬ

ተማሪዎች ትምህርት ከመጀመራቸዉ በፊት መገንዘብ ያለባቸዉ የሥነ ምግባር አይነቶች፦ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ተማሪዎች የትምህርት ዘመንን ከመጀመራቸው በፊት በትምህርት ገበታቸው፣ ከጓደኞቻቸው እና ከአስተማሪዎቻቸው ጋር የሚያደርጉትን ግንኙነት ስኬታማ ለማድረግ ሊገነዘቧቸውና ሊተገብሯቸው የሚገቡ ዋና ዋና የሥነ ምግባር ዓይነቶች ናቸዉ። እነሱም፦ ✔️የግል ሥነ ምግባር፦ በፈተናዎች፣ በቤት ሥራዎች እና በጥናት ወቅት ከማጭበርበር መቆጠብ እና የራስን ጥረት ብቻ መጠቀም ይኖርባቸዋል። በትምህርት ገበታ፣ በክፍል ሰዓት እና በስብሰባዎች ላይ በሰዓቱ የመገኘት እና የተሰጡ የቤት ሥራዎችን እና ፕሮጀክቶችን በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ አጠናቆ ማቅረብ ይገባል። ✔️የማህበራዊ እና የትምህርት ቤት ሥነ ምግባር፦ ለአስተማሪዎች፣ ለትምህርት ቤት ሰራተኞች እና ለአካባቢው ህብረተሰብ ተገቢውን አክብሮት ማሳየት ይገባል። የክፍል ጓደኞችን በብሔር፣ በሃይማኖት፣ በፆታ ወይም በኢኮኖሚ አቅም ሳይለዩ በእኩልነት ማየት እና መደጋገፍም ከተማሪዎች ይጠበቃል። ✔️የአካዳሚክ ሥነ ምግባር፦ የሌሎችን ሥራ፣ ሀሳብ ወይም ጽሑፍ ያለፍቃድ ወይም ምንጩን ሳያመለክቱ የራስ አድርጎ ተገቢ አይደለም። በቡድን ሥራዎች ወቅት ተገቢውን ድርሻ መወጣት እና የሌሎችን ሀሳብ በትዕግስት ማዳመጥ አስፈላጊ ነዉ። ✔️የንብረት እና የአካባቢ ሥነ ምግባር፦ የትምህርት ቤቱን ወንበሮች፣ ጥቁር ሰሌዳ፣ የመጻሕፍት መደርደሪያዎችን እና ቤተ-መጻሕፍትን በጥንቃቄ መጠቀም ይገባል። የትምህርት ቤቱን ቅጥር ግቢ እና የክፍል ውስጥ አካባቢን ንፁህ አድርጎ መጠበቅም ይገባል። ✔️የዲጂታል ሥነ ምግባር፦ ስልክ እና ኮምፒውተርን ለትምህርት አላማ ብቻ ማዋል፣ በበይነመረብ (Internet) ላይ ሰዎችን ከሚጎዱ ድርጊቶች እና ሀሰተኛ መረጃዎች መቆጠብ ያስፈልጋል።

ግብረ-ገባዊ ትዉፊቶች እነማን ናቸዉ? 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ግብረ ገባዊ ትውፊቶች ማለት በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተላላፉ የመጡ፣ የሰዎችን መልካም ባህሪ፣ ስርዓት፣ ግብረገብነት እና ማህበራዊ አኗኗር የሚመሩ አባቶችና እናቶች ያስረከቧቸው እሴቶች፣ ባህሎችና ልማዶች ናቸው። እነዚህ ትውፊቶች ማህበረሰቡ መልካምን ከክፉ፣ ትክክለኛውን ከስህተት የሚለይባቸው መመሪያዎች ናቸው።እነሱም፦ ✍️ታላላቆችን ማክበር እና መንከባከብ፦ ለታላላቆች ቅድሚያ መስጠት፣ በሽማግሌዎች ምክር መመራት፣ አረጋውያንን መንከባከብ፣ ሰላምታ ሲሰጡ ወይም ሲቀበሉ አክብሮትን በሚገልጽ መልኩ ጎንበስ ማለት ወይም እጅ መንሳት። ✍️አገር አቀፍ ዕርቅ እና የሽምግልና ስርዓት፦ በሰዎች ወይም በቤተሰብ መካከል አለመግባባት ሲፈጠር በህግ አሰራር ብቻ ሳይሆን በሀገር ሽማግሌዎች፣ በሃይማኖት አባቶች እና በባህላዊ የዕርቅ ስርአቶች ግጭቶችን በሰላም መፍታት። ✍️መረዳዳት እና ማህበራዊ ደጋፊነት፦ ዕድር እና እቁብ፣ በደቦ ወይም ወንፈል እና ጽዋ/ማህበር አማካኝነት በደስታና በችግር ጊዜ በጋራ መቆም፣ በግብርና፣ በቤት መስራት እና በከባድ ስራዎች ወቅት እርስ በእርስ በነጻ መረዳዳት እንዲሁም መንፈሳዊና ማህበራዊ ትስስርን ማጠናከር ናቸዉ። ✍️እንግዳ ተቀባይነት፦ እንግዳን ወይም መንገድ አዳሪን በፍቅር መቀበል፣ ማስተናገድ፣ ምግብና መጠጥ ማቅረብ እንዲሁም መጠለያ መስጠት ናቸዉ። ✍️እውነትን መናገር እና ቃልን መጠበቅ፦ ታማኝነት፣ በቃል መቆም እና "የአባት ቃል" ወይም "የሀገር ማህላ" ማክበር፣ ሀሰት መናገርን እና መስረቅን እንደ ትልቅ ነውር እና ውርደት መቁጠር ተገቢ ነዉ። ✍️ይሉኝታ እና ነውርን ማወቅ፦ ሌሎች ሰዎችን የሚጎዳ ወይም የሚያሳፍር ነገር ላለማድረግ መጠንቀቅ፣ የህዝብና የማህበረሰብን ክብር የሚነኩ ድርጊቶችን ከመፈጸም መቆጠብ የሚሉ ናቸዉ።

የሌባ ቀን በተባበረ ህብረት ሊመሽ ይገባል! 🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ሌብነትና ሙስና የወል ሃብታችን፣ የእድገት ተስፋችንና የማህበረሰባችን የሞራል መሠረት የሚሸረሽሩ አደገኛ አደጋዎች ናቸው። "የሌባ ቀን በተባበረ ክንድ ሊመሽ ይገባል!" ሲባል ሌብነት የጥቂት ግለሰቦች ወንጀል ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው ማህበረሰብ ህልውና ስጋት መሆኑን ያመለክታል። ሌብነትንና ህገ-ወጥነትን በግል ጥረት ብቻ ማስቆም አይቻልም፤ የመልካም አስተዳደርና የፍትህ የበላይነት እንዲነግስ የማህበረሰቡ የተባበረ ክንድ እና ህዝባዊ ትግል ወሳኝ ነው። ሌብነት በተለያየ መንገድ ይገለጻል። የህዝብ ሃብት ከመበዝበዝ ጀምሮ፣ አገልግሎት ለመስጠት ጉቦ እስከ መጠየቅ እና የህዝብን አመኔታ እስከ ማጎደል። እነዚህ ድርጊቶች የሀገርን ኢኮኖሚ ከማደናቀፋቸውም በላይ በዜጎች መካከል ያለው እምነት እንዲሸረሸር ያደርጋሉ። በአጠቃላይ የሌባን ቀን በይፋ ለማስመሸትና ስርዓት ለማስያዝ ህገ-ወጥ ድርጊቶች እና የሌብነት እንቅስቃሴዎች ሲታዩ ለሚመለከታቸው አካላት በጥቆማ ማሳወቅ፣ እውነትንና ፍትህን ይዘው የሚታገሉት አካላትን የህግ ከለላ መስጠት እና በየአካባቢያችን ያሉ የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አየሚሰጡት ገልግሎት ግልጽ እና ፍትሃዊ መሆኑን በቅርበት መከታተልና መጠየቅ። በእነዚህ የተቀናጁ እርምጃዎች ብቻ የሌቦችን እድሜ ማሳጠር እና የፍትህ፣ የታማኝነትና የእኩልነት ስርዓት መገንባት ይቻላል።

ሙስና የጋራ ጠላታችን በመሆኑ "በኅብር" እንታገል! 🌿🌿🌿🌿🌿🌿 «ኅብር» (አንድነት፣ ስምምነት፣ ህብረት ወይም የልዩነቶች ውህደት) ማለት ሲሆን ሥነ ምግባርን ከመገንባትና ሙስናን ከመከላከል አኳያ ሲታይ የጋራ አቋም፣ የሕዝብ ተሳትፎ እና የተቀናጀ ትግል ማለት ነው። ኅብር የልዩነቶች መተሳሰር ብቻ ሳይሆን፣ ሕዝባዊ አቅምን፣ የሞራል ጽናትን እና የጋራ ኃላፊነትን አስተባብሮ የሥነ ምግባር ጥሰቶችን ቀድሞ ለመከላከል የሚያስችል ጽኑ መሠረት ነው። በአንድ መሥሪያ ቤት፣ ማኅበረሰብ ወይም ሀገር ደረጃ የፀረ-ሙስና እና የሥነ ምግባር ግንባታን ውጤታማ ለማድረግ «ኅብር» የማይተኩ መሠረታዊ ሚናዎች አሉት፦ ✍️የተቀናጀ የጋራ ትግል፦ ሙስናን በተበታተነና በግለሰብ ደረጃ በሚደረግ ጥረት ብቻ መግታት አይቻልም። «ኅብር» ሲባል የመንግሥት አካላት፣ የሕዝብ ተወካዮች፣ የሲቪል ማኅበራት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ መገናኛ ብዙኃንና ሙሉው ማኅበረሰብ በአንድነትና በትስስር በመቆም በሙስና ላይ የሚፈጥሩትን የጋራ ግንባር ያመለክታል። ✍️የጋራ እሴትና የጋራ የሥነ ምግባር መስፈርት፦ ሥነ ምግባር ያለው ማኅበረሰብ የሚገነባው ማኅበረሰቡ በጋራ የሚቀበላቸውና የሚያከብራቸው እሴቶች (እንደ ታማኝነት፣ ግልጽነት፣ ፍትሐዊነትና ተጠያቂነት) ሲኖሩ ነው። «ኅብር» የነዚህን መልካም እሴቶች በጋራ ማበርታትና የጸና የሕሊና ደንብ ማድረግን ያመለክታል። ✍️ብዝሃነትን ለበጎ ዓላማ ማስተባበር፦ በማኅበረሰብ ውስጥ የሚገኙ ልዩ ልዩ እውቀቶችን፣ ባህሎችን፣ የሥራ ድርሻዎችንና አቅሞችን አስተባብሮ ለአንድ የጋራ ዓላማ በሕብረት መቆምን ያሳያል። ✍️የጋራ ባለቤትነትና የሕዝብ ቁጥጥር፦ «ኅብር» ማለት የሕዝብ ሀብትና ንብረት የሁላችንም ነው የሚል የባለቤትነት ስሜት ማሳደግ ነው። ሁሉም ዜጋ የሙስና ጠቆሚ፣ ተቆጣጣሪና የማኅበረሰቡ ባለቤት ሆኖ በኅብረት የሚቆምበትን አካባቢ መፍጠር ነው። በአጠቃላይ «ኅብር» ማለት ሙስናን ለመከላከልና ታማኝነትን ለማስፈን የሚደረግ «የጋራ ህሊና፣ የጋራ ትግል እና የተቀናጀ የሕዝብ ተሳትፎ» ማለት ነው። በመሆኑም ተቋማት፣ ዜጎች እና ባለድርሻ አካላት በሐሳብ፣ በዕውቀት እና በቁርጠኝነት በአንድነት በመቆም የጋራ ግንባር ሲፈጥሩ፣ የፍትሐዊነት፣ የታማኝነት እና የተጠያቂነት መርሆዎች በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ በዘላቂነት እንዲሰርፁ ማስቻል ይቻላል ማለት ነዉ።

መልካምነት የሚጀምረው ከሀሳብ ነው። 🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ማንኛውም ተግባር ከመከናወኑ በፊት በመጀመሪያ በሀሳብ ደረጃ ይጸነሳል። በጎ ሀሳብ ደግሞ የቆንጆ ስብዕና እና የተሻለ ማህበረሰብ መሠረት ነው።
መልካምነት የሚጀምረው ከሀሳብ ነው። 🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ማንኛውም ተግባር ከመከናወኑ በፊት በመጀመሪያ በሀሳብ ደረጃ ይጸነሳል። በጎ ሀሳብ ደግሞ የቆንጆ ስብዕና እና የተሻለ ማህበረሰብ መሠረት ነው። ለነገሮች ያለንን እይታ አዎንታዊ ሲሆን፣ የምንወስዳቸው እርምጃዎች ሁሉ ሌሎችን የማይጎዱ እና የሚጠቅሙ ይሆናሉ። በውስጣችን የምናሰላስለው በጎ ነገር ውሎ አድሮ ወደ ተግባር በመቀየር ለሌሎች መርህና አርአያ እንድንሆን ይረዳናል። መልካም የሚያስብ አእምሮ ከቅናት፣ ከጥላቻና ካልተገባ ምኞት የጸዳ ስለሚሆን ለራስም ትልቅ የሰላም ምንጭ ነው። በተለይ ለቀጣዩ ትውልድ የምናስተላልፈው ትልቁ ቅርስ ቢኖር፣ በቅንነትና በታማኝነት ላይ የተገነባ አስተሳሰብን ነው። መልካም ሀሳብ ወደ መልካም ንግግር፣ መልካም ንግግር ደግሞ ወደ መልካም ተግባር ያመራል ማለት ነዉ።

"ሙስና የሀገር ዕድገት ደንቃራ ነው!" 🌿🌿🌿🌿🌿 ሙስና የሀገር ሀብትን በጥቂት ሰዎች እጅ በመሰብሰብ የብዙሃኑን የወደፊት ተስፋ ያጨልማል። ዛሬ ሙስናን ለመታገል የምንሰበስበው እጅ፣ የነገውን
"ሙስና የሀገር ዕድገት ደንቃራ ነው!" 🌿🌿🌿🌿🌿 ሙስና የሀገር ሀብትን በጥቂት ሰዎች እጅ በመሰብሰብ የብዙሃኑን የወደፊት ተስፋ ያጨልማል። ዛሬ ሙስናን ለመታገል የምንሰበስበው እጅ፣ የነገውን የልጆቻችንና የሀገራችን ተስፋ ያጨልማል፡፡ ተስፋው የጨለመ ትውልድ ደግሞ የቤተሰቡና የሀገሩ ሽክም ከመሆኑም በላይ በአቋራጭ መክበርን እንጂ ወጥቶ ወርዶ ውጤታማ መሆንን በፍጹም አይሻም፡፡ ስለዚህ የልጆቻችን ተስፋ እንዳይጨልም እና ሰርቶ በማግኘት የሚያምን ትውልድ እንዲፈጠር ሁላችንም የድርሻችንን መወጣት ግዴታችን መሆኑን ልብ ልንል ይገባል:: #በመሠረት ተስፋዬ

ፅኑ ሥነ-ምግባር የትውልድ ብርሃን ነው! 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 «ፅኑ ሥነ-ምግባር የትውልድ ብርሃን ነው!» የሚለው መልክት የሞራልና የሥነ-ምግባር እሴቶች ለአንድ ህብረተሰብ እና ለሀገር ህልውና ያላቸውን መሰረታዊ ሚና በአጭርና በኃይለኛ መንገድ የሚገልጽ ጥልቅ ፍልስፍናዊ መልእክት አለው። «ፅኑ» ሲባል በደስታም ሆነ በፈተና፣ በጥቅም አጋጣሚም ሆነ በችግር ጊዜ የማይለወጥ፣ ለሙስና፣ ለሌብነትና ለብልሹ አሰራር እጅ የማይሰጥ ጠንካራ የሞራል አቋምን ያሳያል። ህግና ተቆጣጣሪ በሌለበት ቦታ እንኳን ሳይቀር አንድ ሰው ትክክለኛውን ነገር ብቻ እንዲሰራ የሚያደርግ የህሊና ዳኝነት ነው። በህብረተሰብ ውስጥ የሚታዩ እንደ ሌብነት፣ ማታለል፣ መዋሸትና የራስን ጥቅም ብቻ ማሳደድ ያሉ እኩይ ተግባራት «የሞራል ጨለማዎች» ናቸው። ፅኑ ሥነ-ምግባር ግን ይህንን ጨለማ ገፎ እውነትንና ፍትህን የሚያበራ መብራት ነው። አሁን ያለው ትውልድ የሚያሳየው መልካም ሥነ-ምግባር ለሚቀጥለው ትውልድ እንደ ታላቅ የእግር መንገድና የብርሃን አቅጣጫ ሆኖ ያገለግላል። ሥነ-ምግባር ያለው ትውልድ በስራ ቦታ፣ በማህበራዊ ህይወት እና በመንግስት አገልግሎት ውስጥ ግልጽነትና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ያደርጋል። ያለ ሥነ-ምግባር የሚገነባ የትኛውም ቁሳቁሳዊ እድገት ወይም እውቀት በሌብነትና በብልሹ አሰራር ምክንያት በቀላሉ ይፈራርሳል። ሥነ-ምግባር ግን የእድገት ሁሉ ፅኑ መሰረት ነው። በአጠቃላይ ቃሉ «እውቀትና ስልጣን ያለ ሥነ-ምግባር ጨለማና አጥፊ ሲሆኑ፤ በፅኑ ሥነ-ምግባር የተገነባ ትውልድ ግን ሀገርንና ህዝብን ወደተሻለ ብርሃናማ ምዕራፍ ይመራል» የሚል መልእክት አስተላልፋል።

ሌብነት፣ ማታለልና መዋሸት ትልቅ የሞራል ጨለማዎች ናቸው። 🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ሌብነት፣ ማታለልና መዋሸት የሰው ልጅን ማህበራዊ፣ ስነ-ልቦናዊ እና መንፈሳዊ ህይወት የሚያፈራርሱ ትልልቅ የሞራል ጨለማዎች ናቸው። እነዚህ ነውረኛ ድርጊቶች እርስ በእርስ የተሳሰሩና የአንድን ህብረተሰብ የእሴት መሰረት የሚሸረሽሩ ናቸው። እነዚህ እኩይ ተግባራት የሚያደርሱት ችግር፦ ➽ የእምነት እና የልቦና መፍረስ ያመጣሉ። የማንኛውም ህብረተሰብ፣ ቤተሰብ ወይም ተቋም መረጋጋት እና እድገት የተገነባው በእምነት ላይ ነው። መዋሸት የእውነትን ብርሃን ይሸፍናል፤ በሰዎች መካከል ያለውን የመተማመን ድልድይም ይሰብራል። ማታለል የሰዎችን ቅንነትና የልብ ግልጽነት አላግባብ በመጠቀም ተስፋንና እምነትን ያኮስሳል። ሌብነት ደግሞ የሰዎችን ልፋት፣ ሀብትና መብት በግፍ በመንጠቅ ፍርሃትንና መጠራጠርን ይዘራል። እምነት በጠፋበት ማህበረሰብ ውስጥ ፍቅር፣ ሰላም እና አብሮነት አይኖርም። ➽ የፍትህ እና የእኩልነት መዛባት ያስከትላሉ። እነዚህ ድርጊቶች የሰዎችን ህጋዊ እና ተፈጥሮአዊ መብት ይጋፋሉ፡- ሌብነት የሌላውን ልፋትና ጥረት በነጻ ለመውሰድ የሚደረግ ስግብግብነት በመሆኑ ኢ-ፍትሃዊነትን ያነግሳል። ማታለል እና መዋሸት ሰዎችን ትክክለኛ መረጃ በመከልከል የተሳሳተ ውሳኔ እንዲወስዱ ያደርጋሉ፤ ይህም ሰለባዎቹን ለአእምሯዊና ለአካላዊ ጉዳት ይዳርጋል። ➽ የስነ-ልቦና እና የባህሪ ውድቀት ይከሰታል። አንድ ሰው መዋሸት፣ ማታለልና መስረቅ ሲጀምር የውስጥ ህሊናው መንፈሳዊና ሞራላዊ ውጊያ ውስጥ ይገባል። ድርጊቱ እየደጋገመ ሲሄድ ህሊና ደንዝዞ ለጥፋት እጅ ይሰጣል። ውሸትና ማታለል ሌላ ተጨማሪ ውሸትን ስለሚጠይቁ ግለሰቡን የማይወጣበት የስነ-ልቦና ጨለማና ስጋት ውስጥ ይከተዋል። ➽ የማህበራዊ እና የኢኮኖሚ እድገት ጸር ይሆናሉ። በሀገር ደረጃ ሲታይ ሌብነት፣ ማታለልና ውሸት የህዝብን ሀብት በማባከን፣ ፍትህን በማዛባት እና የስራ ባህልን በመግደል ሀገርን ወደ ድህነትና ምስቅልቅል የሚከቱ ትልልቅ እንቅፋቶች ናቸው። በአጠቃላይ እውነት፣ ታማኝነት እና ቅንነት የብርሃን መንገዶች ሲሆኑ፤ ሌብነት፣ ማታለልና መዋሸት ደግሞ የሰውን ልጅ ክብር የሚያስገፉ፣ ህሊናን የሚያጨልሙና ማህበረሰብን የሚያፈርሱ የሞራል ጨለማዎች ናቸው።