en
Feedback
ሰዋስወ ብርሃን ቅ/ጳ/ገዳም ሰንበት ት/ቤት (Official)

ሰዋስወ ብርሃን ቅ/ጳ/ገዳም ሰንበት ት/ቤት (Official)

Closed channel
649
Subscribers
-224 hours
-37 days
-530 days
Posts Archive
የበገና ተማሪዎች የምርቃት መርሐግብር የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰ/ት/ቤት ባሳለፍነው የ2018 ዓ.ም ለ10 ወራት ያስተማራቸውን የበገና ተማሪዎች በታላቅ ድምቀት አስመረቀ በትናንትናው ዕለት ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም በነበረው የምርቃት መርሐግብር ለ16 ኛ ዙር የተማሩ 59 ተማሪዎች ተመርቀዋል:: በመርሐግብሩ ቃለ እግዚአብሔር ,በግል የበገና ዝማሬ እንዲሁም በተመራቂ ተማሪዎች የበገና ዝማሬዎች ቀርበዋል:: በምርቃቱ ተጋባዥ አባቶች,መምህራነ ወንጌል,በርካታ የተመራቂ ተማሪዎች ወላጆች,ተመራቂ ተማሪዎችና የሰንበት ት/ቤታችን አባላት ተሳትፈዋል:: በመጨረሻም ለ2019  የትምህርት ዘመን የበገና ትምህርት ለማስተማር ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን መማር ለምትፈልጉ በሙሉ ሰንበት ት/ቤታችን ምዝገባ ላይ መሆኑን እንገልፃለን::

ዐዲሱ ምንድነው? ምንድነው ዐዲሱ በዐዲሱ ዓመት ሰማዩ ወይ ምድሩ ወይስ የቆምንበት የተፈጠርንበት ጽኑ ግዙፍ መሬት ወይስ የአበቦች የጽጌያት መምጣት? መስከረም ወይ ጥቅምት የአበባ ወራት የአደይ አበባ የሚያበራባቸው በየዓመት ዓመት ምንድነው ዐዲሱ ይኾን ወይ ዮሐንስ የበረሃው ጀግና የምናኔው ንጉሥ አንገቱን የሰጠው ለቃለ ክርስቶስ እሱን ይኾን ወይ ዐዲስ? ዐዲስ ያልከኝ ማነው? ዐዲስ ዓመት ስትል ሉቃስ ነው ሐኪሙ ወይስ የርሱ ሥዕል የቱን ነው ንገረኝ ቀኑ ነው ሰዓቱ ፀሓይ የምትወጣ የምትገባበቱ የምትለኝ ዐዲስ ምን ዐዲስ ነው ኖሮ  ነፋሱም ዝናሙም ቁሩም እንደድሮ ሰማዩ እንዳለ ነው ጽርሐ አርያሙ ምድሩም ደከመ እንጂ አልጠፋም ቀለሙ ኹሉም እንዳለ ነው የሥላሴ ፍጥረት ተከታይ ሠላሳ የመስከረም ጥቅምት ወፎቹም እንዳሉ አለች አደይቱ እንደ ድሮ ጥንቱ ከሰሎሞን በላይ ያማሩት አበቦች እንደድሮ አሉ አምላክ አስውቦናል እዩማ እያሉ የበረሃው ኮከብ መጥምቅ ዮሐንስም በአባቱ ፈለግ በሰይፍ መሞቱ ዛሬ አልተለወጠም እንደ ቀድሞው ጊዜ እንደ ቀድሞው ዘመን ዛሬም ይሰብከናል ከዝሙት እንድንድን ሰማዕትነቱም አይደለችም ዐዲስ የሰማዕታቱ ደም ዛሬም ስለምትፈስ። በሉቃስም እጆች ዛሬም ይሣላሉ የማርያም እቅፍ የጌታ አካሉ የታመሙም ልቦች በሐኪሙ ቅዱስ ዛሬም ይድናሉ። ቅዱሳኑ ኹሉ እንደ አምላክ ናቸው ዮሐንስም ሉቃስ ዐዲስ ቃል አይሰጡም ሌላ ከክርስቶስ። ከዘመን ቁጥሩ ከቅዱሱ ሌላ ዐዲስ ነገር ማየት መፍጠሩ ካሰኘህ ከአሮጌው በኋላ.... በአርባ በሰማንያ ወዳለቺው አካል ወደ ሐዳሲቱ የጌታ ሰውነት አካልህን መልስ ዛሬ በዚህች ዕለት በዚህች ቅዱስ ሰዓት። በብክነትህ ብዛት የደከመቺውን ያንተን ውብ ገጽታ በንስሓ ዐድስ ሳይመጣ ምሽቱ ሳትከሠት ማታ። ዐዲስ ቀን ፍለጋ ለምን ትደክማለህ? ክብርህን ወደ ዐዲስ መለወጫው ቅመም ንስሓ እያለልህ! ተነሥና ዛሬ ኺድ ወደ ካህኑ ልብህ ነፍስህ ክብርህ ዐዳዲስ ይኹኑ! በዐዲሱ ዘመን ዐዲስ ከመፈለግ ተከትለህ ተነሥ የጴጥሮስን ፈለግ! በዐዲሱ ዓመት በጳጕሜን መነሻ ዛሬ ቊረብና ዐዲስ ትኹንልህ የአካልህ ሐሳብ የአካልህ ልቡና! ያደፈውን አካል በጌታ አምላክህ ፊት ዕጠበው በዕንባ ዐዲሲቷ አገር ገነት እንድትገባ። ዐዲስ ዘመንና ብዙ ዐዳዲስ ኬክሮስ ምን ያስፈልግሀል እያለ ዐዲሱ ንጹሑ ክርስቶስ በሥጋና ደሙ ተዋሐደውና አካላቱን ልበስ። ሌላ ዐዲስ የለም ያለፈቸው ዘመን ካለፈች በኋላ ካንተይቱ አካል ሰውነትህ ሌላ። እሱንም ራስህ ተነሥና አድሰው ! ይህን የሚፈጽም የለህም ሌላ ሰው ። በቃ ወስንና አግኝ ዐዲስ አካል በዮሐንስ ስብከት በበረሃው ሰው ቃል። ዐዲሱን ሰውነት አካሉን ለማግኘት ፍጹም የለብህም ዶሮ ማረድና አካሏን መበለት... ተዘጋጅቶልሀል የታረደልህ በግ እርሱን ብላውና ዐዲስ አካል አግኝ ወደ አካሉ እደግ! ✍ ተጽሕፈ በአቤል ፈታ (ዲ/ን) አመ አሚሩ ለጳጒሜን ፳፻ወ፲፰ ዓ.ም

የተወደዳችሁ የሰ/ት/ቤታችን የቀን እና የማታ ተማሪዎች ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን። ካሳለፍነው ሰኞ ጀምሮ ውጤት ስናሳይ መቆየታችን የሚታወቅ ነው። ስለሆነም ዛሬ እና ነገ ‼️የመጨረሻ ቀ
+1
የተወደዳችሁ የሰ/ት/ቤታችን የቀን እና የማታ ተማሪዎች ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን። ካሳለፍነው ሰኞ ጀምሮ ውጤት ስናሳይ መቆየታችን የሚታወቅ ነው። ስለሆነም ዛሬ እና ነገ ‼️የመጨረሻ ቀን‼️በመሆኑ ማንኛውም ተማሪ ዛሬ(ቅዳሜ 12:00 - 1:30) እንዲሁም እሑድ ጠዋት (3:00 - 4:30) እና ከሰዓት (9:00 - 11:00) ባለዉ ጊዜ መቶ ውጤቱን ማየት እንደሚችል በትህትና እንገልጻለን። የትምህርት እና ሥልጠና ሥራ አስፈጻሚ

ለ2019 ዓ.ም የመስቀል መዝሙርና ትርዒት አጥኚዎች በ2019 ዓ.ም የመስቀል መዝሙርና ትርዒት በማዕከል እንድታጠኑ የተመረጣችሁ እና ጥናት የጀመራችሁ አባላት በሙሉ በአገልግሎቱ ዙርያ ኦረንቴሽን ስላ
ለ2019 ዓ.ም የመስቀል መዝሙርና ትርዒት አጥኚዎች በ2019 ዓ.ም የመስቀል መዝሙርና ትርዒት በማዕከል እንድታጠኑ የተመረጣችሁ እና ጥናት የጀመራችሁ አባላት በሙሉ በአገልግሎቱ ዙርያ ኦረንቴሽን ስላለ ነገ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ሰዓት በሰንበት ት/ቤቱ ፅ/ቤት እንድትገኙ እያሳሰብን በገለፃው የማይሳተፍ አባል የመዝሙር ጥናቱን የማይቀጥል መሆኑን እናሳስባለን።

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰ/ት/ቤት በ2018 ዓ.ም ባለፉት 10 ወራት ያስተማራቸውን የበገና ተማሪዎች ሊያስመርቅ ነው:: የምርቃት መርሐግብሩ የፊታችን ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ
የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰ/ት/ቤት በ2018 ዓ.ም ባለፉት 10 ወራት ያስተማራቸውን የበገና ተማሪዎች ሊያስመርቅ ነው:: የምርቃት መርሐግብሩ የፊታችን ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ በ7:30 በሰንበት ት/ቤቱ አዲሱ አዳራሽ ይከናወናል:: በመርሐግብሩ በሁለት ፈረቃ የተማሩ 59 ተማሪዎች የሚመረቁ ይሆናል በኘሮግራሙ ተመራቂ ተማሪዎችና ወላጆች,ተጋባዥ መምህራንና ዘማሪያን ይገኛሉ:: ከዚህ በተጨማሪ በዕለቱ በ2019 ዓ.ም የበገና ትምህርት ለመማር የሚፈልጉ ምዕመናን እና የሰንበተሰ ት/ቤቱ አባላት የምዝገባ ኘሮግራም ተይዞል::

የቀን ከራብዓይ እስከ ሳድሳይ እና ከቀዳማይ እስከ ኃምሳይ የማታ ያላችሁ ተማሪዎች ጠቅላላ ውጤት ተሠረቶ ስላለቀ በነሐሴ 27 - 30 (ከረቡዕ እስከ ቅዳሜ) ትምህርት እና ሥልጠና ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ
የቀን ከራብዓይ እስከ ሳድሳይ እና ከቀዳማይ እስከ ኃምሳይ የማታ ያላችሁ ተማሪዎች ጠቅላላ ውጤት ተሠረቶ ስላለቀ በነሐሴ 27 - 30 (ከረቡዕ እስከ ቅዳሜ) ትምህርት እና ሥልጠና ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ ዲ.ን ዮሐንስ ዳዊት ብላችሁ ውጤታችሁን እንድታረጋግጡ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ ውጤቱን በወቅቱ ተገኝቶ ላላረጋገጠ ለሚከሰት ችግር ሥራ አስፈጻሚው ኃላፊነት አይወስድም።

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ እያልን የ 2019 ዓ.ም የመስቀል በዓልን አገልግሎት ለማገልገል እንደገናም በጋራ የሚደረገውን የማዕከል መዝሙር ጥናት መሳተፍ የምትችሉ በተጠቀሡት ስልኮች በመደወ
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ እያልን የ 2019 ዓ.ም የመስቀል በዓልን አገልግሎት ለማገልገል እንደገናም በጋራ የሚደረገውን  የማዕከል መዝሙር ጥናት መሳተፍ የምትችሉ በተጠቀሡት ስልኮች በመደወል እንዲሁም ከታች ባለው የቴሌግራም አካውንት ስማችሁን በመላክ መመዝገብ ይቻላል #ማሳሰብያ መሳተፍ የምትችሉት ከራብዓይ እስከ ወጣት ብቻ ነው ምዝገባ የመጨረሻ እስከ ዛሬ ነሀሴ 24 ማታ 3:00 @Tibebu_tensae መዝሙርና በዓላት ከሰው ኃይል ስራ አስፈፃሚ

የቀን ከቀዳማይ እስከ ሣልሳይ ያላችሁ ተማሪዎች ጠቅላላ ውጤት ተሠረቶ ስላለቀ በነሐሴ 25 - 30 ትምህርት እና ሥልጠና ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ ዲ.ን ዮሐንስ ዳዊት ብላችሁ ውጤታችሁን እንድታረጋግጡ እናሳ
የቀን ከቀዳማይ እስከ ሣልሳይ ያላችሁ ተማሪዎች ጠቅላላ ውጤት ተሠረቶ ስላለቀ በነሐሴ 25 - 30 ትምህርት እና ሥልጠና ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ ዲ.ን ዮሐንስ ዳዊት ብላችሁ ውጤታችሁን እንድታረጋግጡ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ ውጤቱን በወቅቱ ተገኝቶ ላላረጋገጠ ለሚከሰት ችግር ሥራ አስፈጻሚው ኃላፊነት አይወስድም።