Roots and Wings Ethiopia
Open in Telegram
Non-Governmental Organisation (NGO) 💻 https://www.rootsandwingsglobal.org/ ☎️ +251911634301
Show moreEthiopia15 055The category is not specified
400
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+7130 days
Posts Archive
እጆች ሲናገሩ ዓለም ያዳምጣል!
ቤቲ ሽታሁን ትባላለች በ 4 ዓመቷ ነው መስማት እንደማትችል ቤተሰቦቿ የተረዱት። በትምህርት ቤት ስትጀምርም ክፍል ውስጥ ብትገኝም አንድ ቃል መረዳት አልቻለችም ነበር። የክፍል ጓደኞቿ ሲያወሩ እና ሲሳሳቁ ብትመለከትም ተቀላቅላ መጫወት ግን አልቻለችም።
አንደኛ ክፍልን እንኳን ለማለፍ 3 ዓመት ፈጅቶባታል። ቤቲ ትምህርት ቤት በመቀየሯ የተሻለ እድል አገኘች።
ህልሟ ዶክተር መሆን እና ላጋጠማት እክል መፍትሔ ለማግኘት ነበር።
ዩኒቨርሲቲ ስትገባ ግን ዳግም ሁሉም ነገር ተለወጠ።
🔹 አስተርጓሚ በሌለበት፤ ድጋፍ በማታገኝበት ለመማር ምንም ምቹ ሁኔታ በሌለበት ትምህርቷን ጀመረች፤
🔹 አንዳንድ መምህራን "ለምን ወደዚህ መጣሽ ካልሰማሽ ሐኪም መሆን አትችይም" ብለው ተናገሯት፤
🔹በዚህም ተስፋ ቆርጣ ለአንድ አመት ቤት ቆየች።
💡 ቤቲ ግን ዝም ለማለት ፈቃደኛ አልሆነችም።
ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ቤት ዝውውር በማድረግ ትምህርቷን ጀመረች። በዚህ ጊዜም ለሌሎች ድምጽ ለመሆን ወሰነች። ዛሬ፣ መስማት ለተሳናቸው ታዳጊ ሴቶች ልምዷን በማካፈልና በተለያዩ እንቅስቃሴዎች ላይ ከሩትስ ኤንደ ዊንግስ ጋር በጋራ ትሰራለች።
"መስማት የተሳናቸው ታዳጊ ሴቶች፣ ልክ እንደ ሁሉም ታዳጊ ሴቶች ትምህርት ቁልፍ ነገር ነው። ታሪኬ የእኔ ብቻ ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያ ውስጥ መስማት የተሳናቸው ሴቶች ጭምር ነው።" ትላለች።
📢 የቤቲ እና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሴቶች ድምጽ እንዲሰማ ይህን እናጋራ!
#DeafGirlsMatter #HandsSpeakEyesListen #EducationForAll
📢 ጥራት ያለው ትምህርት መስማት ለተሳናቸው ታዳጊ ሴቶች፡ መብት እንጂ ችሮታ አይደለም! 👐📚
🔹 በኢትዮጵያ ከሚገኙት መስማት የተሳናቸው ህጻናት 10 በመቶ ያህሉ ብቻ ናቸው የትምህርት እድል የሚያገኙት።
🔹 የምልክት ቋንቋ መምህራን እጥረት እና ቋንቋው እንደ ኦፊሺያል ቋንቋ አለመታወቁ ብዙዎች እንዳይማሩ አድርጓቸዋል።
🔹 መስማት የተሳናቸው ታዳጊ ሴቶች ላይ የሚደርሰው መገለል፣ አድሎና እና የቤት ውስጥ ጫና የወደፊት ህይወታቸው ላይ ጥቁር ጠባሳ ሆኗል።
💡 ጊዜው ለውጥ ይፈልጋል! መስማት የተሳናቸው ልጃገረዶች አቅማቸውን ለማሳካት በቤት እና በትምህርት ቤት እኩል ዕድል ተጠቃሚ መሆን አለባቸው።
ሩትስ ኤንደ ዊንግስ እና ማላላ ፈንድ ይህንን በመደገፍ ረገድ ለውጥ የሚፈጥሩ ሥራዎችን እየሰሩ ይገኛሉ።
✅ 500+ በላይ በምልክት ቋንቋ ማሰልጠን ተችሏል 🗣
✅ ፈጠራን የሚያበረታቱ የመማሪያ ቦታዎች እንዲኖሩ የተለያዩ የጥበብ ሥራዎችን (Mural Art) እንዲሁም የሥዕል ውድድሮችን አካሂዷል
🎨
✅ በ73+ ክፍሎች የተዘጋጀና በመማሪያ መጽሐፍ ላይ የተመሰረተ የምልክት ቋንቋ መማሪያ ቪዲዮዎች ተዘጋጅተው መስማት ለተሳናቸው ትምህርት ቤቶች ተሰራጭተዋል:: 🎥📚
✅ ለመምህራን፣ ለትምህርት ቤት አመራሮች እና ሰራተኞች ቀጣይነት ያለው ስልጠና ተሰጥቷል 👩🏫
✅ መስማት የተሳናቸውን ተማሪዎች ለማብቃት የክህሎት ስልጠና ተሰጥቷል 📖
✅ ተማሪዎችን አርዓያ መሆን ከሚችሉ መስማት የተሳናቸው ግለሰቦች ጋር የሚያገናኙ ፕሮግራሞች ተዘጋጅተዋል፡፡
🚀 ይህንን እንቅስቃሴ ይቀላቀሉን! ድምጻቸው ለማይሰማ ታዳጊ ሴቶች ድምጽ በመሆን እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ አብረን እንስራ! ለውጥ ከዚህ ይጀምራል! 💙
#HandsSpeakEyesListen #EducationForAll #SignLanguageRights
🔹 "Hands Speak, Eyes Listen" – Breaking Barriers for Deaf Girls! 🔹
For years, this powerful message has driven change, and today, it's shaping a success story! 🌍✨ Roots and Wings, in collaboration with Malala Fund and Special Schools for the Deaf, is working on:
📢 Raising Awareness
✊ Advocating for Inclusion
📚 Ensuring Quality Education
Join our Telegram channel and help us ensure that sign language is recognized on par with spoken language—and that deaf girls receive quality education, just like their peers. 👐💙
Join our telegram channel https://t.me/RWethiopia
#HandsSpeakEyesListen #DeafGirlsMatter
✅Roots and Wings ELIXIR : What inspires you for the future of deaf girls?
✅Rediet Tariku: “As an Ethiopian Deaf woman who has struggled to overcome many barriers since losing my hearing at the age of 16, I have persevered to complete my undergraduate studies, pursue advanced education, and work as a Disability Inclusion Officer at a UN agency.
What inspires me for the future of Ethiopian Deaf girls is the growing recognition of their rights and potential. With advancements in sign language recognition, inclusive education, employment opportunities, and accessibility, I envision a future where no Deaf girl in Ethiopia has to fight for the basics but instead thrives in a society that values and embraces her abilities. I want to be part of this change, ensuring that future generations of Ethiopian Deaf girls know that success is not just possible - it is theirs to claim.”
For All women & Girls: Rights, Equality, Empowerment!
#InternationalWomenDay2025 #DeafWoman #Inclusion #RoleModel
✅ Roots and Wings : What inspires you for the future of Deaf girls?
✅ Bethelhem Shitahun : "The future of Deaf girls is full of endless possibilities. What inspires me the most is seeing Deaf girls confidently embracing who they are, breaking down barriers, and pursuing their dreams without limitations. It’s essential that we continue to create spaces where they can shine, be heard, and lead. This world needs our unique perspectives, talents, and voices."
#InternationalWomenDay2025 #DeafWoman #Rolemodel
ጥራት ያለው ትምህርት መስማት ለተሳናቸው ታዳጊ ሴቶች!
ሁሉም መስማት የተሳናቸው ታዳጊ ሴቶች የመማር እና የእኩል ተጠቃሚነት መብት አላቸው።
ሩትስ ኤንደ ዊንግስ መስማት የተሳናቸው ታዳጊ ሴቶች በትምህርት፤ በጤና፤ እንዲሁም በስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየታገለ ይገኛል።
🚀 ተልዕኮ
✅ ለህብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ ማስጨበጥ 📢
✅ የተለያዩ ንቅናቄዎችን መፍጠር ✊
✅ እውነተኛ ለውጥ እንዲመጣ መታገል 🌍
ኑ! የኢትዮጵያ የምልክት ቋንቋ እንደ ብሔራዊ ቋንቋ የሚቆጠርበትንና ማንም በቋንቋ የተነሳ የማይበደልበትን ነገን እንገንባ!
#DeafGirlsMatter #EducationForAll #InclusionNow #SignLanguageRights
