የወሎ ድምፅ/Voice Of Wollo
Open in Telegram
በዚህ የቴሌግራም ቻናል ትክክለኛና ጠቃሚ የሆኑ አጠቃላይ በወሎ ፖለቲካዊ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁነቶችንን እናቀርባለን። የቻናላችን አባል ይሁኑ
Show more5 803
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#ወሎ|| #ወረባቦ "መሪን በመግደል የሚቆም ትግል የለም!"
………………………………
በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ በቅርቡ በአቶ ግርማ የሺጥላ ላይ የተከሰተውን መሰዋእትነት የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ።
መሪን በመግደል የሚቆም ምንም አይነት ትግል የለም፤ ፅንፈኝነት ለክልላችን እና ለሃገራችን ብልፅግና ሳንካ መሆኑን አዉቀን እንታገላለን፤ የሃገር መከላከያ ሰራዊት ዋስትናችን ነዉ፤ ለክብሩም ደጀን እንሆናለን፣ ህብረ ብሄራዊ ወንድማማችነት እና እህትማማችነትን በማጎልበት ለኢትዮጵያ አንድነት መትጋት አለበት ሲሉ በሰልፉ ላይ ጠይቀዋል።
በመጨረሻም ስልፈኞቹ የአቶ ግርማን እና የእነ ዶ/ር አምባቸዉን ህልም ለማሳካት ዘወትር እንተጋለን በቀጣይ መንግስትን ህግ የማስከበር ስራ አጠናክሮ እንዲቀጥል እንፈልጋለን፤ እኛም እናግዛለን በማለት ገልጸዋል።
#ወሎ|| ደሴ ዙሪያ ወረዳ፦
በደቡብ ወሎ ዞን በደሴ ዙሪያ ወረዳ በቅርቡ በአቶ ግርማ የሺጥላ ላይ የተከሰተውን መሰዋእትነት የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ።
መሪን በመግደል የሚቆም ምንም አይነት ትግል የለም፤ ፅንፈኝነት ለክልላችን እና ለሃገራችን ብልፅግና ሳንካ መሆኑን አዉቀን እንታገላለን፤ የሃገር መከላከያ ሰራዊት ዋስትናችን ነዉ፤ ለክብሩም ደጀን እንሆናለን፣ ህብረ ብሄራዊ ወንድማማችነት እና እህትማማችነትን በማጎልበት ለኢትዮጵያ አንድነት መትጋት አለበት ሲሉ በሰልፉ ላይ ጠይቀዋል።
በመጨረሻም ስልፈኞቹ የአቶ ግርማን እና የእነ ዶ/ር አምባቸዉን ህልም ለማሳካት ዘወትር እንተጋለን በቀጣይ መንግስትን ህግ የማስከበር ስራ አጠናክሮ እንዲቀጥል እንፈልጋለን፤ እኛም እናግዛለን በማለት ገልጸዋል።
#ወሎ|| መንግስት የህግ የበላይነትን በማስከበር አስተማማኝ ሠላም የማስፈን ኃላፊነቱን እንዲወጣ በደቡብ ወሎ ዞን የሚገኙ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ‼
በዞኑ በሚገኙ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የተካሄደው በአማራ ክልል መሪዎች እየተፈጸመ ያለውን ተደጋጋሚ ግድያ የሚያወግዝ ሰልፍ በሰላም መጠናቀቁን የዞኑ አስተዳደር አስታውቋል።
ደሴ - ሚያዚያ 27/2015 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን)
በደቡብ ወሎ ዞን በሚገኙ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች በአማራ ክልል መሪዎች እየተፈፀመ ያለውን ተደጋጋሚ ግድያዎች የሚያወግዝ ሰልፍ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል፡፡
በአማራ ክልል በቅርቡ በጭካኔ የተገደሉት የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ ግርማ የሺጥላን ጨምሮ በሌሎች መሪዎች ላይ ግድያ መፈጸሙ ይታወቃል፡፡ እናም ግድያዎቹንና በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች ሠላምን የሚያውኩ ድርጊቶችን ለማውገዝ ነው ኅብረተሰቡ ሰልፍ ያካሄደው፡፡ በሰልፉም ሴቶች፣ ወጣቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈውበታል፡፡
በመገዳደል የሚገኘው ጥፋት እንጅ አንዳችም ለውጥ እንደማይመጣና ይልቁንም ወደ እርስ በእርስ መተላለቅ እንደሚያስገባ በሠልፉ የተሳተፉት የኩታበር ወረዳና የሌሎች ወረዳ ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ዓለም በሰለጠነበት ዘመን ሐሳብን በዴሞክራሲያዊ መንገድ ማራመድና ችግሮችን በውይይት መፍታት እንጂ ጠመንጃ ማንሳት ኋላቀርነትና የአማራን ክብር የሚመጠን አይደለም ነው ያሉት ነዋሪዎቹ፡፡ መንግስትም የህግ የበላይነትን በማስከበር አስተማማኝ ሠላምን የማረጋገጥ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል፡፡ሠላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው እንቅስቃሴም ሕዝቡ ኃላፊነቱን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑንም ነው የሠልፉ ተሳታፊዎች ያረጋገጡት፡፡
የአማራ ሕዝብ በወረራው ሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ስነ ልቦናዊ ቀውስ ውስጥ መቆየቱ ሳያንሰው አሁንም በሰላም እጦት ውስጥ በመሆኑ በተረጋጋ መንገድ ወጥቶና ሠርቶ ለመግባት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ስለሆነ ፓርቲውም ሆነ መንግስት ሠላማዊ በሆነ መንገድ በንግግር እንዲፈታ ፍላጎት ኖሯቸው ጥረት ቢያደርጉም አልተሳካም ያሉት የደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር የህዝብ ግንኙነት፣ ተሳትፎና አደረጃጀት አማካሪ አቶ አሊ መኮንን ናቸው፡፡
የአማራን ሕዝብ መሠረታዊ ጥያቄዎች ከሌሎች ጓዶቻቸው ጋር በመሆን በብቃት ምላሽ እንዲያገኙ እየሠሩ የነበሩ በቅርቡ በታጣቂዎች የተገደሉት አቶ ግርማ የሺጥላን ጨምሮ ሌሎች መሪዎችን ክልሉ በሞት ያጣ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
እናም አሁን በሰለጠነው ዘመን ጉዳዮችን በንግግርና በውይይት እንጂ በጠመንጃ መሆን እንደሌለበትና ግድያ መቆም እንዳለበት ህዝቡ ባካሄደው ሰልፍ ገልጿል ነው ያሉት አቶ አሊ፡፡ ህዝቡ በሠላም ወጥቶ በሠላም እንዲገባ የክልሉና የፌዴራል መንግስት የህግ የበላይነትን እንዲያስከብሩለትም መጠየቁም ተብራርቷል፡፡ ህዝቡ የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ ለማበርከት ዝግጁ መሆኑን በመጠቆም፡፡
ነገሮችን በውይይት መፍታት እየተቻለ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚገኙ የተለያዩ አካላት በማኅበራዊ ሚዲያ የአማራ ሕዝብ እርስ በእርሱ እንዲጋጭና ከሌሎች ወንድምና እህት ከሆኑ ህዝቦች ጋር በፍቅርና በአንድነት እንዳይኖር የሚያደርጉት ቅስቀሳ ተቀባይነት እንደሌለውና መንግስትም አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ እንደሚገባው ሕዝቡ ባደረገው ሠልፍ መጠየቁን አቶ አሊ አመላክተዋል፡፡
አገርን ከመፍረስ የታደገ ለሀገር ሉዓላዊነት ሕይወቱን አሳልፎ የሰጠ ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊትን ስም የሚያንቋሽሹ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ኅብረተሰቡ በሰልፉ ድምፁን ገልጸዋል፡፡
በሀገር ደረጃ ያሉ ችግሮችም ሆኑ የአማራ ሕዝብ መሠረታዊ ጥያቄዎች ምላሽ የሚያገኙት ኅብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ሥር እንዲሰድና እንዲጎለበት በማድረግ ላይ የተመሠረት አቅጣጫን በመከተል እንደሆነም ኅብረተሰቡ መልዕክት ማስተላለፉን አቶ አሊ አክለው አብራርተዋል፡፡
በዞኑ ካሉት 29 ወረዳዎች መካከል በ21 ወረዳዎች በ17 ማዕከሎች ከ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ የኅብረተሰቡ ክፍሎች በሰልፉ መሳተፋቸውን አማካሪው አቶ አሊ መኮንን አረጋግጠዋል፡፡
***
የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግባቸው አማራጮች ቀጣዮቹ አድራሻዎች ናቸው። ሊንኮቹን በመጫንና በመወዳጀት ፈጣንና ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ቤተሰባችን ይሁኑ!
ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Southwollozonecommunicationaffairoffice
ቴሌግራም፡ https://t.me/+zufNKt2lSgIwNGFk
ቲዩተር፡ https://twitter.com/WolloNews?t=Lrv74tG3nMkhl51mvR4_QA&s=09
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/p/Cb1bEhbK0hw/?utm_medium=copy_link
ዩቱዩብ፡ https://youtube.com/channel/UC5WAkOJxv-uE3HxyTQepVrA
ዌብ ሳይት፡ https://www.southwollocommunication.gov.et
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=547478990893057&id=100068928830750&mibextid=ZbWKwL
#አሚኮ||
በአማራ ክልል መሪዎች በተደጋጋሚ እየተፈጸመ ያለውን ግድያ እንዲሁም ሰላምን የሚያውኩ ድርጊቶች የሚያወግዝ ሰልፍ በደቡብ ወሎ ዞን በሚገኙ ወረዳዎችና ከተማ አሥተዳደሮች ተካሄደ።
በአማራ ክልል መሪዎች በተደጋጋሚ እየተፈጸመ ያለውን ግድያ እንዲሁም ሰላምን የሚያውኩ ድርጊቶች የሚያወግዝ ሰልፍ በደቡብ ወሎ ዞን የተካሄደው።
በዞኑ በሚገኙ ወረዳዎችና ከተማ አሥተዳደሮች በዛሬው ዕለት በተካሄደው ሰልፍ የተለያዩ የኀብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ ኾነዋል። ሃሳብ በሃሳብ እንጅ በጠመንጃ አይገነባም፣ ጠመንጃ ሀገር ያፈርሳል፣ መሪን በመግደል የሚቆም ምንም ዓይነት ትግል የለም፣ መንግሥትን ሕግ የማስከበር ሥራ አጠናክሮ እንዲቀጥል እንፈልጋለን፤ እኛም እናግዛለን!! ብለዋል በመፈክሮቻቸው።
ከደቡብ ወሎ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው በሰልፉ ላይ ሃሳብን በዴሞክራሲያዊ ትግል እንጅ አፈ ሙዝ የደካሞች ባህሪ ነው፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ዋስትናችን ነው፤ ለክብሩም ደጀን እንኾናለን፣ ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነትን በማጎልበት ለኢትዮጵያ አንድነት እንተጋለን የሚሉ መፈክሮች በሰልፎቹ ተስተጋብተዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
#ወሎ #ቃሉ ሀርቡ
በደቡብ ወሎ ዞን ሀርቡ ከተማ አስተዳደር በአማራ ክልል አመራሮች በተደጋጋሚ እየተፈጸመ ያለውን ግድያ እንዲሁም ሰላምን የሚያውኩ ድርጊቶች የሚያወግዝ ሰልፍ ተካሄደ።
በዛሬው ዕለት እየተካሄደ ባለው ሰልፍ የተለያዩ የኀብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ ሲሆኑ ሃሳብ በሃሳብ እንጅ በጠመንጃ አይገነባም፣ ጠመንጃ አገር ያፈርሳል፣ መሪን በመግደል የሚቆም ምንም ዓይነት ትግል የለም፣ መንግስትን ህግ የማስከበር ሥራ አጠናክሮ እንዲቀጥል እንፈልጋለን፤ እኛም እናግዛለን!! ሃሳብን በዴሞክራሲያዊ ትግል እንጅ አፈ ሙዝ የደካሞች ባህሪ ነው፣ የሃገር መከላከያ ሰራዊት ዋስትናችን ነው፤ ለክብሩም ደጀን እንሆናለን፣ ህብረ ብሄራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነትን በማጎልበት ለኢትዮጵያ አንድነት እንተጋለን የሚሉ መፈክሮች በሰልፎቹ ላይ ተስተጋብተዋል።
#ወሎ|| የወሎ ሕዝብ ማፊያና ፅንፈኛ ገዳይ ፋኖን መንግስት አደብ ያስይዝልን ብሏል!🙏
•••••••••••••••••••••
በአማራ ክልል አመራሮች በተደጋጋሚ እየተፈጸመ ያለውን ግድያ እንዲሁም ሰላምን የሚያውኩ ድርጊቶች የሚያወግዝ ሰልፍ በደቡብ ወሎ ዞን በሚገኙ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች እየተካሄደ ነው።
ደሴ - ሚያዝያ 27/2015 (ደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን)
በአማራ ክልል አመራሮች በተደጋጋሚ እየተፈጸመ ያለውን ግድያ እንዲሁም ሰላምን የሚያውኩ ድርጊቶች የሚያወግዝ ሰልፍ በደቡብ ወሎ ዞን በሚገኙ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች እየተካሄደ ነው።
በዞኑ በሚገኙ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች በዛሬው ዕለት እየተካሄደ ባለው ሰልፍ የተለያዩ የኀብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ ሲሆኑ ሃሳብ በሃሳብ እንጅ በጠመንጃ አይገነባም፣ ጠመንጃ አገር ያፈርሳል፣ መሪን በመግደል የሚቆም ምንም ዓይነት ትግል የለም፣ መንግስትን ህግ የማስከበር ሥራ አጠናክሮ እንዲቀጥል እንፈልጋለን፤ እኛም እናግዛለን!! ሃሳብን በዴሞክራሲያዊ ትግል እንጅ አፈ ሙዝ የደካሞች ባህሪ ነው፣ የሃገር መከላከያ ሰራዊት ዋስትናችን ነው፤ ለክብሩም ደጀን እንሆናለን፣ ህብረ ብሄራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነትን በማጎልበት ለኢትዮጵያ አንድነት እንተጋለን የሚሉ መፈክሮች በሰልፎቹ ላይ እየተስተጋቡ ነው።
#WOLLO|| «የወሎ ሕዝብ ችግር በሲፊክ ማህበር ብቻ አይፈታም።ጥያቄዎቻችንም መልስ አያገኙም።ወጣቱም ባሉባሌ ነገር ስራ ፈትቶ ባሉባሌ ነገር እየዋለ ነው። ለዩቲዩብ መሸቀያ በሚነዙ የረከሱ ወሬወችንና የማይጠቅሙ አጀንዳወችን እየተሸከመ ስለ ልማትና እድገት የሚያስብበት ጊዜና ሁኔታ እየጠፋ ነው!!»
@Ahmed Mohammednur
#WOLLO|| «የወሎ ሕዝብ ችግር በሲፊክ ማህበር ብቻ አይፈታም።ጥያቄዎቻችንም መልስ አያገኙም።ወጣቱም ባሉባሌ ነገር ስራ ፈትቶ ባሉባሌ ነገር እየዋለ ነው። ለዩቲዩብ መሸቀያ በሚነዙ የረከሱ ወሬወችንና የማይጠቅሙ አጀንዳወችን እየተሸከመ ስለ ልማትና እድገት የሚያስብበት ጊዜና ሁኔታ እየጠፋ ነው!!»
@Ahmed Mohammednur
የአማራ ክልል ህዝብ በሐገር መከላከያ ሠራዊት ግንባታ ያለውን ሚና የማጥፋት ሴራ⁉️
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
የአማራ ህዝብ ተቆርቋሪ ነን የሚሉ ጽንፈኞች የሐገር መከላከያ ሠራዊትን የአንድ ብሄር ተወላጅ ብቻ የተጠራቀሙበት በማስመሠል በየቀኑ ያለመታከት እየጮሁ ይገኛሉ። ከዚህም አልፈው የሐገር መከላከያ ሠራዊትን የኦነጎቹ ብርሀኑ ጁላ ፣የአብይ አህመድ እና የብልጽግና ፖርቲ ታዛዥና ተላላኪ ሠራዊት ነው በማለት እጅግ በሚያሳፍር ሁኔታ ያለመታከት ስሙን እያጠለሹ ይገኛሉ።
ነገር ግን እነዚህ የአማራ ህዝብ ጠበቃ ነን የሚሉ ጽንፈኞች እየፈፀሙት የሚገኘው ሴራ የአማራ ክልል ህዝብ በአሁኑ ሠአት በኢትዮጵያ የሐገር መከላከያ ሠራዊት ግንባታ ላይ ያለውን ጉልህ ድርሻ እና ሚና የመደፍጠጥ እና የማጥፋት ሴራ ነው። በየቀኑ ውሸትን ደጋግሞ ወደ ሠው ጆሮ በማድረስ እውነት የማድረግ የትርክት ስትራቴጂን በመጠቀም በሐገር ግንባታ ላይ የአማራ ክልል ህዝብ እያበረከተ ያለውን አስተዋፅኦ በመደበቅ ከታሪክ የመነጠል ሴራ እየሠሩ ነው።
👉በጣም በሚገርም ሁኔታ ባለፉት 3 አመታት በተደረጉ ከ4 ዙር በላይ የሐገር መከላከያ ሠራዊት የቅጥር ምልመላ የአማራ ክልል ከመቸውም ጊዜ በላይ እጅግ በርካታ ወጣቶችን መልምሎ ግዙፉን የሐገር መከላከያ ሠራዊት እንዲቀላቀሉ ማድረግ ችሏል። በዚህ ምልመላ ወቅት ግን እነዚህ የአማራ ህዝብ ተቆርቋሪ ነን የሚሉ ጽንፈኞች የአማራ ክልል ወጣት ወደ አገር መከላከያ ተቋም እንዳይገባ ሲቀሠቅሱ የነበረውን ቅስቀሳ ማንም የማይረሣው የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው ⁉️ነገር ግን የአማራ ክልል መንግስት በየደረጃው ያለ አመራር የእነዚህን ጽንፈኞች የሴራ ጩኸት ወዠብ ተቋቁሞ ቆፍጠን ያለ ስራ በመስራቱ በአሁኑ ሠአት በኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ውስጥ እጅግ በርካታ የአማራ ክልል ተወላጅ የሆኑ ወጣት የሐገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ይገኛሉ።
👉በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አመራር ሚናም ቢሆን በአሁኑ ሠአት ከአማራ ክልል ህዝብ አብራክ የተገኙ ለሐገር እጅግ አስደናቂ ሚና እያበረከቱ የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች ቁጥር ቀላል አይደለም። በመከላከያ ሠራዊት የእዝ መዋቅር አመራር ውስጥም ቢሆን በሠራዊት አመራር ብቃት ፣በውጊያ ጥበብ እና ስልት ፣በውጊያ አደረጃጀት እና የጠላትን የውጊያ አሠላለፍን የማንበብ ጥበብ የተካኑ ከፍተኛ የሠራዊት አመራሮችን ዛሬም እያበረከተ የሚገኝ ህዝብ ነው የአማራ ክልል ህዝብ ።
👉በጣም በሚገርማችሁ በአየር ሀይል ተቋም ውስጥ በባለፈው የሀገር ግዳጅ ጥሪ ተደርጎላቸው ተመልሠው እንዲቀላቀሉ የተደረጉትን ጨምሮ በርካታ ከአማራ ክልል ህዝብ አብራክ የተገኙ ጀግኖች በአየር ሀይል ተቋም ውስጥ ይገኛሉ። እስኪ የአየር ሀይል ተቋምን ጠይቁት የጦር ጀትን ሠማይ ላይ እንደፈለጉ የሚያስጨፍሩ ጀግኖች አሉኝ ከሚላቸው ውስጥ የአማራ ክልል ተወላጅ የሆኑት ምን ያህል እንደሆኑ ⁉️
በአሁኑ ሠአት የአማራ ጠበቃ ነን የሚሉ ሴረኛ ጽንፈኞች የሚያደርጉት ሠራዊቱን የአንድ ብሄር የማስመሠል ጥላሸት የአማራ ክልል ህዝብ በሀገር ግንባታ ላይ ያለውን ሚና በውሸት ጩኸት በመደበቅ ሀገር ከመገንባት እና ከማሻገር ታሪካዊ ድርሻ እንዳላበረከተ የመነጠል የሴራ ጩኸት ነው። ‼️
በጣም የሚገርማችሁ አማራ ክልል የገጠመውን ወቅታዊ ቀውስ ለመፍታት እሳቱን ጭምር በድፍረት በመጋፈጥ በየአካባቢው ህዝብ የማረጋጋት እና የማወያየት ስራ እየሠሩ ያሉት ከአማራ ክልል ህዝብ ከገዛ አብራኩ የወጡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮች ናቸው። ተመልከቱ እነዚህ ጽንፈኞች ግን የሚቀሠቅሱት የጩኸት ቅስቀሳ የኦነግ ሸኔ ሠራዊት ሊጨፈጭፍህ አማራ ክልል ገባ ፣ኦነጎቹ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ እና አብይ አህመድ የአማራን ህዝብ ከምድረ ገፅ ለማጥፋት በአማራ ክልል ጦርነት አወጁብህ እያሉ ነው ። ‼️
ይሄ ሁሉ ስም ማጥፋት ፣ይሄ ሁሉ ጥላሸት የመቀባት ስራ ፣ከዚህ አልፎም የግድያ ተኩስ በጽንፈኞች እየተፈፀመበት በትእግስት ችሎ የህዝብና የሐገር ሠላምን ለማረጋገጥ መስዋዕትነት በመክፈል ላይ ለሚገኘው የኢትዮጵያ የሐገር መከላከያ ሠራዊት እና አመራር ታላቅ አክብሮት ይገባቸዋል።‼️
@አገር ጮሬ
"የማንም ውርጋጥ እንድፈነጭ አድርጎ ብዙ ችግር እንድፈጠር እዲል የሰጠው የመንግስት ልፍስፍስነት ነው!!"
=======================
በዚህ አገር ላይ እየሆነ ላለው ነገር ሁሉ ዋናው ተጠያቂ መንግስት ነኝ የሚለው ልፍስፍስ ቡድን ነው። ይኸ መንግስት በዚህ ልክ እየታገዘ እንኳን ፈቅ የማይል ፖሊዮ የመታው ልምሻ ነገር ነው። ብዙ ሰዎች መልካም ስማችን እየጠፋ፣ ህይዎታችን አደጋ ላይ ወድቆ፣ የማንንም ውርጋጥ ዛቻ ተቋቁመን ትክክል ነው ያልነውን መንገድ መርጠናል። ምን አልባትም ብዙዎቻችን ይህን መንገድ ባንመርጥ ኖሮ ሐገሩም መንግስቱም እስካሁን ለመቆየቱ እርግጠኛ መሆን አይቻልም። ይኸ መንግስት የተደገፈውን ሩብ ያክል ወያኔ/ኢህአዴግ አግኝቶት ቢሆን ኖሮ እስከ ደቡብ አፍሪካ ድረስ ያለውን ሐገር ሁሉ ያስገብረው ነበር ብንል ያጋነንን አይሆንም።
ለእርስ በርስ ሽኩቻ ያግዘናል በሚል የውስጥ ሚስጥር እያወጣ የሚዘረግፈው መንግስት ውስጥ ያለ ካድሬ ነው። ከውስጥ በደረሰን መረጃ እየተባለ የሐገሪቱን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ምስጢር ሳይቀር አየር ላይ ይውላል። ይህም የሚወጣው አንድ በዘር በተቧደኑ ክሊኮች ነው አንድም በጥቅም ትስስር በፈጠሩ የመንደር ኦሊጋርኪ ቡድን ነው። መንግስት ይህን መሰሉን አሰራር እስካላሻሻለ ድረስ ጉዞው እዛው ባለህበት ሂድ ይሆናል። እኔን የሚያሳስበኝ ይኸ አካሄድ ይዞን ወደ ጥልቁ እንዳይወርድ ብቻ ነው።
ከሰሞኑ በተፈጠረውም ሆነ በሌላው ጉዳይ ላይ አንድም መረጃ በአግባቡ እና በወቅቱ ከመንግስት ለህዝቡ አይደርስም። ህዝብ መረጃ የማግኘት መብት እንዳለሁ ሁሉ የሚያውቁ አይመስለኝም። ለምን እንደሆነ አላውቅም ችግር ሲፈጠር ጥጋቸውን ይዘው ይጠፋሉ። ችግሩ ትንሽ በረድ ሲል ብቅ ይላሉ። በችግር ውስጥ እንኳን የአደጋ ጊዜ መሪነት አያሳዩም። በዚህ የተነሳ ህዝቡ ለአጭበርባሪዎች፣ ለሃሰት ዜና ሰባሪዎች፣ ለጥንቆላ ፖለቲካ ተጋላጭ ይሆናል። የጠራ መረጃ ስለማይሰጥ ማንም ደስ ያለውን ያቦካል፣ ይጋግራል። በዋናነት የእዝ ሰንሰለት የሚባል ነገር ያልፈጠረበት፣ መልክ የሌለው መንግስት ነው ያጋጠመን። መንግስት መቸ ምን ያደርጋል የሚለውን እንኳን ህዝቡ ራሱም አያውቀውም ማለት ኩልል ያለ እውነት ነው።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን ነኝ የሚለው መስሪያ ቤት መቸ ምን ኮሙኒኬት እንደሚያደርግ የሚያውቅ አይመስለኝም። ቀድሞ ነገር አንድ ጉዳይ ወደ ትግበራ ከመሄዱ በፊት በቂ ውይይት ማድረግ አስፈላጊ ነው። ከውይይት በኋላ እንኳን የሙከራ ትግበራ በቀላሉ ይተገበራል። ያ ሙከራ ስኬታማ ከሆነ ወደ ሙሉ ትግበራ ይገባል። ይህን ሀ ሁ የማያውቁ ሰዎች አንድ ቅርጫት ውስጥ ተቀምጠው መንግስት ነን ይላሉ። አቅዶ መስራት ቀርቶ ችግር በተፈጠረ ቁጥር እንደ እሳት አደጋ ሰራተኛ መሯሯጥ ዋና ስራችን ከሆነ አምስት ዓመታት ከነፉ።
ማውራት እና መስራት የአራባ እና ቆቦን ያክል ተራራቁ። ድሮ ድሮ መንግስት በአንድ እዝ ስር ጠርንፎ ሁሉም ካድሬ ተመሳሳይ እቅድ ብቻ ሳይሆን ተመሳሳይ ቃላት እንዲጠቀም ይደረግ ነበር። የአሁኑ ግን ሁሉንም የሚሰማው እንደ እኛ በሶሻል ሚድያ ሆኗል። በዚህ አያያዝ የተነሳ ሐገራችን የመሰሪዎች፣ የጠላቶቻችን ተላላኪዎች፣ ያላዋቂ ሰዎች መፈንጫ ሆነች። ህዝባችንም መከራው በዛ...!
መንግስት ሆይ ወይ መንግስት ሁን፣ ወይ መንግስት ለሚሆኑት ቦታውን አመቻች። በዚህ የእሳት አደጋ ሰራተኛ ሩጫ መቶ ሜትር እንጅ ማራቶን መሮጥህን እንጃ...!
ይኸ ነው የሚሰማኝ...!
@Gashaw Mersha
Mulugeta vs Gashaw Mersha ["የትኛው ጎንደር?"]
በሙሉጌታ አንበርብር ተፃፈ:-
*******
ሰበር!
የዐቢይ አህመድ ጦር በጎንደር ወደ ሕዝብ ተኮሰ!
አማራን ለማስገበር የተላከው የዐቢይ አህመድ ጦር በዛሬው ዕለት በጎንደር አማራዎች ላይ ተኩስ ከፍቷል። በተከፈተው ተኩስም በርካታ ንጹሃን መገደላቸው ከቦታው የደረሰኝ መረጃ ያመላክታል። በተለይ ከቀኑ ስድስት ሰዓት ከአስር ደቂቃ ላይ መሐል ፒያሳ ላይ ሶስት የከተማው ወጣቶችን ተኩሱ እንደገደለ ከተለቀቀ ተንቀሳቃሽ ምስል መመልከት ችለናል።
የጎንደር ሕዝብም የተከፈተበትን ወረራ ለመቀልበስ ከፍተኛ ተጋድሎ እያደረገ መሆኑን ለማወቅ ችያለሁ።
የአማራ ሕዝባዊ እንቢተኝነት መሪዎች እና የጎንደር ወጣቶች ወደ ጎንደር የሚያስገቡ በሮች ሁሉ እንዲዘጉ እና አማራዊ ግዴታውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
ድል ለአማራ !
#AmharaStruggle
#Justice4Amhara
#AmharaGenocide
በጋሻው መርሻ ለ ሙሉጌታ አንበርብር የተሰጠ ምላሽ:-
***********
ጎንደር የት ነው? እኛ የማናውቀው ጎንደር አለ እንዴ? ለምን በዚህ ደረጃ ያልተደራጀ ህዝብ እንዲወጋ እንደፈለጋችሁ ብቻ ነው ግልፅ ያልሆነልኝ። ለማንኛውም በአካባቢው ያለው የመከላከያ ኃይል አዛዦች በአጋጣሚ አማራዎች ናቸው። ስማቸውን አጣርተህ ድረስበት። ችግሩ በውይይት ይፈታል። የማትዋጋውን ጦርነት ባትቀሰቅስ ጥሩ ነው። አንዳንዴ ዝም የምንለው ለትዝብት ሁሉ እንደሆነ ይታወቅ።
@Ebdalkachew Mola
☞በኢትዮጵያ ሉዓላዊ ቀጣና ዉስጥ የሀገር መከላከያ ሰራዊት እንዳይገባ እንዳይወጣ የሚከለክልና የሚፈቅድ፣እንዳሻው ተነስቶ መንገድ የሚዘጋ የጎበዝ አለቃ፣የመንደርን ወንበደ መንግስት ስርዓት ማስያዝ ካልቻለ እንደ ሀገር ቀላል የሚመስል ግን ትልቅ ዋጋ የሚያስከፍል ችግር ላይ እንወድቃለን!!
