en
Feedback
የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲ አሰሪዎች ፌዴሬሽን

የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲ አሰሪዎች ፌዴሬሽን

Open in Telegram

🔰We are the only Foreign Employment Associations Federation in Ethiopia 🌐 Gulf Aziz building 4th floor Room No. 404, Bole Medhanialem, Addis Ababa, Ethiopia ✍️ አስተያየት መቀበያ : @eoeaf2022bot ⚜️ Our Group : @eoeaf2022

Show more
438
Subscribers
+124 hours
+77 days
+730 days
Posts Archive
ለተከበራችሁ የፌደሬሽኑ አባል ማህበራት በሙሉ ! ዛሬ ጥር14/2016 ዓ.ም በሥራና ክህሎት ሚ/ር አማካኝነት በሃያት ሪጀንሲ ሆቴል በፍልሰት ረገድ የፋይናንስና የሴኩዩሪቲ ተቋማትን ያማከለ የፓናል ውይይት ተካሂዷል ። በውይይቱ ወቅት የተነሱ ዋና ዋና ሀሳቦች የሚከተሉት ናቸው ። #የሬሚተንስ አቅምን ማጎልበት ;የሬሚተንስ ፍሰት ማሳለጫ መላዎች # የፋይናንስ ተቋማት ሚና ሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ;የገንዘብ አጠባና ዝውውርን በመግታትና መደበኛ ፍልሰትን በማበረታታት ረገድ # የፋይናንስ ደህንነት ሚና የገንዘብ አጠባና ሕገወጥ ገንዘብ ዝውውርን በመግታት ረገድ # የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት እና አገናኝ ኤጀንሲዎች ሕጋዊ አሠራርን የማረጋገጥ ጥረቶች ላይ ያሉ ክፍተቶችን እንዴት በጋራ መልክ ማስያዝ ይቻላል በሚል : _ከኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት _ ከፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት _ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ _ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች ሰፊ ውይይት ተደርጓል ።ፌደሬሽናችንን ጨምሮ ከ14 በላይ ተቋማት ገንቢ ተሳትፎ አድርገዋል ። በቀጣይም ሕጋዊ ፍልሰት ተጠናክሮ የሚሄድበትን የሕግ ድጋፍና አመራር ለመስጠት የመንግስትን ዝግጁ መሆን እና ከባለድርሻ አካላት ጋር የበለጠ ተቀራርቦ ለመስራት ያለው ቁርጠኝነት የታየበት የፓናል ውይይት እንደነበር ለማሳወቅ እንወዳለን ። ፌደሬሽናችንም የበኩሉን ገንቢ ሚና የተጫወተበት የውይይት መድረክ እንደነበር በዚህ አጋጣሚ እንገልጻለን ።